2 ነገሥት 25 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 25:1-30

1በይሁዳ ንጉሥ በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት በዘጠነኛው ዓመት በዐሥረኛው ወር፣ ከወሩም በዐሥረኛው ቀን የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር መላ ሰራዊቱን ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ዘመተ፤ ከከተማዪቱ ቅጥር ውጭ ሰፈረ፤ ዙሪያውንም በሙሉ በዕርድ ከበባት። 2ከተማዪቱም እስከ ሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት ዐሥራ አንደኛ ዓመት ድረስ እንዲሁ እንደ ተከበበች ቈየች።

3በአራተኛው25፥3 ኤር 52፥6 ይመ ወር በዘጠነኛው ቀን በከተማዪቱ ውስጥ የተከሠተው ራብ ጸንቶ ስለ ነበር ሕዝቡ የሚቀምሰው ዐጣ። 4ምንም እንኳ ባቢሎናውያን25፥4 በዚህና በቍጥር 13፡25 እንዲሁም 26 ላይ፣ ከለዳውያን ከተማዪቱን እንደ ከበቧት ቢሆንም የከተማዪቱ ቅጥር ተጣሰ፤ ሰራዊቱም ሁሉ በንጉሡ አትክልት አጠገብ ባሉት በሁለቱ ቅጥሮች መካከል በሚገኘው በር ዐልፎ በሌሊት ሸሸ፤ ሽሽቱም ወደ ዮርዳኖስ ሸለቆ25፥4 ወይም፣ በዓረባም ነበር። 5ይሁን እንጂ የባቢሎን25፥5 በዚህም ሆነ በቍጥር 10 እና 24 ላይ፣ ከለዳውያን ሰራዊት ንጉሡን ተከታትሎ በኢያሪኮ ሜዳ ላይ ደረሰበት። ወታደሮቹ ሁሉ ተለይተውት ተበታትነው ነበር። 6እርሱም ተያዘ፤ በዚያን ጊዜ ሪብላ ወደ ነበረው ወደ ባቢሎን ንጉሥ አመጡት፤ ፈረዱበትም። 7ሴዴቅያስ ዐይኑ እያየም የገዛ ልጆቹን ገደሉበት፤ ከዚያም ሁለት ዐይኖቹን በማውጣት በናስ ሰንሰለት አስረው ወደ ባቢሎን ወሰዱት።

8የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በነገሠ በዐሥራ ዘጠነኛው ዓመት፣ በአምስተኛው ወር ከወሩም በሰባተኛው ቀን የክብር ዘቡ ሰራዊት አዛዥና የባቢሎን ንጉሥ ከፍተኛ ባለ ሥልጣን የሆነው ናቡዘረዳን ወደ ኢየሩሳሌም መጣ። 9የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ፣ ቤተ መንግሥቱንና በኢየሩሳሌም የሚገኙትን ቤቶች ሁሉ አቃጠለ፤ እያንዳንዱንም ታላላቅ ሕንጻ ለእሳት ዳረገው። 10በክብር ዘቡ አዛዥ የተመራው መላው የባቢሎን ሰራዊትም በኢየሩሳሌም ዙሪያ የነበረውን ቅጥር አፈረሰው። 11የክብር ዘቡ አዛዥም በከተማዪቱ ቀርቶ የነበረውን፣ ከድቶም በዚያ የተገኘውን ሰው ሁሉ ወደ ባቢሎን ንጉሥ የገባውን ጭምር በምርኮ ወደ ባቢሎን ወሰደው። 12ሆኖም አዛዡ ከአገሬው ሰዎች ምንም የሌላቸውን ድኾች ወይን እንዲተክሉ፣ ዕርሻም እንዲያርሱ እዚያው ተዋቸው። 13ባቢሎናውያን የናስ ዐምዶቹን፣ በቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩትን ተንቀሳቃሽ የዕቃ ማስቀመጫዎችንና ከናስ የተሠራውን የውሃ ማጠራቀሚያ ክብ በርሜል ሰባብረው ናሱን ወደ ባቢሎን ወሰዱ። 14እንዲሁም ምንቸቶቹን፣ መጫሪያዎቹን፣ መኰስተሪያዎቹን፣ ጭልፋዎቹን፣ በአጠቃላይም ከናስ የተሠሩትን የቤተ መቅደሱን መገልገያ ዕቃዎች ሁሉ ወሰዱ። 15የክብር ዘቡ አዛዥም ከንጹሕ ወርቅና ብር የተሠሩትን ጽናዎችና የመርጫ ወጭቶችን ወሰደ።

16ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መገልገያ ብሎ ከናስ ያሠራቸው ሁለት ዐምዶች፣ የውሃ ማጠራቀሚያው ክብ በርሜልና ተንቀሳቃሽ የዕቃ ማስቀመጫዎቹ ክብደታቸው ከሚዛን በላይ ነበር። 17እያንዳንዱ ዐምድ ዐሥራ ስምንት ክንድ25፥17 8.1 ሜትር ያህል ነው። ሲሆን፣ የናስ ጕልላት ነበረው፤ የጕልላቱ ርዝመት ሦስት ክንድ25፥17 1.3 ሜትር ያህል ነው። ሆኖ፣ ዙሪያውን በሙሉ የናስ መርበብና የሮማን ፍሬዎች ቅርጽ ነበረው፤ ሌላውም ዐምድ ከነቅርጾቹ ከዚሁ ጋር ተመሳሳይ ነበር።

18የክብር ዘብ አዛዡም ሊቀ ካህኑን ሠራያን፣ በማዕረግ ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን ካህኑን ሶፎንያስንና ሦስቱን የበር ጠባቂዎች እስረኛ አድርጎ ወሰዳቸው። 19እስከዚያች ጊዜ ድረስ በከተማዪቱ ውስጥ ከቀሩትም የተዋጊዎቹን አለቃና አምስት የንጉሡን አማካሪዎች ወሰዳቸው። ደግሞም የአገሩን ሕዝብ ለውትድርና የሚመለምለውን ዋና የጦር አለቃ የነበረውን ጸሓፊውንና በከተማዪቱ ውስጥ የተገኙትን የጸሓፊውን ስድሳ ሰዎች ወሰዳቸው። 20አዛዡ ናቡዘረዳንም እነዚህን ሁሉ ይዞ ልብና ወዳለው ወደ ባቢሎን ንጉሥ አመጣቸው። 21ንጉሡም ሰዎቹን በሐማት ምድር እዚያው ልብና ውስጥ አስገደላቸው። ይሁዳም ከምድሩ በዚህ ሁኔታ ተማርኮ ሄደ።

22የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር፣ የሳፋን የልጅ ልጅ የሆነውን የአኪቃምን ልጅ ጎዶልያስን እዚያው በቀረው በይሁዳ ሕዝብ ላይ አለቃ አድርጎ ሾመው። 23መላው የሰራዊቱ ጦር አለቆችና ሰዎቻቸው የባቢሎን ንጉሥ፣ አገረ ገዥ አድርጎ ጎዶልያስን መሾሙን ሲሰሙ፣ እርሱ ወዳለበት ወደ ምጽጳ መጡ፤ እነርሱም የናታንያ ልጅ እስማኤል፣ የቃሬያም ልጅ ዮሐናን፣ የነጦፋዊው የተን ሑሜት ልጅ ሠራያ የማዕካታዊው ልጅ ያእዛንያና ሰዎቻቸው ነበሩ። 24ጎዶልያስም፣ “የባቢሎናውያንን ሹማምት አትፍሩ፤ እዚሁ አገር ኑሩ፤ የባቢሎንን ንጉሥ አገልግሉ፤ ሁሉም ነገር ይሳካላችኋል” ሲል ይህንኑ በቃለ መሐላ አረጋገጠላቸው። 25ነገር ግን በሰባተኛው ወር ንጉሣዊ ዝርያ የነበረው የኤሊሳማ የልጅ ልጅ የሆነው የናታንያ ልጅ እስማኤል ዐሥር ሰዎች ይዞ መጥቶ ጎዶልያስንና በምጽጳ አብረውት የነበሩትን የይሁዳን ሰዎችና ባቢሎናውያንን ገደለ። 26ባቢሎናውያንን ከመፍራታቸው የተነሣም ትንሽ ትልቅ ሳይባል ሕዝቡ ሁሉ ከሰራዊቱ የጦር አለቆች ጋር ወደ ግብፅ ሸሹ።

ዮአኪን ከእስራት ተፈታ

25፥27-30 ተጓ ምብ – ኤር 52፥31-34

27የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪን በተማረከ በሠላሳ ሰባተኛው ዓመት፣ በዐሥራ ሁለተኛው ወር ከወሩም በሃያ ሰባተኛው ቀን ዮርማሮዴቅ25፥27 አሜል ማርዶክ ይባላል። በባቢሎን በነገሠ በዓመቱ ዮአኪንን ከእስራቱ ፈታው። 28በርኅራኄም መንፈስ አነጋገረው፤ በባቢሎን አብረውት ከነበሩት ነገሥታት ይልቅ ከፍ ያለውን የክብር ቦታ ሰጠው። 29ዮአኪንም የእስር ቤት ልብሱን ጣለ፤ እስከ ዕድሜው ፍጻሜ ድረስ ከንጉሡ ማዕድ ዘወትር ይመገብ ጀመር፤ 30ንጉሡም ለዮአኪን እስከ ዕድሜው ፍጻሜ ድረስ የዕለት ቀለቡን ይሰጠው ነበር።

Thai New Contemporary Bible

2พงศ์กษัตริย์ 25:1-30

กรุงเยรูซาเล็มล่มสลาย

(2พศด.36:17-20; ยรม.39:1-10; 40:7-9; 41:1-3,16-18; 52:4-27)

ครั้งนั้นเศเดคียาห์ทรงกบฏต่อกษัตริย์บาบิโลน

1ฉะนั้นกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนทรงกรีธาทัพหลวงมารบกับกรุงเยรูซาเล็มในวันที่สิบเดือนที่สิบของปีที่เก้าแห่งรัชกาลกษัตริย์เศเดคียาห์ พระองค์ทรงตั้งค่ายอยู่นอกเมืองแล้วสร้างเชิงเทินล้อมเมืองไว้ 2กรุงเยรูซาเล็มถูกล้อมอยู่จนถึงปีที่สิบเอ็ดแห่งรัชกาลเศเดคียาห์ 3เมื่อถึงวันที่เก้าของเดือนที่สี่25:3 ยรม.52:6กรุงนี้ก็กันดารอาหารอย่างหนักจนไม่มีอาหารรับประทานเลย 4แล้วกำแพงเมืองก็ถูกพังลง ทั้งกองทัพก็หนีไปในเวลากลางคืน ผ่านประตูระหว่างกำแพงสองชั้นใกล้ราชอุทยาน แม้ว่าชาวบาบิโลนล้อมเมืองอยู่ พวกเขาหนีไปยังอาราบาห์25:4 หรือหุบเขาแห่งจอร์แดน 5แต่กองทัพบาบิโลน25:5 หรือเคลเดียเช่นเดียวกับข้อ 13,25 และ 26ไล่ล่ากษัตริย์ และมาทันพระองค์ในที่ราบเยรีโค ส่วนทหารทั้งปวงของเศเดคียาห์แตกหนีกันไปคนละทิศคนละทาง 6และพระองค์ทรงถูกจับกุม พระองค์ทรงถูกคุมตัวมาเข้าเฝ้ากษัตริย์บาบิโลนที่ริบลาห์และรับการตัดสินโทษ 7พวกเขาประหารบรรดาโอรสของเศเดคียาห์ต่อหน้าต่อตาพระองค์ แล้วควักพระเนตรของพระองค์ออกทั้งสองข้าง จองจำพระองค์ด้วยโซ่ตรวนทองสัมฤทธิ์ และคุมพระองค์ไปยังบาบิโลน

8ในวันที่เจ็ดเดือนที่ห้าของปีที่สิบเก้าแห่งรัชกาลกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลน เนบูซาระดานผู้บัญชาการทหารรักษาพระองค์ ผู้เป็นข้าราชการของกษัตริย์บาบิโลนมายังกรุงเยรูซาเล็ม 9เขาจุดไฟเผาพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า พระราชวัง และบ้านเรือนทุกหลังในเยรูซาเล็ม รวมทั้งอาคารสำคัญทุกแห่ง 10ผู้บัญชาการทหารรักษาพระองค์สั่งการให้กองทัพบาบิโลนทั้งหมดทลายกำแพงรอบกรุงเยรูซาเล็ม 11เนบูซาระดานผู้บัญชาการทหารรักษาพระองค์กวาดต้อนผู้คนที่ยังอยู่ในกรุงนั้น ประชากรอื่นๆ ที่เหลือ และชาวยิวที่ยอมสวามิภักดิ์ต่อกษัตริย์บาบิโลนไปเป็นเชลย 12แต่ผู้บัญชาการทหารรักษาพระองค์ได้ทิ้งประชากรที่ยากจนข้นแค้นที่สุดบางคนไว้ให้ทำสวนองุ่นและทำไร่ไถนา

13ชาวบาบิโลนทำลายเสาหานทองสัมฤทธิ์ทั้งสอง แท่นเคลื่อนที่ และขันสาครทองสัมฤทธิ์ที่พระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า และนำทองสัมฤทธิ์ทั้งหมดไปยังบาบิโลน 14พวกเขายังได้นำหม้อ ทัพพี กรรไกรตัดไส้ตะเกียง จานชาม และเครื่องใช้ทองสัมฤทธิ์ทั้งหมดที่ใช้ในพระวิหารไปด้วย 15ผู้บัญชาการทหารรักษาพระองค์ยังได้ริบกระถางไฟเผาเครื่องหอมและอ่างประพรมทั้งหมดที่ทำด้วยทองคำบริสุทธิ์หรือเงินไปด้วย

16ทองสัมฤทธิ์ที่ได้จากเสาหานทั้งสองต้น ขันสาคร และแท่นเคลื่อนที่ซึ่งโซโลมอนทรงสร้างขึ้น เพื่อพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้านั้นมีปริมาณมากเกินกว่าที่จะชั่งน้ำหนักได้ 17เสาแต่ละต้นสูง 18 ศอก25:17 คือ ประมาณ 8.1 เมตร และมีข่ายทองสัมฤทธิ์สลับกับผลทับทิมทองสัมฤทธิ์ประดับรอบหัวเสายาว 3 ศอก25:17 คือ ประมาณ 1.3 เมตร

18ผู้บัญชาการทหารรักษาพระองค์ได้จับตัวเสไรอาห์หัวหน้าปุโรหิต เศฟันยาห์รองหัวหน้าปุโรหิต และนายประตูสามคนไว้ 19เขาจับกุมผู้ที่ยังอยู่ในเมืองได้แก่ แม่ทัพ ราชมนตรีห้าคน ราชเลขาผู้เป็นหัวหน้ากองเกณฑ์พล และคนของเขาที่พบในเมืองอีกหกสิบคน 20ผู้บัญชาการเนบูซาระดานได้นำตัวคนทั้งหมดนี้ไปเข้าเฝ้ากษัตริย์บาบิโลนที่ริบลาห์ 21กษัตริย์ก็ให้ประหารคนเหล่านี้ที่ริบลาห์ในเขตฮามัท

ดังนั้นยูดาห์จึงตกเป็นเชลย ต้องถูกพรากจากดินแดนของตน

22กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนทรงแต่งตั้งเกดาลิยาห์บุตรอาหิคัมและเป็นหลานชาฟานให้ปกครองประชาชนที่เหลืออยู่ในยูดาห์ 23เมื่อบรรดาเจ้าหน้าที่ของกองทัพกับพวกได้ข่าวว่ากษัตริย์บาบิโลนทรงแต่งตั้งเกดาลิยาห์เป็นผู้ว่าการ ก็พากันมาพบเกดาลิยาห์ที่มิสปาห์ได้แก่ อิชมาเอลบุตรเนธานิยาห์ โยฮานันบุตรคาเรอาห์ เสไรอาห์บุตรทันหุเมทจากเนโทฟาห์และยาอาซันยาห์บุตรคนตระกูลมาอาคาห์กับคนของเขา 24เกดาลิยาห์ยืนยันกับพวกเขาว่า “อย่ากลัวเจ้าหน้าที่ของบาบิโลน จงตั้งรกรากในดินแดนและรับใช้กษัตริย์บาบิโลน แล้วทุกอย่างจะเป็นไปด้วยดี”

25แต่อิชมาเอลบุตรเนธานิยาห์และเป็นหลานเอลีชามาซึ่งเป็นเชื้อพระวงศ์คนหนึ่งไปยังมิสปาห์พร้อมคนอีกสิบคนในเดือนที่เจ็ด และได้สังหารเกดาลิยาห์กับชาวยูดาห์และชาวบาบิโลนที่อยู่ด้วย 26แล้วประชากรทั้งหมดตั้งแต่ผู้น้อยที่สุดจนถึงผู้ใหญ่ที่สุดพร้อมทั้งบรรดาเจ้าหน้าที่กองทัพ ก็หนีไปยังอียิปต์เพราะกลัวชาวบาบิโลน

เยโฮยาคีนได้รับการปลดปล่อย

(ยรม.52:31-34)

27ในปีที่สามสิบเจ็ดของการที่กษัตริย์เยโฮยาคีนแห่งยูดาห์ตกเป็นเชลย ซึ่งเป็นปีที่เอวิลเมโรดัก25:27 มีอีกชื่อหนึ่งว่าอาเมลมาร์ดุค ขึ้นเป็นกษัตริย์บาบิโลน พระองค์ทรงปล่อยเยโฮยาคีนออกจากคุกในวันที่ยี่สิบเจ็ดเดือนที่สิบสอง 28พระองค์ตรัสกับเยโฮยาคีนอย่างอ่อนโยน และให้ประทับนั่งในตำแหน่งที่มีเกียรติกว่ากษัตริย์อื่นๆ ที่ถูกจับมาเป็นเชลยในบาบิโลน 29ฉะนั้นเยโฮยาคีนจึงได้ทรงถอดชุดนักโทษออก และได้ทรงร่วมโต๊ะเสวยกับกษัตริย์เป็นประจำตลอดพระชนม์ชีพ 30กษัตริย์ยังได้ประทานเบี้ยเลี้ยงประจำวันแก่เยโฮยาคีนตลอดพระชนม์ชีพ