2 ዜና መዋዕል 3 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 3:1-17

ሰሎሞን ቤተ መቅደስ ሠራ

3፥1-14 ተጓ ምብ – 1ነገ 6፥1-29

1ሰሎሞንም በኢየሩሳሌም እግዚአብሔር ለአባቱ ለዳዊት በተገለጠበት በሞሪያ ተራራ ላይ በኢያቡሳዊው በኦርና ዐውድማ ዳዊት ባዘጋጀው ቦታ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ መሥራት ጀመረ። 2በነገሠም በአራተኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር፣ በሁለተኛው ቀን ቤተ መቅደሱን መሥራት ጀመረ።

3ሰሎሞን ለመቅደሱ ሕንጻ የጣለው መሠረት በቀድሞው ስፍር ልክ ርዝመቱ ስድሳ ክንድ፣ ወርዱም ሃያ ክንድ3፥3 ርዝመቱ 27 ሜትር ወርዱ 9 ሜትር ያህል ነው። ነበር። 4በቤተ መቅደሱ መግቢያ በር ላይ ያለው በረንዳ3፥4 በዚህና በቍጥር 8፡11 እንዲሁም 13 ላይ 9 ሜትር ያህል ነው። ርዝመቱ በቤተ መቅደሱ ወርድ ልክ ሃያ ክንድ ሲሆን፣ ከፍታውም ሃያ3፥4 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን አንድ መቶ ሃያ ይላል። ክንድ ነበር። ውስጡንም በንጹሕ ወርቅ ለበጠው። 5የቤተ መቅደሱን ዋና ክፍል በጥድ ዕንጨት አልብሶ በተጣራ ወርቅ ለበጠው፤ የዘንባባና የሰንሰለት አምሳልም ቀረጸበት። 6ቤተ መቅደሱን በከበረ ድንጋይ አስጌጠው፤ የተጠቀመበትም ወርቅ የፈርዋይም ወርቅ ነበር። 7የጣራውን ተሸካሚዎች፣ መቃኖችን፣ የቤተ መቅደሱን ግድግዳና መዝጊያዎች በወርቅ ለበጠ፤ በግድግዳዎቹም ላይ የኪሩቤልን ምስል ቀረጸ።

8እንደዚሁም ቅድስተ ቅዱሳኑን ሠራ፤ ርዝመቱ ከቤተ መቅደሱ ወርድ ጋር እኩል ሲሆን፣ ርዝመቱ ሃያ ክንድ፣ ስፋቱም ሃያ ክንድ ነበር፤ ውስጡንም በስድስት መቶ3፥8 21 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። መክሊት የተጣራ ወርቅ ለበጠው። 9የወርቅ ምስማሮቹም አምሳ3፥9 0.6 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ሰቅል ይመዝኑ ነበር፤ የላይኛውንም ክፍሎች እንደዚሁ በወርቅ ለበጠ።

10በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ የሁለት ኪሩቤል ምስል አስቀርጾ በወርቅ ለበጣቸው። 11ከዳር እስከ ዳር ገጥሞ የተዘረጋው የኪሩቤል ክንፍ በጠቅላላው ሃያ ክንድ ነበር፤ የመጀመሪያው ኪሩብ አንዱ ክንፍ አምስት ክንድ3፥11 በዚህና በቍጥር 15 ላይ 2.3 ሜትር ያህል ነው። ሆኖ የቤተ መቅደሱን ግድግዳ ሲነካ፣ ሌላው አምስት ክንድ የሆነው ክንፉ ደግሞ የሁለተኛውን ኪሩብ ክንፍ ይነካ ነበር። 12እንደዚሁም የሁለተኛው ኪሩብ አንዱ ክንፍ አምስት ክንድ ሆኖ በአንጻሩ ያለውን የቤተ መቅደስ ግድግዳ ሲነካ፣ አምስት ክንድ የሆነው ሌላው ክንፉ ደግሞ የመጀመሪያውን ኪሩብ ክንፍ ይነካ ነበር። 13የተዘረጋው የእነዚህ ኪሩቤል ክንፍ ሃያ ክንድ ሲሆን፣ ፊታቸውን ወደ ቤተ መቅደሱ ዋና ክፍል አዙረው3፥13 ወይም፣ ወደ ቤተ መቅደሱ እያዩ ተብሎ መተርጐም ይቻላል በእግራቸው ቆመዋል።

14ደግሞም ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊ፣ ከደማቅ ቀይ ፈትልና ከቀጭን በፍታ መጋረጃ ሠርቶ፣ የኪሩቤልን ምስል በጥልፍ ጠለፈበት።

15በቤተ መቅደሱም ፊት ለፊት በአንድነት ቁመቱ ሠላሳ አምስት ክንድ3፥15 16 ሜትር ያህል ነው። የሆነ፣ በእያንዳንዱም ላይ አምስት ክንድ ጕልላት ያለው ሁለት ዐምድ ሠራ። 16እርስ በርሳቸው የተጠላለፉ ሰንሰለቶች ሠርቶ3፥16 ወይም፣ በቤተ መቅደሱ ውስጥ ሰንሰለት ሠርቶ ተብሎ መተርጐም ይችላል፤ በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ከዐምዶቹ ጫፍ ጋር አገናኛቸው፤ ከዚያም መቶ የሮማን ፍሬዎች ሠርቶ ከሰንሰለቶቹ ጋር አያያዛቸው።

17ዐምዶቹንም አንዱን በደቡብ፣ ሌላውን በሰሜን አድርጎ በቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት አቆማቸው፤ በደቡብ በኩል ያለውን፣ “ያኪን”፣3፥17 ምናልባት ያኪን ማለት፣ እርሱ አነጻ ማለት ሊሆን ይችላል። በሰሜን በኩል ያለውንም፣ “ቦዔዝ”3፥17 ምናልባት ቦዔዝ ማለት ብርታት በእርሱ ውስጥ ነው ማለት ሊሆን ይችላል። ብሎ ጠራቸው።

O Livro

2 Crónicas 3:1-17

Salomão constrói o templo

(1 Rs 6.1-38)

1Finalmente, começou a construção do templo em Jerusalém, no cimo do monte Moriá, onde o Senhor aparecera a David, seu pai, onde se localizava a eira de Ornã, o jebuseu. Foi David quem escolheu esse sítio. 2O início da construção teve lugar no dia 2 do segundo mês3.2 Mês de Zive. No nosso calendário, entre a lua nova do mês de abril e o mês de maio., no quarto ano do reinado de Salomão.

3-4Os alicerces tinham 30 metros de comprimento e 10 de largura. Havia um alpendre ao longo dos 10 metros da largura do edifício, na parte da frente. A sua parte interior e o teto eram cobertos de ouro puro. O telhado estava à altura de 60 metros.

5A parte principal do templo era forrada com madeira de cipreste, coberta de ouro puro, com gravações de folhas de palmeiras e cadeias. 6Havia pedras preciosas incrustadas nas paredes, para aumentar a sua beleza; o ouro era do melhor, de Parvaim. 7Todas as paredes, traves, portas e ombreiras das entradas do templo estavam cobertas de ouro com querubins gravados.

O lugar santíssimo

(1 Rs 6.19-38)

8Dentro, numa extremidade, ficava o local mais sagrado, o lugar santíssimo, com 10 metros quadrados. Esta área também era toda coberta de ouro do mais puro, pesando 21 toneladas. 9Os pregos ali usados eram igualmente de ouro e pesavam 575 gramas cada. As salas superiores estavam também forradas a ouro.

10Dentro da referida dependência, o lugar santíssimo, Salomão colocou duas esculturas de querubins revestidas de ouro. 11-13Os querubins estavam de pé ao lado um do outro, voltados para a entrada. Tinha cada um duas asas com 2,5 metros de comprimento. Uma tocava a parede da sala e a outra tocava a asa do outro querubim. As asas assim estendidas mediam 10 metros.

14À entrada desta sala colocou um véu em azul, vermelho, púrpura e linho fino, decorado também com querubins.

Os dois pilares na frente do templo

(1 Rs 7.15-22)

15Na frente do templo havia dois pilares de 17,5 metros de altura, com capitéis de 2,5 metros que os ligavam ao teto. 16Mandou fazer cadeias, como as do santuário, e colocou-as no cimo dos pilares; havia 100 romãs ligadas às cadeias. 17Os pilares, colocou-os um à direita e o outro à esquerda, na parte da frente do templo, e deu-lhes nomes: ao da direita deu o nome de Jaquim, ao da esquerda, Boaz.3.17 Em hebraico, Jaquim significa ele estabelecerá e Boaz significa nele está a força.