مزمور 26 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 26:1-12

الْمَزْمُورُ السَّادِسُ وَالْعِشْرُونَ

لِدَاوُدَ

1رَبُّ أَظْهِرْ بَرَاءَتِي لأَنِّي قَدْ سَلَكْتُ بِكَمَالِي، وَعَلَيْكَ تَوَكَّلْتُ فَلَا أَتَزَعْزَعُ 2افْحَصْنِي أَيُّهَا الرَّبُّ وَاخْتَبِرْنِي. امْتَحِنْ دَخَائِلِي وَقَلْبِي، 3لأَنَّ رَحْمَتَكَ نُصْبَ عَيْنَيَّ، وَقَدْ سَلَكْتُ فِي حَقِّكَ. 4لَمْ أُجَالِسْ أَهْلَ الْبَاطِلِ وَمَعَ الْمُنَافِقِينَ لَا أَشْتَرِكُ. 5بَلْ أَبْغَضْتُ مَعْشَرَ فَاعِلِي الإِثْمِ، وَلَمْ أَجْلِسْ مَعَ الأَشْرَارِ. 6أَغْسِلُ يَدَيَّ عُرْبُونَ بَرَاءَتِي وَأَنْضَمُّ إِلَى الْمُجْتَمِعِينَ حَوْلَ مَذْبَحِكَ يَا رَبُّ. 7مُتَرَنِّماً بِصَوْتِ الْحَمْدِ وَأُحَدِّثُ بِأَعْمَالِكَ الْعَجِيبَةِ كُلِّهَا. 8رَبُّ، قَدْ أَحْبَبْتُ الإِقَامَةَ فِي بَيْتِكَ، حَيْثُ يَحِلُّ مَجْدُكَ.

9فَلَا تَجْمَعْ نَفْسِي مَعَ الْخَاطِئِينَ، وَلَا حَيَاتِي مَعَ سَافِكِي الدَّمِ، 10الَّذِينَ أَيْدِيهِمْ مُلَوَّثَةٌ بِالسُّوءِ، وَيَمِينُهُمْ مَلأَى بِالرِّشْوَةِ. 11أَمَّا أَنَا فَبِكَمَالِي أَسْلُكُ، فَافْدِنِي وَتَحَنَّنْ عَلَيَّ. 12قَدَمَايَ مُنْتَصِبَتَانِ عَلَى طَرِيقٍ مُسْتَوِيَةٍ، وَأُرَنِّمُ لِلرَّبِّ جَهْراً فِي مَحَافِلِ الْعِبَادَةِ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 26:1-12

መዝሙር 26

የንጹሕ ሰው ጸሎት

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ያለ ነቀፋ እንደ መሆኔ፣

አንተው ፍረድልኝ።

ወዲያ ወዲህ ሳልልም፣

በእግዚአብሔር ታምኛለሁ።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈትነኝ፤

መርምረኝም፤

ልቤንና ውስጤን መርምር፤

3ምሕረትህ ከፊቴ አልተለየምና፣

በእውነትህም ተመላለስሁ።

4ከማይረቡ ጋር አልተቀመጥሁም፤

ከግብዞችም ጋር አልተባበርሁም።

5የክፉዎችን ማኅበር ተጸየፍሁ፤

ከዐመፀኞችም ጋር አልቀመጥም።

6እጆቼን በየዋህነት እታጠባለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መሠዊያህንም እዞራለሁ፤

7የምስጋናን ድምፅ አሰማ ዘንድ፣

ታምራትህንም አወራ ዘንድ ነው።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ የምትኖርበትን ቤት፣

የክብርህን ማደሪያ ቦታ ወደድሁ።

9ነፍሴን ከኀጢአተኞች ጋር፣

ሕይወቴንም ከደም አፍሳሾች ጋር አታስወግዳት።

10በእነርሱ እጅ የተንኰል ዕቅድ አለ፤

ቀኝ እጃቸውም ጕቦን ያጋብሳል።

11እኔ ግን በተአማኒ ሕይወት እጓዛለሁ፤

አድነኝ፤ ምሕረትንም አድርግልኝ።

12እግሮቼ በደልዳላ ስፍራ ቆመዋል፤

በታላቅ ጉባኤ መካከልም እግዚአብሔርን እባርከዋለሁ።