مزمور 63 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 63:1-11

الْمَزْمُورُ الثَّالِثُ وَالسِّتُّونَ

مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ عِنْدَمَا كَانَ فِي بَرِّيَّةِ يَهُوذَا

1يَا اللهُ أَنْتَ إِلَهِي وَإِيَّاكَ أَطْلُبُ بَاكِراً. عَطِشَتْ إِلَيْكَ نَفْسِي وَيَشْتَاقُ إِلَيْكَ جِسْمِي فِي أَرْضٍ قَاحِلَةٍ يَابِسَةٍ لَا مَاءَ فِيهَا، 2حَتَّى أُعَايِنَ قُدْرَتَكَ وَمَجْدَكَ، مِثْلَمَا رَأَيْتُكَ فِي مَوْضِعِكَ الْمُقَدَّسِ. 3لأَنَّ رَحْمَتَكَ خَيْرٌ مِنَ الْحَيَاةِ، لِذَلِكَ تُسَبِّحُكَ شَفَتَايَ. 4أَحْمَدُكَ عَلَى بَرَكَاتِكَ مَدَى حَيَاتِي، وَبِاسْمِكَ أَرْفَعُ يَدَيَّ مُبْتَهِلاً. 5تَشْبَعُ نَفْسِي كَأَنَّهَا أَكَلَتْ مِنَ الشَّحْمِ وَالدَّسَمِ، وَيُسَبِّحُكَ فَمِي بِشَفَتَيْنِ مُبْتَهِجَتَيْنِ 6أَذْكُرُكَ عَلَى فِرَاشِي وَأَتَأَمَّلُ فِيكَ فِي أَثْنَاءِ اللَّيْلِ. 7لأَنَّكَ كُنْتَ عَوْناً لِي، فَإِنِّي فِي ظِلِّ جَنَاحَيْكَ أُرَنِّمُ مُبْتَهِجاً.

8تَتَعَلَّقُ نَفْسِي بِكَ. يَمِينُكَ تَدْعَمُنِي 9أَمَّا طَالِبُو نَفْسِي لِيُهْلِكُوهَا فَسَيَدْخُلُونَ أَسْفَلَ أَعْمَاقِ الأَرْضِ. 10يُسَلَّمُونَ إِلَى حَدِّ السَّيْفِ وَيَضْحَوْنَ مَأْكَلاً لِبَنَاتِ آوَى. 11أَمَّا الْمَلِكُ فَيَفْرَحُ بِاللهِ وَيَفْتَخِرُ بِهِ كُلُّ مَنْ يُقْسِمُ (صَادِقاً) لأَنَّ أَفْوَاهَ النَّاطِقِينَ بِالْكَذِبِ تُسَدُّ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 63:1-11

መዝሙር 63

እግዚአብሔርን መፈለግ

በይሁዳ ምድረ በዳ በነበረ ጊዜ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አምላኬ ነህ፤

አንተን ከልብ እሻለሁ፤ ውሃ በሌለበት፣

በደረቅና በተራቈተ ምድር፣

ነፍሴ አንተን ተጠማች፤

ሥጋዬም አንተን ናፈቀች።

2ስለዚህ በመቅደስ ውስጥ አየሁህ፤

ኀይልህንና ክብርህንም ተመለከትሁ።

3ምሕረትህ ከሕይወት ይበልጣልና፤

ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።

4እንግዲህ፣ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ፤

በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ።

5ነፍሴ በቅቤና በሥብ እንደሚረካ ሰው ትረካለች፤

አፌም በሚያዜሙ ከንፈሮች በደስታ ያወድስሃል።

6በመኝታዬ ዐስብሃለሁ፤

ሌሊቱንም ሁሉ ስለ አንተ አሰላስላለሁ።

7አንተ ረዳቴ ነህና፣

በክንፎችህ ሥር ተጠልዬ በደስታ እዘምራለሁ።

8ነፍሴ አንተን የሙጥኝ ብላለች፤

ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች።

9ነፍሴን ለማጥፋት የሚሹ ግን፣

ወደ ምድር ጥልቅ ይወርዳሉ፤

10ለሰይፍ ዐልፈው ይሰጣሉ፤

የቀበሮዎችም ምግብ ይሆናሉ።

11ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል፤

በእግዚአብሔርም ስም ቃል የሚገቡ ሁሉ ይከብራሉ፤

የሐሰተኞች አንደበትም ትዘጋለች።