2 ዜና መዋዕል 32 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 32:1-33

ሰናክሬም በኢየሩሳሌም ላይ ዛተ

32፥9-19 ተጓ ምብ – 2ነገ 18፥17-35ኢሳ 36፥2-20

32፥20-21 ተጓ ምብ – 2ነገ 19፥35ኢሳ 37፥36-38

1ሕዝቅያስ እንዲህ ባለ ታማኝነት ነገሮችን ሁሉ ካከናወነ በኋላ፣ የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም መጥቶ ይሁዳን ወረረ። ድል አድርጎ የራሱ ሊያደርጋቸው በማሰብም የተመሸጉትን ከተሞች ከበበ።

2ሕዝቅያስም ሰናክሬም መምጣቱንና ኢየሩሳሌምንም ለመውጋት ማሰቡን ባወቀ ጊዜ፣ 3ከከተማዪቱ ውጭ ያሉት የውሃ ምንጮች እንዲዘጉ ከሹማምቱና ከጦር አለቆቹ ጋር ተማከረ፤ እነርሱም ረዱት። 4ብዙ ሰዎችም ተሰብስበው “የአሦር ነገሥታት32፥4 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል የሰብዓ ሊቃናትና የሱርስቱ ትርጕም ግን፣ ንጉሥ ይላል። መጥተው ስለ ምን ብዙ ውሃ ያገኛሉ?” በማለት ምንጮቹን ሁሉና በምድር ውስጥ ለውስጥ ይተላለፍ የነበረውን ውሃ ዘጉ። 5ከዚህ በኋላም ንጉሡ ጠንክሮ በመሥራት፣ ከቅጥሩ የፈራረሱትን ሁሉ ጠገነ፤ በላዩም ማማ ሠራበት፤ በውጭ በኩልም ሌላ ቅጥር በመገንባት የዳዊትን ከተማ ድጋፍ እርከን አጠናከረ፤ እንደዚሁም ብዙ የጦር መሣሪያዎችንና ጋሻዎችን ሠራ።

6የጦር መኮንኖችንም በሕዝቡ ላይ ሾሞ በከተማዪቱ በር አደባባይ ላይ በፊቱ ከሰበሰበ በኋላ፣ እንዲህ ሲል አበረታታቸው፤ 7“በርቱ፤ ጠንክሩ፤ ከእኛ ጋር ያለው ከእርሱ ጋር ካለው ስለሚበልጥ፣ የአሦርን ንጉሥና አብሮት ያለውን ብዙ ሰራዊት አትፍሩ፤ አትደንግጡም። 8ከእነርሱ ጋር ያለው የሥጋ ክንድ ሲሆን፣ ከእኛ ጋር ያለው ግን የሚረዳንና ጠላታችንን የሚዋጋልን አምላካችን እግዚአብሔር ነው።” ሕዝቡም የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስ በተናገረው ቃል ተበረታታ።

9ከዚህ በኋላ ሰናክሬም ከሰራዊቱ ሁሉ ጋር ለኪሶን ከብቦ ሳለ፣ የሚከተለውን መልእክት በጦር መኰንኖቹ አማካይነት፣ ለሕዝቅያስና ከእርሱ ጋር በኢየሩሳሌም ለነበሩት ለይሁዳ ሕዝብ ላከ፤

10“የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም የሚለው ይህ ነው፤ በተከበበችው በኢየሩሳሌም እስከዚህ የቈያችሁት በማን ተማምናችሁ ነው? 11ሕዝቅያስ፣ ‘አምላካችን እግዚአብሔር ከአሦር ንጉሥ እጅ ያድነናል’ ማለቱስ በራብና በጥማት እንድትሞቱ ሊያስታችሁ አይደለምን? 12ለይሁዳና ለኢየሩሳሌም፣ ‘በአንድ መሠዊያ ፊት ስገዱ፤ በላዩም መሥዋዕት አቃጥሉ’ በማለት የራሱን አምላክ የኰረብታ መስገጃ ስፍራዎችንና መሠዊያዎችን ያስወገደስ ሕዝቅያስ አይደለምን?

13“እኔና አባቶቼ በሌሎች አገሮች ሕዝቦች ሁሉ ላይ ያደረግነውን አታውቁምን? ታዲያ የእነዚያ መንግሥታት አማልክት ምድራቸውን ከእጄ ለማዳን ችለዋልን? 14አባቶቼ ካጠፏቸው ከእነዚህ የመንግሥታት አማልክት ሁሉ፣ ሕዝቡን ከእጄ ሊያድን የቻለ አምላክ የትኛው ነው? ታዲያ አምላካችሁ እንዴት ከእጄ ሊያድናችሁ ይችላል? 15አሁንም ሕዝቅያስ በዚህ ዐይነት አያታልላችሁ፤ አያስታችሁም። የየትኛውም አገር ሕዝብ ወይም መንግሥት አምላክ ሕዝቡን ከእጄ ወይም ከአባቶቼ እጅ መታደግ የቻለ ስለሌለ አትመኑት። የእናንተ አምላክማ ከእጄ ያድናችሁ ዘንድ ምንኛ ያንስ!”

16የሰናክሬም ሹማምትም በእግዚአብሔር አምላክና በባሪያው በሕዝቅያስ ላይ ከዚህ የከፋ ብዙ ነገር ተናገሩ። 17ንጉሡም እንደዚሁ የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን በመሳደብ፣ “የሌሎቹ አገሮች ሕዝቦች አማልክት፣ ከእጄ እንዳልታደጉ ሁሉ፣ የሕዝቅያስም አምላክ ሕዝቡን ከእጄ ሊታደግ አይችልም” ሲል በእርሱ ላይ ደብዳቤ ጻፈ። 18ከዚያም በማስደንገጥና በማስፈራራት ከተማዪቱን ለመያዝ ሲሉ በቅጥሩ ላይ ወደ ተቀመጠው ወደ ኢየሩሳሌም ሕዝብ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው በዕብራይስጥ ቋንቋ ጮኹ፤ 19የሰው እጅ በሠራቸው በሌሎች የምድር አሕዛብ አማልክት ላይ እንደ ተናገሩት ሁሉ፣ በኢየሩሳሌም አምላክ ላይም ተናገሩ።

20ንጉሥ ሕዝቅያስና የአሞጽ ልጅ ነቢዩ ኢሳይያስም ስለዚህ ጕዳይ በጸሎት ወደ ሰማይ ጮኹ። 21እግዚአብሔርም መልአክ ልኮ በአሦር ንጉሥ ሰፈር ተዋጊዎችን፣ መሪዎችንና የጦር መኰንኖችን እንዲያጠፋቸው አደረገ። ስለዚህ ንጉሡ በውርደት ወደ ገዛ አገሩ ተመለሰ። ወደ አምላኩ ቤተ ጣዖት እንደ ገባም፣ የገዛ ወንዶች ልጆቹ በሰይፍ ገደሉት።

22እግዚአብሔርም ሕዝቅያስንና የኢየሩሳሌምን ሕዝብ ከአሦር ንጉሥ ከሰናክሬምና ከሌሎችም እጅ ሁሉ አዳናቸው፤ በዙሪያቸው ካሉትም ሁሉ ጠበቃቸው32፥22 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል የሰብዓ ሊቃናት የቩልጌት ቅጆች ግን አሳረፋቸው ይላል።23ብዙዎችም ለእግዚአብሔር መባ ይዘው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፤ ለይሁዳ ንጉሥ ለሕዝቅያስም ውድ የሆኑ ገጸ በረከቶችን አመጡለት፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮም በአሕዛብ ሁሉ ፊት ከፍ ከፍ አለ።

የሕዝቅያስ ዕብሪት፣ ያከናወናቸው ተግባሮችና ሞቱ

32፥24-33 ተጓ ምብ – 2ነገ 20፥1-21ኢሳ 37፥21-3838፥1-8

24በዚያ ጊዜ ሕዝቅያስ ታሞ ሊሞት ተቃርቦ ነበር፤ ወደ እግዚአብሔርም ጸለየ፤ እርሱም መለሰለት፤ ምልክትም ሰጠው። 25የሕዝቅያስ ልብ ግን ታበየ እንጂ ስለ ተደረገለት በጎ ነገር ተገቢ ምላሽ አልሰጠም፤ በዚህ ምክንያት የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ፣ በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ ወረደ። 26ይሁን እንጂ ሕዝቅያስና የኢየሩሳሌም ሕዝብ ስለ ልባቸው ትዕቢት ራሳቸውን አዋረዱ፤ ስለዚህ የእግዚአብሔር ቍጣ በዘመነ መንግሥቱ አልመጣባቸውም።

27ሕዝቅያስ እጅግ ብዙ ሀብትና ክብር ነበረው፤ ከዚህ የተነሣም ለብሩ፣ ለወርቁ፣ ለከበሩት ዕንቍዎቹ፣ ለቅመማ ቅመሞቹ፣ ለጋሻዎቹና ለተለያዩ ውድ ዕቃዎቹ ሁሉ ግምጃ ቤቶችን ሠራ። 28እንደዚሁም ለእህሉ፣ ለወይን ጠጁና ለዘይቱ ማከማቻ የሚሆኑ ግምጃ ቤቶች ለተለያዩ እንስሳት በረት ለበግና ለፍየል መንጋም በረት ሠራ። 29እግዚአብሔር ታላቅ ብልጽግና ስለ ሰጠው፤ ብዙ የበግና የፍየል፣ የእንስሳትም መንጋ ሰበሰበ፤ መንደሮችንም ሠራ።

30የላይኛውን የግዮንን ምንጭ መውጫ ገድቦ፣ ውሃውን በቦይ ቍልቍል ወደ ምዕራቡ የዳዊት ከተማ እንዲወርድ ያደረገም ይኸው ሕዝቅያስ ነበር፤ ሥራውም ሁሉ ተከናወነለት። 31ነገር ግን በምድሪቱ ላይ ስለ ተፈጸመው ታምራዊ ምልክት እንዲጠይቁት፣ የባቢሎን ገዦች መልእክተኞችን በላኩ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ሊፈትነውና በልቡ ያለውን ሁሉ ሊያውቅ ስለ ፈለገ ተወው።

32በሕዝቅያስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራና ቸርነቱ በአሞጽ ልጅ በነቢዩ በኢሳይያስ ራእይ፣ በይሁዳና በእስራኤል ነገሥታት መጽሐፍ ተጽፏል። 33ሕዝቅያስም እንደ አባቶቹ ሁሉ አንቀላፋ፤ የዳዊት ዘሮች መካነ መቃብር በሆነው ኰረብታም ተቀበረ። በሞተም ጊዜ ይሁዳ ሁሉና የኢየሩሳሌም ሕዝብ በሙሉ አከበሩት። ልጁ ምናሴም በእርሱ ፈንታ ነገሠ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศาวดาร 32:1-33

เซนนาเคอริบคุกคามกรุงเยรูซาเล็ม

(2พกษ.18:17-35; 19:35-37; อสย.36:2-20; 37:36-38)

1หลังจากกษัตริย์เฮเซคียาห์ได้ปฏิบัติพระราชกิจทั้งสิ้นอย่างซื่อสัตย์แล้ว กษัตริย์เซนนาเคอริบแห่งอัสซีเรียมารุกรานยูดาห์ และล้อมเมืองป้อมปราการทั้งหลาย หมายจะพิชิตเป็นเมืองขึ้น 2เมื่อเฮเซคียาห์เห็นว่าเซนนาเคอริบตั้งใจจะสู้รบกับเยรูซาเล็ม 3ก็ทรงปรึกษากับข้าราชบริพารและนายทหารเพื่อจะถมธารน้ำพุต่างๆ นอกเมืองและพวกเขาก็ช่วยพระองค์ 4ระดมกำลังคนมากมายเพื่ออุดตาน้ำและปิดกั้นลำธารที่ไหลผ่านทั่วแดน พวกเขากล่าวว่า “ทำไมจะให้บรรดากษัตริย์32:4 ฉบับ LXX. และ Syr. ว่าทำไมจะให้กษัตริย์อัสซีเรียมาพบน้ำมากมายเล่า?” 5จากนั้นพระองค์ทรงเร่งซ่อมกำแพง อุดรอยโหว่ทุกแห่ง และสร้างหอคอยบนกำแพง ก่อกำแพงรอบนอก และเสริมกำลังป้อมปราการ32:5 หรือมิลโลในเมืองดาวิด พระองค์ยังได้ทำอาวุธกับโล่จำนวนมากด้วย

6พระองค์ทรงแต่งตั้งนายทหารดูแลประชาชน และให้พวกเขามาชุมนุมกันต่อหน้าพระองค์ที่ลานประตูเมือง และตรัสให้กำลังใจพวกเขาว่า 7“จงเข้มแข็งและกล้าหาญ อย่ากลัวหรือท้อแท้เพราะกษัตริย์อัสซีเรียกับกองทัพมหึมาของเขา เพราะมีพลังอำนาจหนึ่งอยู่ฝ่ายเราซึ่งยิ่งใหญ่กว่าฝ่ายเขามากนัก 8พวกเขาเป็นเพียงมนุษย์ ส่วนเรามีพระยาห์เวห์พระเจ้าของเราซึ่งจะช่วยเราทำสงคราม” สิ่งที่เฮเซคียาห์แห่งยูดาห์ตรัส ทำให้ประชาชนมีความมั่นใจยิ่งนัก

9ต่อมากษัตริย์เซนนาเคอริบแห่งอัสซีเรียกับกองกำลังทั้งหมดซึ่งล้อมเมืองลาคีชอยู่ส่งเจ้าหน้าที่มายังกรุงเยรูซาเล็ม ให้นำสาส์นมาถึงกษัตริย์เฮเซคียาห์แห่งยูดาห์และปวงชนยูดาห์ซึ่งอยู่ที่นั่นความว่า

10“กษัตริย์เซนนาเคอริบแห่งอัสซีเรียตรัสดังนี้ว่า เจ้าทั้งหลายพึ่งพาอะไร จึงยังอยู่ในเยรูซาเล็มท่ามกลางวงล้อมของเรา? 11เฮเซคียาห์หลอกลวงพวกเจ้า จะให้พวกเจ้าตายเพราะความหิวและกระหาย โดยพูดว่า ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าของเราจะช่วยเราให้พ้นมือกษัตริย์อัสซีเรีย’ 12ก็เฮเซคียาห์คนนี้เองไม่ใช่หรือที่รื้อทำลายสถานบูชาบนที่สูงทั้งหลายกับแท่นบูชาต่างๆ และบัญชายูดาห์กับเยรูซาเล็มว่า ‘ท่านจะต้องนมัสการและเผาเครื่องบูชาโดยใช้แท่นบูชาในพระวิหารเพียงแห่งเดียวเท่านั้น’?

13“เจ้าไม่รู้หรือว่าเรากับบรรพบุรุษทำอะไรแก่ชนชาติทั้งหลายในดินแดนต่างๆ บ้าง? พระทั้งปวงของชนชาติเหล่านั้นสามารถกอบกู้ดินแดนของเขาจากมือเราได้หรือ? 14เทพเจ้าของชนชาติต่างๆ องค์ไหนบ้างที่บรรพบุรุษของเราทำลายล้างไปซึ่งสามารถช่วยคนของตนให้พ้นจากมือเราได้? ก็แล้วพระเจ้าของพวกเจ้าจะช่วยเจ้าจากมือเราได้อย่างไร? 15อย่าให้เฮเซคียาห์ล่อหลอกหรือเกลี้ยกล่อมเจ้า อย่าเชื่อเขาเลย เพราะไม่มีเทพเจ้าองค์ไหนของชนชาติหรืออาณาจักรใดๆ สามารถกอบกู้คนของตนให้พ้นจากมือของเราหรือของบรรพบุรุษของเราได้ พระเจ้าของเจ้ายิ่งไม่อาจช่วยเจ้าให้พ้นมือเรา!”

16คนของเซนนาเคอริบยังกล่าวลบหลู่ดูหมิ่นพระเจ้าพระยาห์เวห์และเฮเซคียาห์ผู้รับใช้ของพระองค์อีกต่างๆ นานา 17เซนนาเคอริบยังส่งสาส์นมาดูหมิ่นพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลว่า “เช่นเดียวกับพระของชนชาติทั้งหลายในดินแดนต่างๆ ที่ไม่อาจช่วยคนของตนจากมือเรา พระเจ้าของเฮเซคียาห์ก็ไม่อาจช่วยคนของเขาจากมือเราเช่นกัน” 18จากนั้นพวกเขาร้องบอกเป็นภาษาฮีบรูข่มขู่ประชาชนบนกำแพงเมืองเพื่อข่มขวัญให้เสียกำลังใจ จะได้ยึดเมือง 19พวกเขากล่าวถึงพระเจ้าแห่งเยรูซาเล็มเหมือนที่ได้กล่าวถึงพระต่างๆ ของชนชาติทั้งหลายในโลกซึ่งสร้างขึ้นด้วยมือมนุษย์

20กษัตริย์เฮเซคียาห์และผู้เผยพระวจนะอิสยาห์บุตรอาโมศร้องทูลอธิษฐานขึ้นสู่ฟ้าสวรรค์เกี่ยวกับเรื่องนี้ 21และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงส่งทูตองค์หนึ่งมาทำลายล้างนักรบ ผู้นำ และนายทหารทั้งปวงในค่ายของกษัตริย์อัสซีเรียจนหมดสิ้น เซนนาเคอริบจึงถอยทัพกลับดินแดนของพระองค์ไปด้วยความอัปยศอดสู และเมื่อพระองค์เสด็จเข้าไปในวิหารของเทพเจ้าของพระองค์ ก็ถูกโอรสบางองค์ปลงพระชนม์ด้วยดาบ

22เป็นอันว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงช่วยเฮเซคียาห์และชาวเยรูซาเล็มจากเงื้อมมือกษัตริย์เซนนาเคอริบแห่งอัสซีเรียและคนอื่นๆ พระองค์ทรงปกป้องดูแลพวกเขา32:22 ฉบับ LXX. และ Vulg. ว่าทรงให้พวกเขาหยุดพักทุกด้าน 23คนมากมายนำของถวายมายังกรุงเยรูซาเล็ม เพื่อถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าและนำของมีค่ามาถวายแด่กษัตริย์เฮเซคียาห์แห่งยูดาห์ นับแต่นั้นมาพระองค์ทรงเป็นที่นับถืออย่างยิ่งของชนชาติทั้งปวง

ความเย่อหยิ่ง ความสำเร็จ และการสิ้นพระชนม์ของเฮเซคียาห์

(2พกษ.20:1-21; อสย.37:21-38; 38:1-8)

24ครั้งนั้นเฮเซคียาห์ประชวรหนักใกล้สิ้นพระชนม์ พระองค์ทรงอธิษฐานต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงตอบโดยประทานหมายสำคัญ 25แต่เฮเซคียาห์มีพระทัยหยิ่งผยองและไม่ได้สำนึกในพระกรุณา องค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงพระพิโรธเฮเซคียาห์ ยูดาห์ และเยรูซาเล็ม 26แล้วเฮเซคียาห์และชาวเยรูซาเล็มกลับใจจากความเย่อหยิ่ง ฉะนั้นพระพิโรธขององค์พระผู้เป็นเจ้าจึงไม่ได้ตกแก่พวกเขาในรัชกาลเฮเซคียาห์

27เฮเซคียาห์ทรงมั่งคั่งด้วยทรัพย์สมบัติและทรงเกียรติอย่างมาก ทรงสร้างคลังต่างๆ เพื่อเก็บเงินทอง เพชรนิลจินดา เครื่องเทศ โล่ และของมีค่าทั้งปวง 28ทั้งทรงสร้างคลังเก็บข้าว เหล้าองุ่นใหม่ น้ำมัน พร้อมทั้งคอกต่างๆ สำหรับปศุสัตว์ แกะและแพะ 29พระองค์ทรงสร้างหมู่บ้านหลายแห่ง ทรงมีฝูงสัตว์และฝูงแพะแกะมากมาย เนื่องจากพระเจ้าประทานความมั่งคั่งแก่พระองค์เป็นอันมาก

30เฮเซคียาห์ทรงกั้นน้ำพุกีโฮนด้านบน และทำทางระบายน้ำมาทางแถบตะวันตกของเมืองดาวิด พระองค์ทรงประสบความสำเร็จในกิจการทุกอย่างที่ทรงทำ 31แต่เมื่อคณะทูตจากผู้ปกครองบาบิโลนมาทูลถามเกี่ยวกับหมายสำคัญที่เกิดขึ้นในดินแดน พระเจ้าทรงปล่อยเฮเซคียาห์เพื่อจะทดสอบและเพื่อจะทราบธาตุแท้ในใจของเฮเซคียาห์

32เหตุการณ์อื่นๆ ในรัชกาลเฮเซคียาห์ และพระราชกิจทั้งปวงที่พระองค์ทรงทุ่มเทเพื่อพระเจ้ามีบันทึกอยู่ในนิมิตของผู้เผยพระวจนะอิสยาห์บุตรอาโมศในจดหมายเหตุกษัตริย์แห่งยูดาห์และอิสราเอล 33เฮเซคียาห์ทรงล่วงลับไปอยู่กับบรรพบุรุษและถูกฝังไว้บนเนินเขาซึ่งเป็นอุโมงค์ฝังพระศพของวงศ์วานดาวิด ประชากรทั่วทั้งยูดาห์และเยรูซาเล็มร่วมถวายพระเกียรติเมื่อพระองค์สิ้นพระชนม์ จากนั้นมนัสเสห์โอรสของพระองค์ขึ้นครองราชย์แทน