2 ዜና መዋዕል 8 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 8:1-18

ሰሎሞን ያከናወናቸው ሌሎች ሥራዎች

8፥1-18 ተጓ ምብ – 1ነገ 9፥10-28

1ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስና የራሱን ቤተ መንግሥት የሠራባቸው ሃያ ዓመት ከተፈጸመ በኋላ፣ 2ኪራም የሰጠውን ከተሞች አድሶ እስራኤላውያን እንዲሰፍሩባቸው አደረገ። 3ከዚያም ሰሎሞን ወደ ሐማት ሱባ ዘመተ፤ ያዛትም። 4በምድረ በዳውም ውስጥ ተድሞርንና ቀድሞ በሐማት ሠርቷቸው የነበሩትን የዕቃ ቤት ከተሞች ሁሉ ሠራ። 5እንዲሁም የላይኛውን ቤት ሖሮንና የታችኛውን ቤትሖሮን የተመሸጉ ከተሞች አድርጎ ከቅጥሮቻቸው፣ ከበሮቻቸውና ከመዝጊያዎቻቸው ጋር ሠራ። 6ደግሞም ባዕላትንና የዕቃ ቤት ከተሞቹን ሁሉ፣ ሠረገሎችና8፥6 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይችላል። ፈረሶች የሚኖሩባቸውን ከተሞች ሁሉ፣ በአጠቃላይ በኢየሩሳሌም፣ በሊባኖስና በግዛቱ ሁሉ ለመሥራት የፈለጋቸውን ነገሮች ሁሉ ሠራ።

7እስራኤላውያን ያልሆኑ ግን ከኬጢያውያን፣ ከአሞራውያን፣ ከፌርዜያውያን፣ ከኤዊያውያንና ከኢያቡሳውያን የቀሩት ሕዝቦች ሁሉ፣ 8እስራኤላውያን ያላጠፏቸውን፣ በምድሪቱ የቀሩ ዘሮቻቸውን የጕልበት ሥራ ይሠሩ ዘንድ ሰሎሞን መለመላቸው፤ እስከ ዛሬም ይሠራሉ።8፥8 ወይም ከሌቦ ሐማት ተብሎ መተርጐም ይችላል። 9ይሁን እንጂ ሰሎሞን ማንም እስራኤላዊ ባሪያ ሆኖ በግዳጅ ሥራውን እንዲሠራ አላደረገም፤ እነርሱ ተዋጊዎች፣ የሻምበል አዛዦች፣ የሠረገሎችና የሠረገላ ነጂዎች አዛዦች ነበሩና። 10ከእነዚህም ሁለት መቶ አምሳዎቹ የንጉሥ ሰሎሞን ሹማምት ሰዎቹን የሚቈጣጠሩ ነበሩ።

11ሰሎሞንም፣ “የእግዚአብሔር ታቦት የገባበት ቦታ ሁሉ ቅዱስ ስለሆነ፣ ሚስቴ በእስራኤል ንጉሥ በዳዊት ቤተ መንግሥት መኖር አይገባትም” በማለት የፈርዖንን ልጅ ከዳዊት ከተማ እርሱ ወደ ሠራላት ቤተ መንግሥት አመጣት።

12ሰሎሞንም በቤተ መቅደሱ መመላለሻ ፊት ለፊት ባሠራው የእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ የሚቃጠል መሥዋዕት ለእግዚአብሔር አቀረበ። 13ሙሴ ስለ መሥዋዕት አቀራረብ ባዘዘው መሠረት በእያንዳንዱ የበዓል ቀን ይኸውም በየሰንበቱ፣ በየወሩ መባቻና በሦስቱ የዓመት በዓላት ማለትም በቂጣ በዓል፣ በመከር በዓልና በዳስ በዓል ጊዜ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር አቀረበ። 14የአባቱን የዳዊትን ሥርዐት በመከተልም፣ ካህናቱን በየአገልግሎት ክፍላቸው ሌዋውያኑንም ምስጋናውን እንዲመሩና በየዕለቱ ሥራቸው ካህናቱን እንዲረዱ መደባቸው። ደግሞም የእግዚአብሔር ሰው ዳዊት ባዘዘው መሠረት፣ የቤተ መቅደሱን በር ጠባቂዎች በልዩ ልዩ በሮች ጥበቃ ላይ በየክፍላቸው መደባቸው። 15እነርሱም ንጉሡ ግምጃ ቤቱን ጨምሮ ስለ ማናቸውም ነገር ለካህናቱና ለሌዋውያኑ የሰጠውን ትእዛዝ አልተላለፉም ነበር።

16የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሠረት ከተጣለበት ዕለት አንሥቶ እስከ ፍጻሜው ድረስ ያለው የሰሎሞን ሥራ ሁሉ ተከናወነለት፤ በዚሁ ሁኔታም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሥራ ከፍጻሜ ደረሰ።

17ከዚያም ሰሎሞን የኤዶም የባሕር ጠረፍ ወደ ሆኑት ወደ ዔጽዮንጋብርና ወደ ኤሎት ሄደ። 18ኪራምም ባሕሩን በሚያውቁት በራሱ መኰንኖች የሚታዘዙ መርከቦችን ላከለት፤ እነዚህም ከሰሎሞን ሰዎች ጋር በመሆን ወደ ኦፊር ተጓዙ፤ ከዚያም አራት መቶ አምሳ መክሊት8፥18 ዐሥራ ስድስት ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ወርቅ አምጥተው ለንጉሥ ሰሎሞን ሰጡት።

New International Version – UK

2 Chronicles 8:1-18

Solomon’s other activities

1At the end of twenty years, during which Solomon built the temple of the Lord and his own palace, 2Solomon rebuilt the villages that Hiram8:2 Hebrew Huram, a variant of Hiram; also in verse 18 had given him, and settled Israelites in them. 3Solomon then went to Hamath Zobah and captured it. 4He also built up Tadmor in the desert and all the store cities he had built in Hamath. 5He rebuilt Upper Beth Horon and Lower Beth Horon as fortified cities, with walls and with gates and bars, 6as well as Baalath and all his store cities, and all the cities for his chariots and for his horses8:6 Or charioteers – whatever he desired to build in Jerusalem, in Lebanon and throughout all the territory that he ruled.

7There were still people left from the Hittites, Amorites, Perizzites, Hivites and Jebusites (these people were not Israelites). 8Solomon conscripted the descendants of all these people remaining in the land – whom the Israelites had not destroyed – to serve as slave labour, as it is to this day. 9But Solomon did not make slaves of the Israelites for his work; they were his fighting men, commanders of his captains, and commanders of his chariots and charioteers. 10They were also King Solomon’s chief officials – two hundred and fifty officials supervising the men.

11Solomon brought Pharaoh’s daughter up from the City of David to the palace he had built for her, for he said, ‘My wife must not live in the palace of David king of Israel, because the places the ark of the Lord has entered are holy.’

12On the altar of the Lord that he had built in front of the portico, Solomon sacrificed burnt offerings to the Lord, 13according to the daily requirement for offerings commanded by Moses for the Sabbaths, the New Moons and the three annual festivals – the Festival of Unleavened Bread, the Festival of Weeks and the Festival of Tabernacles. 14In keeping with the ordinance of his father David, he appointed the divisions of the priests for their duties and the Levites to lead the praise and to assist the priests according to each day’s requirement. He also appointed the gatekeepers by divisions for the various gates, because this was what David the man of God had ordered. 15They did not deviate from the king’s commands to the priests or to the Levites in any matter, including that of the treasuries.

16All Solomon’s work was carried out, from the day the foundation of the temple of the Lord was laid until its completion. So the temple of the Lord was finished.

17Then Solomon went to Ezion Geber and Elath on the coast of Edom. 18And Hiram sent him ships commanded by his own men, sailors who knew the sea. These, with Solomon’s men, sailed to Ophir and brought back four hundred and fifty talents8:18 That is, about 15 metric tons of gold, which they delivered to King Solomon.