2 ነገሥት 20 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 20:1-21

የሕዝቅያስ መታመም

20፥1-11 ተጓ ምብ – 2ዜና 32፥24-26ኢሳ 38፥1-8

1በዚያ ጊዜ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ሊሞት ተቃርቦ ነበር። የአሞጽ ልጅ ነቢዩ ኢሳይያስም ወደ እርሱ ሄዶ፣ “እግዚአብሔር፣ ‘ትሞታለህ፤ ከእንግዲህ በሕይወት አትኖርምና ቤትህን አስተካክል’ ብሎሃል” አለው።

2ሕዝቅያስም ፊቱን ወደ ግድግዳው መልሶ እንዲህ ሲል ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ 3እግዚአብሔር ሆይ፤ በታማኝነትና በፍጹም ልብ በፊትህ እንደ ሄድሁ፣ አንተን ደስ የሚያሰኝህንም እንዳደረግሁ ዐስብ፤” ሕዝቅያስም ምርር ብሎ አለቀሰ።

4ኢሳይያስ የመካከለኛውን አደባባይ ዐልፎ ከመሄዱ በፊት የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እርሱ መጣ፤ 5“ተመለስና የሕዝቤን አለቃ ሕዝቅያስን እንዲህ በለው፤ ‘የአባትህ የዳዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ጸሎትህን ሰምቻለሁ፤ እንባህንም አይቻለሁ፤ እነሆ፤ እፈውስሃለሁ። ከዛሬ ሦስት ቀን በኋላ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ትወጣለህ፤ 6በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምርልሃለሁ፤ አንተንና ይህችንም ከተማ ከአሦር ንጉሥ እጅ እታደጋለሁ፤ ስለ እኔ ስለ ራሴና ስለ ባሪያዬ ስለ ዳዊት ስል ይህችን ከተማ እከላከልላታለሁ።’ ”

7ከዚያም ኢሳይያስ፣ “ትኵስ የበለስ ጥፍጥፍ አዘጋጁ” አላቸው፤ እነርሱም አዘጋጅተው ዕባጩ ላይ አደረጉለት፤ ተፈወሰም።

8ሕዝቅያስም፣ “እግዚአብሔር እኔን ስለ መፈወሱ፣ ከሦስት ቀን በኋላም ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስለ መውጣቴ ምልክቱ ምንድን ነው?” ሲል ኢሳይያስን ጠየቀው።

9ኢሳይያስም፣ “እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ እንደሚፈጽም ምልክቱ ይህ ነው፤ ጥላው ዐሥር ደረጃ ወደ ፊት ይቅደምን? ወይስ ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ ይመለስ?” ሲል ጠየቀው።

10ሕዝቅያስም መልሶ፣ “ጥላው ዐሥር ደረጃ ወደ ፊት መሄዱ ቀላል ነገር ነው፤ ይልቁን ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ ይመለስ” አለ።

11ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ፤ እግዚአብሔርም አካዝ በሠራው ደረጃ ላይ የወረደውን ጥላ ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላው እንዲመለስ አደረገ።

ከባቢሎን የመጡ መልእክተኞች

20፥12-19 ተጓ ምብ – ኢሳ 39፥1-8

20፥20-21 ተጓ ምብ – 2ዜና 32፥32-33

12በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ የባልዳን ልጅ መሮዳክ ባልዳን የሕዝቅያስን መታመም ሰምቶ ስለ ነበር፣ ደብዳቤና ገጸ በረከት ለሕዝቅያስ ላከለት። 13ሕዝቅያስም መልክተኞቹን ተቀብሎ በዕቃ ቤቱ ያለውን ሁሉ ብሩን፣ ወርቁን ቅመማ ቅመሙንና ከፍ ያለ ዋጋ ያለውን ዘይት የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቱንና በቀረውም ግምጃ ቤት ያለውን በሙሉ አሳያቸው። በቤተ መንግሥቱም ሆነ በመላው ግዛቱ ሕዝቅያስ ሳያሳያቸው የቀረ ምንም ነገር አልነበረም።

14ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ ሕዝቅያስ ሄዶ፣ “እነዚያ ሰዎች ምን አሉህ? የመጡትስ ከወዴት ነው?” ሲል ጠየቀው።

ሕዝቅያስም መልሶ፣ “የመጡት ከሩቅ አገር ከባቢሎን ነው” አለው።

15ነቢዩም፣ “በቤተ መንግሥትህ ምን ምን አዩ?” ሲል ጠየቀው።

ሕዝቅያስም፣ “በቤተ መንግሥቴ ያለውን ሁሉ አይተዋል፤ በግምጃ ቤቶቼ ሳላሳያቸው የቀረ ምንም ነገር የለም” አለ።

16ከዚያም ኢሳይያስ ሕዝቅያስን እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ 17በቤተ መንግሥትህ ያለው ሁሉ አባቶችህም እስከ ዛሬ ድረስ ያከማቹት በሙሉ ወደ ባቢሎን የሚወሰድበት ጊዜ በርግጥ ይመጣል፤ አንዳች የሚቀር ነገር የለም ይላል እግዚአብሔር18የሥጋህ ቍራጭ የዐጥንትህ ፍላጭ ከሚሆኑት፣ ከምትወልዳቸው ልጆችህ አንዳንዶቹ በምርኮ ይወሰዳሉ፤ በባቢሎንም ቤተ መንግሥት ጃንደረቦች ይሆናሉ።” 19ሕዝቅያስም፣ “የተናገርኸው የእግዚአብሔር ቃል መልካም ነው” ሲል መለሰ፤ “እኔ እስካለሁ ድረስ ሰላምና ጸጥታ ከተገኘ የሆነው ይሁን” ብሎ አስቧልና። 20በሕዝቅያስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራ፣ የፈጸመውም ሁሉ ኵሬውንና ውሃውን ወደ ከተማዪቱ ያመጣበትን የመሬት ለመሬት ቦይ እንዴት አድርጎ እንደ ሠራው በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 21ሕዝቅያስም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ ምናሴም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Swedish Contemporary Bible

2 Kungaboken 20:1-21

Hiskias sjukdom

(2 Krön 32:24; Jes 38:1-8; 38:21-22)

1Vid denna tid blev Hiskia dödligt sjuk, och profeten Jesaja, Amos son, kom till honom och sa: ”Så säger Herren: ’Se om ditt hus, för du kommer att dö; du överlever inte detta.’ ”

2Hiskia vände sig då mot väggen och bad till Herren: 3Herre, kom ihåg hur jag har levt inför dig troget och helhjärtat och gjort det som är gott i dina ögon!” Och han grät förtvivlat.

4Innan Jesaja hade lämnat den mellersta palatsgården, kom Herrens ord till honom igen: 5”Gå tillbaka till Hiskia, fursten över mitt folk, och säg: ’Så säger Herren, din förfader Davids Gud: ”Jag har hört din bön och sett dina tårar. Jag ska göra dig frisk, och om tre dagar ska du gå till Herrens hus. 6Jag ska förlänga ditt liv med femton år. Jag ska rädda dig och denna stad från den assyriske kungens makt. Jag ska försvara denna stad för min och för min tjänare Davids skull.” ’ ”

7Jesaja sa: ”Ta fram en kaka av fikon.” De gjorde så och lade den på svullnaden. Så blev Hiskia frisk.

8Hiskia frågade Jesaja: ”Vad är tecknet på att Herren ska göra mig frisk och att jag får gå upp till Herrens hus om tre dagar?” 9Jesaja svarade: ”Herren ska ge dig ett tecken på att han ska hålla vad han lovat. Vill du att skuggan på soluret ska gå tio streck framåt eller tio streck bakåt?” 10”Solskuggan har ju alltid lätt att gå tio streck framåt. Gör så att den går tio streck bakåt”, svarade Hiskia.

11Profeten Jesaja bad då Herren att göra så, och han lät skuggan på Achas solur gå tio streck tillbaka, streck som den redan gått framåt.

Sändebud från Babylon till Hiskia

(Jes 39:1-8)

12Då skickade kungen av Babylonien, Berodak Baladan, Baladans son, ett brev och en gåva till Hiskia, eftersom han hade hört att denne varit sjuk men blivit frisk igen.

13Hiskia lyssnade till sändebuden och visade dem hela sitt förrådshus med silver och guld, kryddor, välluktande oljor och sitt vapenförråd och allt som fanns i hans skattkammare. Det fanns ingenting i hans palats eller i hela riket som han inte visade för dem.

14Profeten Jesaja kom då till kung Hiskia och frågade honom: ”Vad ville dessa män? Var kom de ifrån?” ”De kom från ett avlägset land, ända bortifrån Babylonien”, svarade Hiskia. 15”Hur mycket lät du dem se i ditt palats?” frågade Jesaja. Hiskia svarade: ”Jag visade dem allt i mitt palats. Det finns ingenting i mina skattkamrar som jag inte visat dem.”

16Då sa Jesaja till Hiskia: ”Hör vad Herren säger: 17’Den tid ska komma då allt som finns i ditt palats, allt som dina förfäder har samlat fram till nu, ska föras bort till Babylonien. Ingenting kommer att lämnas kvar, säger Herren. 18Och några av dina egna söner som ska födas åt dig kommer att tas till tjänst i den babyloniske kungens palats.’ ”

19Hiskia svarade: ”Herrens ord, som du har talat, är gott.” Men för sig själv tänkte han: ”Det kommer åtminstone att vara fred och trygghet under min livstid.”

20Hiskias historia i övrigt, hans stora bedrifter, dammen och vattenledningen han byggde och hur han ledde vattnet in i staden, finns nedtecknat i Juda kungars krönika.

21När Hiskia dog begravdes han bland sina förfäder. Hans son Manasse blev kung efter honom.