نشيد الأنشاد 6 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

نشيد الأنشاد 6:1-13

1(بَنَاتُ أُورُشَلِيمَ): أَيْنَ ذَهَبَ حَبِيبُكِ أَيَّتُهَا الْجَمِيلَةُ بَيْنَ النِّسَاءِ؟ إِلَى أَيْنَ تَحَوَّلَ حَبِيبُكِ فَنَبْحَثَ عَنْهُ مَعَكِ؟

2(الْمَحْبُوبَةُ): قَدِ انْطَلَقَ حَبِيبِي إِلَى جَنَّتِهِ، إِلَى خَمَائِلِ الأَطْيَابِ لِيَرْعَى فِي الرَّوْضَاتِ وَيَقْطِفَ السَّوْسَنَ. 3أَنَا لِحَبِيبِي، وَحَبِيبِي لِي، وَهُوَ يَرْعَى بَيْنَ السَّوْسَنِ.

4(المُحِبُّ): أَنْتِ جَمِيلَةٌ يَا حَبِيبَتِي كَتِرْصَةَ، حَسْنَاءُ كَأُورُشَلِيمَ، وَجَلِيلَةٌ كَجَيْشٍ يَرْفَعُ أَعْلامَهُ. 5أَشِيحِي بِعَيْنَيْكِ عَنِّي فَقَدْ قَهَرَتَانِي. شَعْرُكِ كَقَطِيعِ مَاعِزٍ مُنْحَدِرٍ مِنْ جِلْعَادَ. 6أَسْنَانُكِ فِي بَيَاضِهَا كَقَطِيعِ غَنَمٍ خَارِجٍ مِنَ الاغْتِسَالِ؛ كُلُّ وَاحِدَةٍ مِنْهَا ذَاتُ تَوْأَمٍ وَمَا فِيهَا عَقِيمٌ. 7خَدَّاكِ تَحْتَ نَقَابِكِ كَفِلْقَتَيْ رُمَّانَةٍ. 8هُنَاكَ سِتُّونَ مَلِكَةً وَثَمَانُونَ سُرِّيَّةً وَعَذَارَى لَا يُحْصَى لَهُنَّ عَدَدٌ. 9لَكِنَّكِ يَا حَمَامَتِي يَا كَامِلَتِي فَرِيدَةٌ، الابْنَةُ الْوَحِيدَةُ لأُمِّهَا، الأَعَزُّ عَلَى مَنْ أَنْجَبَتْهَا. رَأَتْهَا الْعَذَارَى فَطَوَّبْنَهَا، وَشَاهَدَتْهَا الْمَلِكَاتُ وَالسَّرَارِي فَمَدَحْنَهَا. 10مَنْ هَذِهِ الطَّالِعَةُ كَالْفَجْرِ، الْجَمِيلَةُ كَالْبَدْرِ، الْمُشْرِقَةُ كَالشَّمْسِ، الْجَلِيلَةُ كَجَيْشٍ يَرْفَعُ أَعْلامَهُ؟

11(الْمَحْبُوبَةُ): نَزَلْتُ إِلَى حَدِيقَةِ الْجَوْزِ لأَرَى ثَمَرَ الْوَادِي الْجَدِيدَ، وَأَنْظُرَ هَلْ أَزْهَرَ الْكَرْمُ وَنَوَّرَ الرُّمَّانُ؟ 12وَقَبْلَ أَنْ أُدْرِكَ مَا يَجْرِي وَجَدْتُ نَفْسِي بَيْنَ أُمَرَاءِ قَوْمِي فَهَرَبْتُ.

13(بَنَاتُ أُورُشَلِيمَ): ارْجِعِي، ارْجِعِي يَا شُولَمِّيثُ، اِرْجِعِي، اِرْجِعِي لِنَتَأَمَّلَ فِيكِ.

(الْمَحْبُوبَةُ): مَاذَا تَرَوْنَ فِي شُولَمِّيثَ؟

(المُحِبُّ): مِثْلَ رَقْصِ صَفَّيْنِ!

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 6:1-13

ባልንጀሮቿ

1አንቺ ከሴቶች ሁሉ የተዋብሽ ሆይ፤

ውድሽ ወዴት ሄደ?

አብረንሽም እንድንፈልገው፣

ውድሽ የሄደው በየት በኩል ነው?

ሙሽራዪቱ

2ውዴ መንጋውን ለማሰማራት፣

ውብ አበቦችንም ለመሰብሰብ፣

የቅመማ ቅመም መደቦቹ ወዳሉበት፣

ወደ አትክልት ቦታው ወርዷል።

3እኔ የውዴ ነኝ፤ ውዴም የእኔ ነው፤

መንጋውንም በውብ አበቦች መካከል ያሰማራል።

ሙሽራው

4ውዴ ሆይ፤ አንቺ እንደ ቴርሳ የተዋብሽ፣

እንደ ኢየሩሳሌም ያማርሽ፣

ዐርማቸውን እንደ ያዙ ወታደሮችም ግርማን የተጐናጸፍሽ ነሽ።

5አስጨንቀውኛልና፣

እባክሽ ዐይኖችሽን ከእኔ ላይ አንሺ፤

ጠጕርሽ ከገለዓድ ተራራ የሚወርድ፣

የፍየል መንጋ ይመስላል።

6ጥርሶችሽ

ከመታጠቢያ እንደ ወጡ የበግ መንጋ ናቸው፤

ሁሉም መንታ መንታ የወለዱ፣

ከመካከላቸውም መካን የሌለባቸው ናቸው።

7ከመሸፈኛሽ ውስጥ ያሉት ጕንጮችሽ፣

ለሁለት የተከፈለ ሮማን ይመስላሉ።

8ስድሳ ንግሥቶች፣

ሰማንያ ቁባቶች፣

ቍጥራቸውም የበዛ ደናግል ሊኖሩ ይችላሉ፤

9እንከን የሌለባት ርግቤ ግን ልዩ ናት፤

እርሷ ለወለደቻት የተመረጠች፣

ለእናቷም አንዲት ናት፤

ቈነጃጅት አይተው “የተባረክሽ ነሽ”

አሏት፤

ንግሥቶችና ቁባቶችም አመሰገኗት።

ባልንጀሮቿ

10እንደ ንጋት ብርሃን ብቅ የምትል፣

እንደ ጨረቃ የደመቀች፣ እንደ ፀሓይ ያበራች፣

ዐርማ ይዞ በሰልፍ እንደ ወጣ ሰራዊት ግርማዋ የሚያስፈራ ይህች ማን ናት?

ሙሽራው

11በሸለቆው ውስጥ አዲስ የበቀሉትን አትክልቶች ለማየት፣

ወይኑ ማቈጥቈጡን፣

ሮማኑ ማበቡን ለመመልከት፣

ወደ ለውዙ ተክል ቦታ ወረድሁ።

12ይህን ከማወቄ በፊት፣

ምኞቴ በሕዝቤ ንጉሣዊ ሠረገሎች መካከል6፥12 ወይም ከአሚናዳብ ሠረገሎች መካከል ወይም ከልዑል ሕዝቦች ሠረገሎች መካከል አስቀመጠኝ።

ባልንጀሮቿ

13አንቺ ሱላማጢስ ሆይ፤ ተመለሺ፤

ኧረ ተመለሺ፤ እንድናይሽ ተመለሺ፤ እባክሽ ተመለሺ።

ሙሽራው

የመሃናይምን ዘፈን እንደሚመለከት ሰው፣

ሱላማጢስን የምትመለከቷት ለምንድን ነው?