2 ዜና መዋዕል 23 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 23:1-21

1በሰባተኛው ዓመት ዮዳሄ በረታ፤ የመቶ አለቆች ከሆኑት ከይሮሐም ልጅ ከዓዛርያስ፣ ከይሆሐናን ልጅ ከይስማኤል፣ ከዖቤድ ልጅ ከዓዛርያስ፣ ከዓዳያ ልጅ ከማዕሤያ፣ ከዝክሪ ልጅ ከኤሊሳፋጥ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ። 2እነርሱም ወደ መላው ይሁዳ ሄደው፣ ሌዋውያንንና የእስራኤል ቤት አለቆችን ከየከተማው ሁሉ ሰበሰቡ። ወደ ኢየሩሳሌም በመጡ ጊዜም፣ 3ጉባኤው ሁሉ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ከንጉሡ ጋር ቃል ኪዳን አደረጉ።

ዮዳሄም እንዲህ አላቸው፤ “እግዚአብሔር ለዳዊት ዘር በሰጠው ተስፋ መሠረት እነሆ፤ የንጉሡ ልጅ ይነግሣል። 4እንግዲህ እናንተ የምታደርጉት ይህ ነው፤ በሰንበት ዕለት ተረኛ ከሆናችሁት ከእናንተ ከካህናቱና ከሌዋውያኑ አንድ ሦስተኛው በሮቹን ጠብቁ፤ 5አንድ ሦስተኛው ቤተ መንግሥቱን፣ አንድ ሦስተኛው ‘የመሠረት ቅጽር በር’ የተባለውን ጠብቁ፤ የቀሩት ሰዎች በሙሉ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አደባባይ ይሁኑ። 6ተረኛ ከሆኑት ካህናትና ሌዋውያን በቀር ማንም ሰው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አይግባ፤ እነርሱ የተቀደሱ ስለሆኑ ይግቡ፤ የቀሩት ሰዎች በሙሉ ግን፣ ወደ ቤተ መቅደሱ እንዳይገቡ እግዚአብሔር ያዘዘውን ይጠብቁ23፥6 ወይም አይግባ የሚለውን የእግዚአብሔር ትእዛዝ ይጠብቁ7ሌዋውያኑም የጦር መሣሪያቸውን በእጃቸው ይዘው በንጉሡ ዙሪያ ይቁሙ፤ ወደ ቤተ መቅደሱ የሚገባ ማንኛውም ሰው ይገደል፤ ንጉሡ በሚሄድበትም ቦታ ሁሉ አብረውት ይሁኑ።”

8ሌዋውያኑና ይሁዳ ሁሉ ልክ ካህኑ ዮዳሄ እንዳዘዘው አደረጉ፤ ካህኑ ዮዳሄ ከጥበቃ ክፍሎች የትኛውንም አላሰናበተም ነበርና፣ እያንዳንዱ በሰንበት ቀን በሥራ ላይ የሚሰማሩትንና ከሥራ የሚወጡትን የራሱን ሰዎች ወሰደ፤ 9ከዚያም በቤተ መቅደሱ የነበሩትን የንጉሥ ዳዊት ጦሮች፣ ታላላቅና ታናናሽ ጋሻዎች ለመቶ አለቆቹ ሰጣቸው። 10ሰዎቹም ሁሉ እያንዳንዳቸው መሣሪያቸውን በእጃቸው እንደ ያዙ ከቤተ መቅደሱ ደቡብ አንሥቶ እስከ ሰሜን ድረስ በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ አጠገብ በንጉሡ ዙሪያ እንዲቆሙ አደረገ።

11ዮዳሄና ወንዶች ልጆቹ የንጉሡን ልጅ አምጥተው ዘውድ ጫኑለት፤ የኪዳኑንም መጽሐፍ ሰጥተውት አነገሡት፤ ቀብተውትም፣ “ንጉሡ ለዘላለም ይኑር!” እያሉ ጮኹ።

12ጎቶልያም የሚሯሯጠውንና ደስታውን ለንጉሡ የሚገልጠውን ሕዝብ ሁካታ ስትሰማ፣ ሕዝቡ ወዳለበት ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሄደች። 13ንጉሡ በመግቢያው ላይ ባለው በዐምዱ አጠገብ ቆሞ አየች፣ የጦር መኮንኖችና መለከት ነፊዎችም በንጉሡ አጠገቡ ነበሩ፤ የምድሪቱ ሕዝብ ሁሉ ይደሰቱ፣ መለከትም ይነፉ ነበር፤ መዘምራንም በዜማ ዕቃ ታጅበው የበዓሉን ዝማሬ ይመሩ ነበር፤ ጎቶልያም ልብሷን ቀድዳ፣ “ይህ ዐመፅ ነው! ይህ ዐመፅ ነው!” ብላ ጮኸች።

14ካህኑ ዮዳሄም የወታደር አዛዥ ወደ ሆኑት ወደ መቶ አለቆቹ፣ “በሰልፉ መካከል አውጥታችሁ አምጧት23፥14 ወይም ከቅጥሩ ውስጥ አውጥታችሁ አምጧት፤ የሚከተላት ካለም በሰይፍ ግደሉት” ሲል ላከባቸው። ካህኑም፣ “በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አትግደሏት” ብሎ ነበርና። 15እርሷም በቤተ መንግሥቱ ግቢ የፈረስ መግቢያ በር ወደ ተባለው ቦታ እንደ ደረሰች ያዟት፤ በዚያም ገደሏት።

16ዮዳሄም ራሱ፣ ሕዝቡና ንጉሡ የእግዚአብሔር ሕዝብ እንደሚሆኑ ቃል ኪዳን ገባ23፥16 ወይም በእግዚአብሔር በሕዝቡና በንጉሡ መካከል የተደረገው ቃል ኪዳን (2ነገ 11፥17)17ከዚህ በኋላ ሕዝቡ በሙሉ ሄዶ የበኣልን ቤተ ጣዖት አፈረሰው፤ መሠዊያዎቹንና ጣዖታቱን አደቀቀ፤ የበኣልን ካህን ማታንንም በመሠዊያዎቹ ፊት ለፊት ገደሉት። 18ዮዳሄ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈውና ዳዊትም እንዳዘዘው፣ በደስታና በመዝሙር የሚቃጠለውን የእግዚአብሔርን መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ዳዊት ለመደባቸው ካህናትና ሌዋውያን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ኀላፊነት ሰጣቸው። 19እንዲሁም በማንኛውም ነገር የረከሰ ሰው እንዳይገባ፣ በቤተ መቅደሱ ቅጥር በሮች ላይ ጠባቆች አቆመ። 20የመቶ አለቆቹን፣ መኳንንቱን፣ የሕዝቡን ገዦችና የአገሩን ሕዝብ ሁሉ ይዞ ንጉሡን ከላይ ከቤተ መቅደሱ ወደ ታች አመጣው። በላይኛውም መግቢያ በኩል ወደ ቤተ መንግሥቱ ገብተው ንጉሡን በመንግሥቱ ዙፋን ላይ አስቀመጡት። 21መላውም የአገሩ ሕዝብ ተደሰተ፤ ጎቶልያ ስለ ተገደለችም ከተማዪቱ ሰላም አግኝታ ነበር።

Swedish Contemporary Bible

2 Krönikeboken 23:1-21

Ataljas död

(2 Kung 11:4-20)

1Under det sjunde året fattade Jojada mod och slöt sig samman med officerarna Asarja, Jerochams son, Ismael, Jochanans son, Asarja, Oveds son, Maaseja, Adajas son, och Elishafat, Sikris son. 2De reste ut över hela Juda och samlade leviterna från alla Judas städer och alla Israels familjeöverhuvuden. När de kom till Jerusalem, 3slöt hela församlingen ett förbund i Guds hus med kungen. Jojada talade till dem:

”Kungens son ska nu bli kung, såsom Herren har sagt om Davids ättlingar. 4Så här ska ni göra: En tredjedel av er, präster och leviter, som går i tjänst på sabbaten, ska bevaka alla dörrar, 5en tredjedel ska vara vid palatset, och en tredjedel ska finnas vid Jesodporten. Folket ska stanna på förgårdarna till Herrens hus. 6Ingen får gå in i Herrens hus, förutom präster och leviter i tjänst. De får gå in eftersom de är helgade. Men folket ska iaktta Herrens förordning. 7Leviterna ska ställa sig runt omkring kungen, var och en med vapen i hand. Om någon försöker gå in i templet måste han dödas. Och håll er nära kungen vart han än går.”

8Leviterna och hela Juda gjorde som de blivit beordrade av prästen Jojada. Var och en tog sina män, både dem som gick på och dem som gick av sitt pass på sabbaten, för prästen Jojada lät ingen avdelning vara fri. 9Sedan gav prästen Jojada officerarna spjut, sköldar och koger som hade tillhört kung David och fanns i Guds hus. 10Han ställde upp allt folket, var och en med vapen i sin hand, runt omkring kungen, från templets södra sida till dess norra, framför altaret och tempelhuset. 11Sedan förde de ut kungasonen, satte en krona på hans huvud, gav honom förbundsförordningarna23:11 Eller: kungainsignierna och utropade honom till kung. Jojada och hans söner smorde honom, och de ropade: ”Länge leve kungen!”

12När Atalja hörde jublet från folket som skyndat till för att hylla kungen, gick hon till dem som var i Herrens hus. 13Där fick hon se kungen stå vid sin pelare vid ingången, med officerarna och trumpetarna vid sina sidor. Allt folket jublade och lät trumpeterna ljuda. Sångarna med sina instrument ledde hyllningssången. Då rev Atalja sönder sina kläder och ropade: ”Förräderi! Förräderi!”

14Prästen Jojada skickade ut officerarna som hade befälet över trupperna och befallde dem: ”För ut henne bortom gången och om någon följer henne, ska han dödas med svärd.” Prästen hade nämligen sagt: ”Ni får inte döda henne i Herrens hus.”

15Då grep de henne och ledde ut henne till Hästporten i kungapalatset, där de dödade henne.

16Jojada slöt sedan ett förbund mellan sig, kungen och folket att de skulle vara Herrens folk. 17Hela folket begav sig sedan till Baals tempel, rev ner det och bröt sönder altarna och gudabilderna och dödade Mattan, Baals präst, framför altarna. 18Jojada placerade sedan vakter vid Herrens hus, som leddes av de levitiska prästerna, som David hade delat upp i avdelningar i templet, för att bära fram brännoffer åt Herren, som det var föreskrivet i Moses lag, med glädje och sång, allt enligt Davids befallningar. 19Han ställde också vakterna vid portarna till Herrens hus, för att ingen som på något sätt var oren skulle kunna komma in.

20Sedan tog han med sig officerarna, de förnämsta, de styrande bland folket och allt folket i landet och förde ut kungen från Herrens hus till palatset via Övre porten och satte honom på kungatronen. 21Allt folket i landet gladde sig, och det blev lugnt i staden, när Atalja dödats med svärd.