أيوب 25 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

أيوب 25:1-6

بلدد

1فَقَالَ بِلْدَدُ الشُّوحِيُّ: 2«لِلهِ السُّلْطَانُ وَالْهَيْبَةُ، يَصْنَعُ السَّلامَ فِي أَعَالِيهِ. 3هَلْ مِنْ إِحْصَاءٍ لأَجْنَادِهِ، وَعَلَى مَنْ لَا يُشْرِقُ نُورُهُ؟ 4فَكَيْفَ يَتَبَرَّرُ الإِنْسَانُ عِنْدَ اللهِ، وَكَيْفَ يَزْكُو مَوْلُودُ الْمَرْأَةِ؟ 5فَإِنْ كَانَ الْقَمَرُ لَا يُضِيءُ، وَالْكَوَاكِبُ غَيْرَ نَقِيَّةٍ فِي عَيْنَيْهِ، 6فَكَمْ بِالْحَرِيِّ الإِنْسَانُ الرِّمَّةُ وَابْنُ آدَمَ الدُّودُ؟»

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 25:1-6

በልዳዶስ

1ሹሐዊውም በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“ገዥነትና ግርማ የእግዚአብሔር ናቸው፤

በሰማይም ከፍታ ሥርዐትን ያደርጋል።

3ሰራዊቱ ሊቈጠር ይችላልን?

ብርሃኑስ የማይወጣው በማን ላይ ነው?

4ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ይሆን ዘንድ፣

ከሴትስ የተወለደ ንጹሕ ይሆን ዘንድ ይችላልን?

5በፊቱ ጨረቃ እንኳ ብሩህ ካልሆነች፣

ከዋክብትም ንጹሓን ካልሆኑ፣

6ይልቁን ከብል የሚቈጠር የሰው ልጅ፣

ትል የሆነውማ ሰው ምንኛ ያንስ!”