2 ዜና መዋዕል 25 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 25:1-28

የይሁዳ ንጉሥ አሜስያስ

25፥1-4 ተጓ ምብ – 2ነገ 14፥1-6

25፥11-12 ተጓ ምብ – 2ነገ 14፥7

25፥17-28 ተጓ ምብ – 2ነገ 14፥8-20

1አሜስያስ በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ሃያ አምስት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ሃያ ዘጠኝ ዓመት ገዛ። እናቱም ዮዓዳን የተባለች የኢየሩሳሌም ሴት ነበረች። 2እርሱም በእግዚአብሔር ፊት መልካም ነገር አደረገ፤ ነገር ግን በፍጹም ልቡ አልነበረም። 3መንግሥቱን ካጸና በኋላ፣ ንጉሥ የነበረውን አባቱን የገደሉትን ሹማምት በሞት ቀጣቸው። 4እግዚአብሔር በሙሴ መጽሐፍ በተጻፈው ሕግ “ሰው ሁሉ በገዛ ኀጢአቱ ይሙት እንጂ ወላጆች ስለ ልጆቻቸው አይገደሉ፤ ልጆችም ስለ ወላጆቻቸው አይገደሉ”25፥4 ዘዳ 24፥16 ብሎ ባዘዘው መሠረት አደረገ እንጂ ልጆቻቸውን አልገደለም።

5አሜስያስ የይሁዳን ሕዝብ በአንድነት ሰብስቦ፣ እንደየቤተ ሰቡ በሻለቆችና በመቶ አለቆች በመደልደል በመላው ይሁዳና በብንያም መደባቸው። ከዚያም ዕድሜያቸው ሃያና ከሃያ በላይ የሆናቸውን ሰብስቦ፣ ለውትድርና አገልግሎት ብቁ ሆነው ጋሻና ጦር መያዝ የሚችሉ ሦስት መቶ ሺሕ ሰዎች አገኘ። 6እንዲሁም በመቶ መክሊት25፥6 በዚህና በቍጥር 9 ላይ 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ጥሬ ብር አንድ መቶ ሺሕ ተዋጊዎች ከእስራኤል ቀጠረ።

7ነገር ግን አንድ የእግዚአብሔር ሰው ወደ እርሱ መጥቶ እንዲህ አለው፤ “ንጉሥ ሆይ፤ እግዚአብሔር ከእስራኤልም ሆነ ከማናቸውም የኤፍሬም ሕዝብ ጋር አይደለምና፣ እነዚህ የእስራኤል ወታደሮች ከአንተ ጋር አይዝመቱ። 8ሄደህ፣ ጦርነቱን በቈራጥነት ብትዋጋም እንኳ፣ የመርዳትና የመጣል ኀይል ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለሆነ፣ እግዚአብሔር በጠላቶችህ ፊት ይጥልሃል።”

9አሜስያስም የእግዚአብሔርን ሰው፣ “ታዲያ ለእነዚህ ለእስራኤል ወታደሮች የከፈልሁት መቶ መክሊት እንዴት ይሁን?” ሲል ጠየቀው የእግዚአብሔርም ሰው፣ “እግዚአብሔር ከዚህ አብልጦ ሊሰጥህ ይችላል” ሲል መለሰለት።

10ስለዚህ አሜስያስ ከኤፍሬም ወደ እርሱ የመጡትን ወታደሮች ወደየመኖሪያ ስፍራቸው አሰናበታቸው። እነርሱም በይሁዳ ላይ ክፉኛ ተበሳጭተው ነበርና በታላቅ ቍጣ ወደ መኖሪያ ስፍራቸው ተመለሱ።

11አሜስያስም ኀይሉን በሚገባ አደራጅቶ ሰራዊቱን ወደ ጨው ሸለቆ መራ፤ በዚያም ዐሥር ሺሕ የሴይር ወታደሮችን ገደለ። 12የይሁዳ ሰራዊት ሌሎች ዐሥር ሺሕ ሰዎች ማረኩ፤ ወደ አንድ ዐለት ዐናት ላይም አውጥተው ቍልቍል ለቀቋቸው፤ ሁሉም ተፈጠፈጡ።

13በዚያኑ ጊዜ አሜስያስ ያሰናበታቸውና በጦርነቱ እንዳይካፈሉ የከለከላቸው ወታደሮች፤ ከሰማርያ እስከ ቤትሖሮን ያሉትን የይሁዳ ከተሞች ወረሩ፤ ሦስት ሺሕ ሰው ገደሉ፤ እጅግ ብዙ ምርኮም ወሰዱ።

14አሜስያስም ኤዶማያውያንን ደምስሶ በተመለሰ ጊዜ፣ የሴይርን ሕዝብ አማልክት ይዞ መጣ፤ ለራሱም አማልክት አድርጎ በማቆም ሰገደላቸው፤ መሥዋዕትም አቀረበላቸው። 15የእግዚአብሔርም ቍጣ በአሜስያስ ላይ ነደደ፤ ነቢይንም ላከበት፤ ነቢዩም፣ “የገዛ ሕዝባቸውን ከእጅህ ማዳን ያልቻሉትን የአሕዛብን አማልክት ርዳታ የጠየቅኸው ለምንድን ነው?” አለው።

16እርሱም በመናገር ላይ ሳለ፣ ንጉሡ፣ “ለመሆኑ አንተን የንጉሥ አማካሪ አድርገን ሾመነሃልን? ዝም አትልም እንዴ! መሞት ትፈልጋለህ?” አለው።

ነቢዩም ዝም አለ፤ ሆኖም፣ “ይህን አድርገሃልና ምክሬንም አልሰማህምና፤ እግዚአብሔር ሊያጠፋህ እንደ ወሰነ ዐውቃለሁ” አለ።

17የይሁዳ ንጉሥ አሜስያስ አማካሪዎቹን ካማከረ በኋላ፣ የእስራኤል ንጉሥ የኢዩ የልጅ ልጅ፣ የኢዮአካዝ ልጅ ወደ ሆነው ወደ ኢዮአስ፣ “እስቲ ናና ፊት ለፊት እንጋጠም” ሲል ላከበት።

18የእስራኤል ንጉሥ ኢዮአስ ግን፣ ለይሁዳ ንጉሥ ለአሜስያስ እንዲህ ሲል መለሰለት፤ “አንድ የሊባኖስ ኵርንችት፣ ‘ሚስት እንድትሆነው ሴት ልጅህን ለልጄ ስጠው’ ሲል ወደ ሊባኖስ ዝግባ ላከበት። ከዚያም የዱር አውሬ ከሊባኖስ ወጥቶ ኵርንችቱን ረገጠው። 19ኤዶምን አሸንፌአለሁ ብለህ ራስህን በትዕቢት ክበኸዋል፤ ኰርተሃልም፤ ግን ዐርፈህ እቤትህ ተቀመጥ! በራስህና በይሁዳ ላይ ውድቀት ታመጣ ዘንድ ችግር የምትጠራው ስለ ምንድን ነው?”

20የኤዶምን አማልክት ማምለክ በመፈለጋቸው፣ እግዚአብሔር በጠላቶቻቸው እጅ አሳልፎ ሊሰጣቸው ወስኗልና፣ አሜስያስ አላዳመጣቸውም። 21ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ኢዮአስ አደጋ ጣለ። እርሱና የይሁዳ ንጉሥ አሜስያስ በይሁዳ ውስጥ ቤትሳሚስ በተባለ ስፍራ ፊት ለፊት ተጋጠሙ። 22ይሁዳ በእስራኤል ክፉኛ ተመታ፤ እያንዳንዱም ሰው ወደየመኖሪያው ሸሸ። 23የእስራኤል ንጉሥ ኢዮአስም የአካዝያስን የልጅ ልጅ የኢዮአስን ልጅ አሜስያስን ቤትሳሚስ ላይ ማርኮ ወደ ኢየሩሳሌም አመጣው፤ ከኤፍሬም በር እስከ ማእዘኑ በር ድረስ አንድ መቶ ሰማንያ ሜትር25፥23 ዕብራይስጡ፣ 80 ሜትር ያህል ነው ይላል፤ አንዳንድ ቅጆች ግን ስድስት መቶ ጫማ ይላሉ። ያህል ርዝመት ያለውንም የኢየሩሳሌምን ቅጥር አፈረሰ። 24እርሱም በዖቤድ ኤዶም ጥበቃ ሥር የነበረውንና በቤተ መቅደሱ የተገኘውን ወርቅ፣ ጥሬ ብርና ዕቃ በሙሉ፣ ከቤተ መንግሥቱም ንብረትና በመያዣ ከያዛቸው ሰዎች ጭምር ወስዶ ወደ ሰማርያ ተመለሰ።

25የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአስ ልጅ አሜስያስ፣ የእስራኤል ንጉሥ የኢዮአካዝ ልጅ ኢዮአስ ከሞተ በኋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ። 26በአሜስያስ ዘመነ መንግሥት ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው የተከናወነው ሌላው ተግባር ሁሉ በይሁዳና በእስራኤል ነገሥታት መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን? 27አሜስያስ እግዚአብሔርን መከተል ከተወ በኋላ፣ በኢየሩሳሌም ስላመፁበት ወደ ለኪሶ ሸሸ፤ ነገር ግን የሚከታተሉትን ሰዎች ከኋላው ልከው በዚያው በለኪሶ ገደሉት። 28በፈረስ ተጭኖ ከመጣ በኋላም፣ እንደ አባቶቹ ሁሉ በይሁዳ ከተማ ተቀበረ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศาวดาร 25:1-28

กษัตริย์อามาซิยาห์แห่งยูดาห์

(2พกษ.14:1-20)

1เมื่ออามาซิยาห์ขึ้นเป็นกษัตริย์ พระองค์ทรงมีพระชนมายุ 25 พรรษา และทรงครองราชย์อยู่ในกรุงเยรูซาเล็ม 29 ปี ราชมารดา คือเยโฮอัดดีน25:1 ภาษาฮีบรูว่าเยโฮอัดดานเป็นอีกรูปหนึ่งของเยโฮอัดดีนจากเยรูซาเล็ม 2อามาซิยาห์ทรงทำสิ่งที่ถูกต้องในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้าแต่ไม่ใช่ด้วยสุดใจ 3ทันทีที่อามาซิยาห์ทรงกุมอำนาจเหนือราชอาณาจักร ก็ทรงประหารชีวิตข้าราชสำนักที่ปลงพระชนม์ราชบิดาซึ่งเป็นกษัตริย์ 4อามาซิยาห์ไม่ได้ประหารลูกของพวกเขา แต่ปฏิบัติตามพระบัญชาขององค์พระผู้เป็นเจ้าซึ่งระบุไว้ในบทบัญญัติของโมเสสว่า “อย่าประหารบิดาเพราะบาปของบุตร หรือประหารบุตรเพราะบาปของบิดา แต่ละคนจะต้องตายเพราะบาปของตนเอง”25:4 ฉธบ.24:16

5อามาซิยาห์ทรงเรียกชาวยูดาห์มาชุมนุม และมอบหมายให้พวกเขาเป็นผู้บัญชาการกองพันและผู้บัญชาการกองร้อยตามวงศ์ตระกูลของตนทั่วยูดาห์และเบนยามิน จากนั้นระดมพลที่อายุยี่สิบปีขึ้นไปพบว่ามีสามแสนคนซึ่งพร้อมออกรบ สามารถใช้หอกกับโล่ได้ 6ทั้งยังทรงใช้เงินหนักประมาณ 3.4 ตัน25:6 ภาษาฮีบรูว่า 100 ตะลันต์ เช่นเดียวกับข้อ 9 จ้างนักรบจากอิสราเอลหนึ่งแสนคน

7แต่คนของพระเจ้ามาทูลอามาซิยาห์ว่า “ข้าแต่กษัตริย์ อย่าให้ทหารจากอิสราเอลร่วมทัพเลย เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ได้สถิตกับอิสราเอลหรือคนในเผ่าเอฟราอิมเลย 8ถึงแม้ท่านออกรบอย่างกล้าหาญ พระเจ้าก็จะทรงเหวี่ยงท่านออกไปต่อหน้าศัตรู เพราะพระเจ้าทรงมีอำนาจจะช่วยเหลือหรือจะโค่นล้มก็ได้”

9อามาซิยาห์ตรัสถามคนของพระเจ้าว่า “แล้วเงินหนักประมาณ 3.4 ตันที่เราจ่ายไปให้กองทัพอิสราเอลเหล่านี้เล่า?”

คนของพระเจ้าตอบว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าสามารถประทานแก่ท่านมากกว่านั้นมากนัก”

10ดังนั้นอามาซิยาห์จึงทรงปลดกองทหารที่มาจากเอฟราอิมให้กลับบ้านไป ซึ่งทำให้พวกเขาโกรธแค้นยูดาห์และกลับบ้านไปด้วยความเกรี้ยวกราด

11แล้วอามาซิยาห์ทรงรวบรวมพลและนำทัพไปยังหุบเขาเกลือ สังหารชาวเสอีร์หนึ่งหมื่นคน 12กองทัพยูดาห์จับเป็นชาวเสอีร์อีกหนึ่งหมื่นคน แล้วนำพวกเขาขึ้นไปบนยอดผาและโยนลงมาให้แหลกเป็นชิ้นๆ

13ส่วนกองทหารรับจ้างซึ่งถูกส่งกลับบ้านโดยไม่ได้ร่วมรบก็บุกปล้นเมืองต่างๆ ของยูดาห์ จากสะมาเรียถึงเบธโฮโรน พวกเขาฆ่าผู้คนสามพันคน และริบเอาข้าวของไปเป็นอันมาก

14เมื่ออามาซิยาห์เสด็จกลับมาจากการฆ่าฟันคนเอโดม พระองค์ทรงนำเทวรูปต่างๆ ของชาวเสอีร์มาสถาปนาขึ้นเป็นเทพเจ้าของพระองค์ ทรงหมอบกราบและเผาเครื่องบูชาถวายแก่เทวรูปเหล่านั้น 15องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระพิโรธอามาซิยาห์ยิ่งนัก จึงทรงใช้ผู้เผยพระวจนะมาถามว่า “เหตุใดเจ้าจึงไปหาพระต่างๆ ของชนชาตินี้ ซึ่งไม่อาจแม้แต่ช่วยคนของตัวให้พ้นมือเจ้าได้?”

16ขณะที่ผู้เผยพระวจนะกำลังพูดอยู่ กษัตริย์ตรัสโต้ตอบว่า “เราได้แต่งตั้งเจ้าให้เป็นที่ปรึกษาของกษัตริย์ตั้งแต่เมื่อใด? เงียบนะ! จะให้เราฆ่าเจ้าทำไม?”

ผู้เผยพระวจนะจึงหยุดแต่กล่าวว่า “ข้าพเจ้าทราบว่าพระเจ้าตกลงพระทัยจะทำลายท่านแล้วเพราะท่านทำอย่างนี้ และไม่รับฟังคำแนะนำของข้าพเจ้า”

17ต่อมากษัตริย์อามาซิยาห์แห่งยูดาห์ทรงหารือกับคณะที่ปรึกษา แล้วส่งคำท้าทายไปยังกษัตริย์เยโฮอาช25:17 ภาษาฮีบรูว่าโยอาชเป็นอีกรูปหนึ่งของเยโฮอาชเช่นเดียวกับข้อ 18,21,23 และ 25แห่งอิสราเอล โอรสของเยโฮอาหาสโอรสของเยฮูว่า “จงออกมาเผชิญหน้ากัน”

18แต่กษัตริย์เยโฮอาชแห่งอิสราเอลทรงตอบกษัตริย์อามาซิยาห์แห่งยูดาห์ว่า “ต้นหนามในเลบานอนส่งข่าวมาถึงต้นสนซีดาร์ในเลบานอนว่า ‘ยกลูกสาวของท่านให้แต่งงานกับลูกชายของข้าพเจ้าเถิด’ แล้วมีสัตว์ป่าตัวหนึ่งในเลบานอนมาเหยียบย่ำต้นหนามนั้นป่นปี้ 19ท่านพิชิตเอโดมได้ก็เลยผยอง แต่จงอยู่กับบ้าน! จะแกว่งเท้าหาเสี้ยนไปทำไม ทำไมหาเรื่องให้ตัวท่านเองและยูดาห์ย่อยยับไปด้วย?”

20แต่อามาซิยาห์ไม่ทรงฟัง เพราะพระเจ้าทรงเตรียมมอบพวกเขาให้กับเยโฮอาช เนื่องจากพวกเขาหันไปหาพระต่างๆ ของเอโดม 21กษัตริย์เยโฮอาชแห่งอิสราเอลจึงทรงบุกเข้าโจมตี และมาเผชิญหน้ากับกษัตริย์อามาซิยาห์แห่งยูดาห์ที่เบธเชเมชในยูดาห์ 22แล้วยูดาห์ก็ถูกอิสราเอลรุกไล่ ทุกคนพ่ายหนีกลับบ้านของตน 23กษัตริย์เยโฮอาชแห่งอิสราเอลทรงจับกุมกษัตริย์อามาซิยาห์แห่งยูดาห์ ซึ่งเป็นโอรสของโยอาชผู้เป็นโอรสอาหัสยาห์25:23 ภาษาฮีบรูว่าเยโฮอาหาสเป็นอีกรูปหนึ่งของอาหัสยาห์ได้ที่เบธเชเมช แล้วนำตัวมายังกรุงเยรูซาเล็ม เยโฮอาชทรงทลายกำแพงเมืองเยรูซาเล็มตั้งแต่ประตูเอฟราอิมจนถึงประตูมุมเป็นระยะทาง 400 ศอก25:23 คือ ประมาณ 180 เมตร 24พระองค์ทรงริบเงินและทองทั้งหมด ตลอดจนเครื่องใช้ไม้สอยทุกชิ้นที่พบในพระวิหารของพระเจ้าซึ่งโอเบดเอโดมดูแลรับผิดชอบอยู่ พร้อมทั้งริบทรัพย์สมบัติจากพระราชวังและจากตัวประกัน แล้วเสด็จกลับสะมาเรีย

25อามาซิยาห์โอรสกษัตริย์โยอาชแห่งยูดาห์ทรงมีพระชนม์อยู่ต่อไปอีกสิบห้าปีหลังจากเยโฮอาชโอรสกษัตริย์เยโฮอาหาสแห่งอิสราเอลสิ้นพระชนม์ 26เหตุการณ์อื่นๆ ในรัชกาลอามาซิยาห์ตั้งแต่ต้นจนจบมีบันทึกไว้ในจดหมายเหตุกษัตริย์แห่งยูดาห์และอิสราเอลไม่ใช่หรือ? 27ตั้งแต่อามาซิยาห์หันเหจากการติดตามองค์พระผู้เป็นเจ้า มีผู้คิดร้ายหมายปลงพระชนม์อามาซิยาห์ในกรุงเยรูซาเล็ม พระองค์จึงเสด็จหนีไปยังเมืองลาคีช แต่ผู้คิดร้ายเหล่านั้นส่งคนตามไปปลงพระชนม์พระองค์ที่นั่น 28พระศพถูกนำขึ้นหลังม้ากลับมา และถูกฝังไว้กับบรรพบุรุษของพระองค์ในนครแห่งยูดาห์