مزمور 41 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 41:1-13

الْمَزْمُورُ الْحَادِي وَالأَرْبَعُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ، مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1طُوبَى لِلْمُتَرَفِّقِ بِالْمِسْكِينِ، فَإِنَّ الرَّبَّ يُنْقِذُهُ فِي يَوْمِ الشَّرِّ. 2الرَّبُّ يَحْفَظُهُ وَيُحْيِيهِ وَيُسْعِدُهُ فِي الأَرْضِ، وَلَا يُسَلِّمُهُ إِلَى مَقَاصِدِ أَعْدَائِهِ. 3يَعْضُدُهُ الرَّبُّ عَلَى فِرَاشِ الأَلَمِ، وَيَرُدُّ عَافِيَتَهُ.

4وَأَنَا قُلْتُ: يَا رَبُّ ارْحَمْنِي! أَبْرِئْ نَفْسِي لأَنِّي قَدْ أَخْطَأْتُ إِلَيْكَ. 5أَعْدَائِي يَتَآمَرُونَ عَلَيَّ بِالشَّرِّ وَيَقُولُونَ: «مَتَى يَمُوتُ وَيَنْقَرِضُ اسْمُهُ؟» 6إِنْ أَقْبَلَ لِيَرَانِي، يُبْدِي لِي نِفَاقاً وَيُضْمِرُ فِي قَلْبِهِ شَرّاً يُشِيعُهُ عَنِّي حَالَمَا يُفَارِقُنِي. 7جَمِيعُ مُبْغِضِيَّ يَتَهَامَسُونَ عَلَيَّ، وَيَتَآمَرُونَ عَلَى إِيذَائِي 8قَائِلِينَ: «قَدِ اعْتَرَاهُ دَاءٌ عُضَالٌ، وَلَنْ يَقُومَ مِنْ فِرَاشِهِ أَبَداً». 9حَتَّى صَدِيقِي الْمُلازِمُ لِي الَّذِي وَثِقْتُ بِهِ، الآكِلُ مِنْ طَعَامِي قَدِ انْقَلَبَ عَلَيَّ، وَرَفَعَ عَلَيَّ عَقِبَهُ.

10أَمَّا أَنْتَ يَا رَبُّ فَارْحَمْنِي وَاشْفِنِي، فَأُجَازِيَهُمْ. 11قَدْ أَدْرَكْتُ أَنِّي حَظِيتُ بِرِضَاكَ (حِينَ نَصَرْتَنِي) فَلَمْ يُطْلِقْ عَلَيَّ عَدُوِّي هُتَافَ الظَّفَرِ 12فَإِنَّكَ تَدْعَمُنِي فِي كَمَالِي، وَتُقِيمُنِي فِي مَحْضَرِكَ إِلَى الأَبَدِ. 13تَبَارَكَ الرَّبُّ إِلَهُ إِسْرَائِيلَ، مِنَ الأَزَلِ وَإِلَى الأَبَدِ. آمِين فَآمِين.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 41:1-13

መዝሙር 41

የሕመምተኛና የብቸኛ ሰው ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ለድኾች የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው፤

እርሱንም እግዚአብሔር በክፉ ቀን ይታደገዋል።

2እግዚአብሔር ይጠብቀዋል፤ በሕይወትም ያኖረዋል፤

በምድርም ላይ ይባርከዋል፤

ለጠላቶቹም ምኞት አሳልፎ አይሰጠውም።

3ታሞ ባለበት ዐልጋ ላይ እግዚአብሔር ይንከባከበዋል፤

በበሽታውም ጊዜ መኝታውን ያነጥፍለታል።

4እኔም፣ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረት አድርግልኝ፤

አንተን በድያለሁና ነፍሴን ፈውሳት” አልሁ።

5ጠላቶቼ በክፋት በመናገር፣ “የሚሞተው መቼ ነው? ስሙስ

የሚደመሰሰው ምን ቀን ነው?” ይላሉ።

6ሊጠይቀኝ የሚመጣ ቢኖር፣

በልቡ ስድብ እያጠራቀመ፣ ከዐንገት በላይ ይናገራል፤

ወጥቶም ወሬ ይነዛል።

7ጠላቶቼ ሁሉ ግንባር ፈጥረው ይንሾካሾኩብኛል፤

እንዲህ እያሉም፣

የከፋ ነገር በላዬ ያውጠነጥናሉ፤

8“ክፉ ደዌ ይዞታል፤

ከእንግዲህም ከተኛበት አይነሣም።”

9እንጀራዬን ተካፍሎኝ የበላ፣

የምተማመንበትም የቅርብ ወዳጄ፣

በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣ።

10እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ምሕረት አድርግልኝ፤

የእጃቸውን እንድከፍላቸው አስነሣኝ።

11ጠላቴ በላዬ ድል አላገኘምና፣

እንደ ወደድኸኝ በዚህ ዐወቅሁ።

12ስለ ጭንቀቴ ደግፈህ ይዘኸኛል፤

በፊትህም ለዘላለም ታኖረኛለህ።

13የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር

ከዘላለም እስከ ዘላለም የተባረከ ይሁን፤

አሜን፤ አሜን።