مزمور 86 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 86:1-17

الْمَزْمُورُ السَّادِسُ وَالثَّمَانُونَ

صَلاةٌ رَفَعَهَا دَاوُدُ

1أَرْهِفْ يَا رَبُّ إِلَيَّ أُذُنَكَ، اسْتَجِبْ لِي، فَإِنِّي مِسْكِينٌ وَبَائِسٌ. 2احْفَظْ نَفْسِي فَإِنِّي تَقِيٌّ يَا إِلَهِي، خَلِّصْ أَنْتَ عَبْدَكَ الْوَاثِقَ بِكَ. 3ارْحَمْنِي يَا رَبُّ فَإِنِّي بِكَ أَسْتَغِيثُ طَوَالَ النَّهَارِ. 4فَرِّحْ نَفْسَ عَبْدِكَ، فَإِنِّي إِلَيْكَ أَيُّهَا السَّيِّدُ أَرْفَعُ نَفْسِي. 5لأَنَّكَ أَنْتَ يَا رَبُّ طَيِّبٌ وَغَفُورٌ، وَكَثِيرُ الرَّحْمَةِ لِجَمِيعِ الَّذِينَ يَدْعُونَكَ.

6يَا رَبُّ أَصْغِ إِلَى صَلاتِي وَاسْتَمِعْ إِلَى صَوْتِ تَضَرُّعَاتِي. 7فِي يَوْمِ ضِيقِي أَدْعُوكَ لأَنَّكَ تَسْتَجِيبُنِي. 8لَا نَظِيرَ لَكَ بَيْنَ الآلِهَةِ يَا رَبُّ، وَلَيْسَ مَنْ يَعْمَلُ كَأَعْمَالِكَ. 9تُقْبِلُ جَمِيعُ الأُمَمِ الَّتِي صَنَعْتَهَا لِتَسْجُدَ أَمَامَكَ يَا رَبُّ وَتُمَجِّدَ اسْمَكَ. 10فَإِنَّكَ عَظِيمٌ وَصَانِعٌ عَجَائِبَ. أَنْتَ اللهُ وَحْدَكَ.

11يَا رَبُّ عَلِّمْنِي طَرِيقَكَ فَأَسْلُكَ بِمُوجِبِ حَقِّكَ. وَحِّدْ قَلْبِي لِيَخَافَ اسْمَكَ. 12أَحْمَدُكَ يَا رَبُّ إِلَهِي بِكَامِلِ قَلْبِي، وَأُمَجِّدُ اسْمَكَ إِلَى الأَبَدِ. 13لأَنَّ رَحْمَتَكَ عَظِيمَةٌ نَحْوِي، وَقَدْ نَجَّيْتَ نَفْسِي مِنَ الْهَاوِيَةِ السُّفْلَى.

14يَا اللهُ قَدْ ثَارَ عَلَيَّ الْمُتَكَبِّرُونَ، وَجَمَاعَةُ الظَّالِمِينَ يَطْلُبُونَ قَتْلِي، غَيْرَ عَابِئِينَ بِكَ. 15إِنَّمَا أَنْتَ يَا رَبُّ إِلَهٌ رَحِيمٌ وَرَؤُوفٌ وَبَطِيءُ الْغَضَبِ وَوَافِرُ الرَّحْمَةِ وَالْحَقِّ. 16الْتَفِتْ إِلَيَّ وَارْحَمْنِي. أَعْطِنِي أَنَا عَبْدَكَ قُوَّتَكَ، وَخَلِّصْنِي أَنَا ابْنَ أَمَتِكَ. 17اصْنَعْ مَعِي آيَةً لِلْخَيْرِ، فَيَرَاهَا مُبْغِضِيَّ وَيَعْتَرِيَهُمُ الْخِزْيُ، فَإِنَّكَ أَنْتَ يَا رَبُّ قَدْ أَعَنْتَنِي وَعَزَّيْتَنِي.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 86:1-17

መዝሙር 86

የመከራ ጊዜ ጸሎት

የዳዊት ጸሎት።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጆሮህን ወደ እኔ ጣል፤ ስማኝም፤

እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝና።

2ለአንተ የተለየሁ ሰው ነኝና ነፍሴን ጠብቃት፤

አንተ አምላኬ ሆይ፤

በአንተ የታመነብህን ባሪያህን አድን።

3ጌታ ሆይ፤ ማረኝ፤

ቀኑን ሙሉ ወደ አንተ እጮኻለሁና።

4የባሪያህን ነፍስ ደስ አሰኛት፤

ጌታ ሆይ፤ ነፍሴን ወደ አንተ አነሣለሁና።

5ጌታ ሆይ፤ አንተ ቸርና ይቅር ባይ ነህ፤

ለሚጠሩህ ሁሉ ምሕረትህ ወሰን የለውም።

6እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን አድምጥ፤

የልመናዬን ጩኸት ስማ።

7አንተ ስለምትመልስልኝ፣

በመከራዬ ቀን ወደ አንተ እጣራለሁ።

8ጌታ ሆይ፤ ከአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ የለም፤

ከአንተም ሥራ ጋር የሚወዳደር ሥራ የለም።

9ጌታ ሆይ፤ አንተ የሠራሃቸው ሕዝቦች ሁሉ፣

መጥተው በፊትህ ይሰግዳሉ፤

ለስምህም ክብር ይሰጣሉ፤

10አንተ ታላቅ ነህና፤ ታምራትም ትሠራለህ፤

አንተ ብቻህን አምላክ ነህ።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ መንገድህን አስተምረኝ፤

በእውነትህም እሄዳለሁ፤

ስምህን እፈራ ዘንድ፣

ያልተከፋፈለ ልብ ስጠኝ።

12ጌታ አምላኬ ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤

ስምህንም ለዘላለም አከብራለሁ፤

13ለእኔ ያሳየሃት ምሕረት ታላቅ ናትና፤

ነፍሴንም ከሲኦል86፥13 አንዳንዶች መቃብር ይላሉ። ጥልቀት አውጥተሃል።

14አምላክ ሆይ፤ እብሪተኞች ተነሥተውብኛል፤

የዐመፀኞችም ጉባኤ ነፍሴን ይሿታል፤

አንተንም ከምንም አልቈጠሩም።

15ጌታ ሆይ፤ አንተ ግን መሓሪና ርኅሩኅ አምላክ ነህ፤

ለቍጣ የዘገየህ፣ ምሕረትህና ታማኝነትህ የበዛ።

16ወደ እኔ ተመልከት፤ ማረኝም፤

ለባሪያህ ኀይልህን ስጥ፤

የሴት ባሪያህንም86፥16 ታማኝ ወንድ ልጅህን የሚሉ አሉ። ልጅ አድን።

17የሚጠሉኝ አይተው ያፍሩ ዘንድ፣

የበጎነትህን ምልክት አሳየኝ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ረድተኸኛልና፤ አጽናንተኸኛልም።