Psalm 57 – NIRV & NASV

New International Reader’s Version

Psalm 57:1-11

Psalm 57

For the director of music. A miktam of David when he had run away from Saul into the cave. To the tune of “Do Not Destroy.”

1Have mercy on me, God. Have mercy on me.

I go to you for safety.

I will find safety in the shadow of your wings.

There I will stay until the danger is gone.

2I cry out to God Most High.

I cry out to God, and he shows that I am right.

3He answers from heaven and saves me.

He puts to shame those who chase me.

He shows his love and that he is faithful.

4Men who are like lions are all around me.

I am forced to lie down among people who are like hungry animals.

Their teeth are like spears and arrows.

Their tongues are like sharp swords.

5God, may you be honored above the heavens.

Let your glory be over the whole earth.

6My enemies spread a net to catch me by the feet.

I felt helpless.

They dug a pit in my path.

But they fell into it themselves.

7God, my heart feels secure.

My heart feels secure.

I will sing and make music to you.

8My spirit, wake up!

Harp and lyre, wake up!

I want to sing and make music before the sun rises.

9Lord, I will praise you among the nations.

I will sing about you among the people of the earth.

10Great is your love. It reaches to the heavens.

Your truth reaches to the skies.

11God, may you be honored above the heavens.

Let your glory be over the whole earth.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 57:1-11

መዝሙር 57

በጨካኝ ጠላቶች ዘንድ

57፥7-11 ተጓ ምብ – መዝ 108፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ “አታጥፋ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤ ከሳኦል ፊት ሸሽቶ በዋሻ በነበረበት ጊዜ፤ የዳዊት ቅኔ57 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ማረኝ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ማረኝ፤

ነፍሴ አንተን መጠጊያ አድርጋለችና፤

በክንፎችህ ሥር እጠለላለሁ።

2ለእኔ ያሰበውን ወደሚፈጽምልኝ አምላክ፣

ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጮኻለሁ።

3ከሰማይ ልኮ ያድነኛል፤

የረገጡኝን ያዋርዳቸዋል፤ ሴላ

እግዚአብሔር ምሕረቱንና ታማኝነቱን ይልካል።

4ነፍሴ በአንበሶች ተከብባለች፤

በሚዘነጣጥሉ አራዊት መካከል ወድቄአለሁ፤

እነዚህም፣ ጥርሳቸው ጦርና ፍላጻ፣

ምላሳቸውም የተሳለ ሰይፍ የሆኑ ሰዎች ናቸው።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።

6ለእግሬ ወጥመድን ዘረጉ፤

ነፍሴንም አጐበጧት፤

በመተላለፊያዬ ላይ ጕድጓድ ቈፈሩ፤

ነገር ግን ራሳቸው ገቡበት። ሴላ

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤

ልቤ ጽኑ ነው፤

እቀኛለሁ፤ አዜማለሁ።

8ነፍሴ ሆይ፤ ንቂ!

በገናና መሰንቆም ተነሡ

እኔም በማለዳ እነሣለሁ።

9ጌታ ሆይ፤ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤

በሰዎችም መካከል እዘምርልሃለሁ፤

10ምሕረትህ እስከ ሰማያት ከፍ ብላለችና፤

ታማኝነትህም እስከ ደመናት ትደርሳለች።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።