مزمور 79 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 79:1-13

الْمَزْمُورُ التَّاسِعُ وَالسَّبْعُونَ

مَزْمُورٌ لآسَافَ

1يَا اللهُ، إِنَّ الأُمَمَ قَدْ دَخَلَتْ مِيرَاثَكَ وَنَجَّسَتْ هَيْكَلَكَ الْمُقَدَّسَ وَجَعَلَتْ أُورُشَلِيمَ أَكْوَاماً. 2جَعَلُوا جُثَثَ عَبِيدِكَ مَأْكَلاً لِطُيُورِ السَّمَاءِ، وَلُحُومَ قِدِّيسِيكَ لِوُحُوشِ الأَرْضِ. 3سَفَكُوا دِمَاءَهُمْ كَالْمَاءِ حَوْلَ أُورُشَلِيمَ، وَلَيْسَ هُنَاكَ مَنْ يَدْفِنُهُمْ. 4قَدْ صِرْنَا عَاراً عِنْدَ جِيرَانِنَا، وَمَثَارَ هُزْءٍ وَأُضْحُوكَةً لِمَنْ حَوْلَنَا. 5إِلَى مَتَى يَدُومُ هَذَا يَا رَبُّ؟ أَتَبْقَى غَاضِباً تَتَّقِدُ غَيْرَتُكَ كَالنَّارِ إِلَى الأَبَدِ؟ 6صُبَّ غَضَبَكَ عَلَى الأُمَمِ الَّذِينَ لَمْ يَعْرِفُوكَ، وَعَلَى الْمَمَالِكِ الَّتِي لَمْ تَدْعُ بِاسْمِكَ، 7فَإِنَّهُمْ قَدِ افْتَرَسُوا يَعْقُوبَ وَقَوَّضُوا مَسْكَنَهُ.

8لَا تَذْكُرْ عَلَيْنَا آثَامَ أَجْدَادِنَا، بَلْ دَعْ مَرَاحِمَكَ تُوَافِينَا سَرِيعاً، لأَنَّنَا قَدْ تَذَلَّلْنَا جِدّاً. 9أَغِثْنَا أَيُّهَا الإِلَهُ مُخَلِّصُنَا مِنْ أَجْلِ مَجْدِكَ. أَنْقِذْنَا وَاغْفِرْ لَنَا خَطَايَانَا مِنْ أَجْلِ اسْمِكَ. 10لِمَاذَا تَسْأَلُنَا الأُمَمُ: أَيْنَ إِلَهُكُمْ؟ دَعْنَا نَرَى كَيْفَ يَذِيعُ بَيْنَ الأُمَمِ خَبَرُ انْتِقَامِكَ لِدِمَاءِ عَبِيدِكَ الْمَسْفُوكَةِ. 11لِيَتَصَاعَدْ أَمَامَكَ أَنِينُ الْمَأْسُورِ. حَافِظْ بِعَظَمَةِ قُوَّتِكَ عَلَى الْمَحْكُومِ عَلَيْهِمْ بِالْمَوْتِ. 12رُدَّ يَا رَبُّ عَلَى الأُمَمِ سَبْعَ مَرَّاتٍ مَا عَيَّرُوكَ وَأَهَانُوكَ بِهِ، 13فَنَحْمَدَكَ نَحْنُ شَعْبَكَ وَغَنَمَ مَرْعَاكَ إِلَى الأَبَدِ وَنُذِيعَ تَسْبِيحَكَ مِنْ جِيلٍ إِلَى جِيلٍ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 79:1-13

መዝሙር 79

ብሔራዊ ሰቈቃ

የአሳፍ መዝሙር።

1አምላክ ሆይ፤ ሕዝቦች ርስትህን ወረሩ፤

የተቀደሰውን ቤተ መቅደስህን አረከሱ፤

ኢየሩሳሌምንም አፈራርሰው ጣሏት።

2የባሪያዎችህን ሬሳ ለሰማይ ወፎች፣

የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት፣

ምግብ አድርገው ሰጡ።

3ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ፣

እንደ ውሃ አፈሰሱ፤

የሚቀብራቸውም አልተገኘም።

4እኛም ለጎረቤቶቻችን መዘባበቻ፣

በዙሪያችንም ላሉት መሣቂያ መሣለቂያ ሆንን።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ነው?

የምትቈጣውስ ለዘላለም ነውን?

ቅናትህስ እንደ እሳት ሲነድድ ይኖራልን?

6በማያውቁህ ሕዝቦች ላይ፣

ስምህን በማይጠሩ፣

መንግሥታት ላይ፣

መዓትህን አፍስስ፤

7ያዕቆብን በልተውታልና፤

መኖሪያ ቦታውንም ባድማ አድርገዋል።

8የአባቶቻችንን ኀጢአት በእኛ ላይ አትቍጠርብን፤

ምሕረትህ ፈጥና ወደ እኛ ትምጣ፤

በጭንቅ ላይ እንገኛለንና።

9አዳኛችን የሆንህ አምላክ ሆይ፤

ስለ ስምህ ክብር ብለህ ርዳን፤

ስለ ስምህ ስትል፣

ታደገን፤ ኀጢአታችንንም ይቅር በል።

10ሕዝቦች፣ “አምላካቸው የት አለ?”

ለምን ይበሉ?

የፈሰሰውን የአገልጋዮችህን ደም በቀል፣

ዐይናችን እያየ ሕዝቦች ይወቁት።

11የእስረኞች ሰቈቃ በፊትህ ይድረስ፤

በክንድህም ብርታት፣

ሞት የተፈረደባቸውን አድን።

12ጌታ ሆይ፤ ጎረቤቶቻችን በአንተ ላይ የተዘባበቱትን መዘባበት፣

ሰባት ዕጥፍ አድርገህ አስታቅፋቸው።

13እኛ ሕዝብህ፣ የማሰማሪያህ በጎችህ፣

ለዘላለም ምስጋና እናቀርብልሃለን፤

ከትውልድ እስከ ትውልድም፣

ውለታህን እንናገራለን።