2 ዜና መዋዕል 3 – NASV & CST

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 3:1-17

ሰሎሞን ቤተ መቅደስ ሠራ

3፥1-14 ተጓ ምብ – 1ነገ 6፥1-29

1ሰሎሞንም በኢየሩሳሌም እግዚአብሔር ለአባቱ ለዳዊት በተገለጠበት በሞሪያ ተራራ ላይ በኢያቡሳዊው በኦርና ዐውድማ ዳዊት ባዘጋጀው ቦታ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ መሥራት ጀመረ። 2በነገሠም በአራተኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር፣ በሁለተኛው ቀን ቤተ መቅደሱን መሥራት ጀመረ።

3ሰሎሞን ለመቅደሱ ሕንጻ የጣለው መሠረት በቀድሞው ስፍር ልክ ርዝመቱ ስድሳ ክንድ፣ ወርዱም ሃያ ክንድ3፥3 ርዝመቱ 27 ሜትር ወርዱ 9 ሜትር ያህል ነው። ነበር። 4በቤተ መቅደሱ መግቢያ በር ላይ ያለው በረንዳ3፥4 በዚህና በቍጥር 8፡11 እንዲሁም 13 ላይ 9 ሜትር ያህል ነው። ርዝመቱ በቤተ መቅደሱ ወርድ ልክ ሃያ ክንድ ሲሆን፣ ከፍታውም ሃያ3፥4 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን አንድ መቶ ሃያ ይላል። ክንድ ነበር። ውስጡንም በንጹሕ ወርቅ ለበጠው። 5የቤተ መቅደሱን ዋና ክፍል በጥድ ዕንጨት አልብሶ በተጣራ ወርቅ ለበጠው፤ የዘንባባና የሰንሰለት አምሳልም ቀረጸበት። 6ቤተ መቅደሱን በከበረ ድንጋይ አስጌጠው፤ የተጠቀመበትም ወርቅ የፈርዋይም ወርቅ ነበር። 7የጣራውን ተሸካሚዎች፣ መቃኖችን፣ የቤተ መቅደሱን ግድግዳና መዝጊያዎች በወርቅ ለበጠ፤ በግድግዳዎቹም ላይ የኪሩቤልን ምስል ቀረጸ።

8እንደዚሁም ቅድስተ ቅዱሳኑን ሠራ፤ ርዝመቱ ከቤተ መቅደሱ ወርድ ጋር እኩል ሲሆን፣ ርዝመቱ ሃያ ክንድ፣ ስፋቱም ሃያ ክንድ ነበር፤ ውስጡንም በስድስት መቶ3፥8 21 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። መክሊት የተጣራ ወርቅ ለበጠው። 9የወርቅ ምስማሮቹም አምሳ3፥9 0.6 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ሰቅል ይመዝኑ ነበር፤ የላይኛውንም ክፍሎች እንደዚሁ በወርቅ ለበጠ።

10በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ የሁለት ኪሩቤል ምስል አስቀርጾ በወርቅ ለበጣቸው። 11ከዳር እስከ ዳር ገጥሞ የተዘረጋው የኪሩቤል ክንፍ በጠቅላላው ሃያ ክንድ ነበር፤ የመጀመሪያው ኪሩብ አንዱ ክንፍ አምስት ክንድ3፥11 በዚህና በቍጥር 15 ላይ 2.3 ሜትር ያህል ነው። ሆኖ የቤተ መቅደሱን ግድግዳ ሲነካ፣ ሌላው አምስት ክንድ የሆነው ክንፉ ደግሞ የሁለተኛውን ኪሩብ ክንፍ ይነካ ነበር። 12እንደዚሁም የሁለተኛው ኪሩብ አንዱ ክንፍ አምስት ክንድ ሆኖ በአንጻሩ ያለውን የቤተ መቅደስ ግድግዳ ሲነካ፣ አምስት ክንድ የሆነው ሌላው ክንፉ ደግሞ የመጀመሪያውን ኪሩብ ክንፍ ይነካ ነበር። 13የተዘረጋው የእነዚህ ኪሩቤል ክንፍ ሃያ ክንድ ሲሆን፣ ፊታቸውን ወደ ቤተ መቅደሱ ዋና ክፍል አዙረው3፥13 ወይም፣ ወደ ቤተ መቅደሱ እያዩ ተብሎ መተርጐም ይቻላል በእግራቸው ቆመዋል።

14ደግሞም ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊ፣ ከደማቅ ቀይ ፈትልና ከቀጭን በፍታ መጋረጃ ሠርቶ፣ የኪሩቤልን ምስል በጥልፍ ጠለፈበት።

15በቤተ መቅደሱም ፊት ለፊት በአንድነት ቁመቱ ሠላሳ አምስት ክንድ3፥15 16 ሜትር ያህል ነው። የሆነ፣ በእያንዳንዱም ላይ አምስት ክንድ ጕልላት ያለው ሁለት ዐምድ ሠራ። 16እርስ በርሳቸው የተጠላለፉ ሰንሰለቶች ሠርቶ3፥16 ወይም፣ በቤተ መቅደሱ ውስጥ ሰንሰለት ሠርቶ ተብሎ መተርጐም ይችላል፤ በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ከዐምዶቹ ጫፍ ጋር አገናኛቸው፤ ከዚያም መቶ የሮማን ፍሬዎች ሠርቶ ከሰንሰለቶቹ ጋር አያያዛቸው።

17ዐምዶቹንም አንዱን በደቡብ፣ ሌላውን በሰሜን አድርጎ በቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት አቆማቸው፤ በደቡብ በኩል ያለውን፣ “ያኪን”፣3፥17 ምናልባት ያኪን ማለት፣ እርሱ አነጻ ማለት ሊሆን ይችላል። በሰሜን በኩል ያለውንም፣ “ቦዔዝ”3፥17 ምናልባት ቦዔዝ ማለት ብርታት በእርሱ ውስጥ ነው ማለት ሊሆን ይችላል። ብሎ ጠራቸው።

Nueva Versión Internacional (Castilian)

2 Crónicas 3:1-17

Construcción del templo

3:1-141R 6:1-29

1Salomón comenzó a construir el templo del Señor en el monte Moria, en Jerusalén, donde el Señor se le había aparecido a su padre David. Lo construyó en el lugar que David había destinado, esto es, en la parcela de Arauna,3:1 Arauna. Lit. Ornán (variante de este nombre). el jebuseo. 2La construcción la comenzó el día dos del mes segundo del cuarto año de su reinado.

3Salomón determinó que los cimientos del templo de Dios fueran de veintisiete metros de largo por nueve metros de ancho.3:3 En los capítulos 3 al 6, las medidas de longitud se han convertido al sistema métrico, sin explicación en las notas. 4El vestíbulo de la nave medía lo mismo que el ancho del templo, es decir, también medía nueve metros de largo, y nueve metros de alto. Por dentro, Salomón lo recubrió de oro puro. 5Recubrió la nave central con paneles de madera de ciprés, sobre los cuales colocó figuras de palmeras y cadenas de oro fino. 6El templo lo adornó con piedras preciosas y con oro de Parvayin. 7En el interior del templo recubrió de oro las vigas, los umbrales, las paredes y las puertas, y en las paredes esculpió querubines.

8Salomón hizo también el Lugar Santísimo, el cual medía lo mismo que el ancho del templo, es decir, nueve metros de largo y nueve metros de ancho. Lo recubrió por dentro con veintitrés toneladas3:8 veintitrés toneladas. Lit. seiscientos talentos. de oro fino. 9Cada clavo de oro pesaba medio kilo.3:9 medio kilo. Lit. cincuenta siclos. También recubrió de oro las habitaciones superiores.

10En el Lugar Santísimo mandó tallar dos querubines, y los recubrió de oro. 11Las alas de los querubines medían nueve metros de largo. Cada una de las alas del primer querubín medía dos metros con veinticinco centímetros; una de ellas tocaba la pared interior de la habitación, y la otra rozaba el ala del segundo querubín. 12Cada una de las alas del segundo querubín también medía dos metros con veinticinco centímetros; una de ellas tocaba la pared interior de la habitación, y la otra rozaba el ala del primer querubín. 13Los querubines estaban de pie, con el rostro hacia la nave, y sus alas extendidas medían en total nueve metros.

14La cortina la hizo de púrpura, carmesí, escarlata y lino, y sobre ella mandó bordar querubines.

15En la fachada del templo levantó dos columnas de dieciséis metros de altura, y el capitel que coronaba cada columna medía más de dos metros; 16además, mandó hacer unas cadenas trenzadas3:16 trenzadas. Alt. asociadas con el santuario. y las colocó en lo alto de las columnas; hizo también cien granadas, y las intercaló entre las cadenas. 17Levantó las columnas en la fachada del templo, una en el lado sur y otra en el lado norte. A la primera la llamó Jaquín, y a la segunda, Boaz.