2 ቆሮንቶስ 9 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

2 ቆሮንቶስ 9:1-15

1ለቅዱሳን ስለሚደረገው አገልግሎት ልጽፍላችሁ አያስፈልግም። 2ምክንያቱም ሌሎችን ለመርዳት ያላችሁን በጎ ፈቃድ ዐውቃለሁ፤ ካለፈው ዓመት ጀምሮ እናንተ በአካይያ የምትኖሩ ሌሎችን ለመርዳት ዝግጁ እንደ ሆናችሁ ለመቄዶንያ ሰዎች አፌን ሞልቼ ተናግሬአለሁ፤ ቅን ፍላጎታችሁም ብዙዎችን ለበጎ ሥራ አነሣሥቷል። 3እንግዲህ በዚህ ነገር በእናንተ ላይ ያለን ትምክሕት ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር፣ አስቀድሞ ስለ እናንተ እንደ ተናገርሁት ተዘጋጅታችሁ እንድትገኙ ወንድሞችን ልኬአለሁ። 4ምናልባት የመቄዶንያ ሰዎች ከእኔ ጋር መጥተው ሳትዘጋጁ ቢያገኟችሁ፣ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ እኛም ያን ያህል በእናንተ በመመካታችን እናፍራለን። 5ስለዚህ ወንድሞች አስቀድመው ወደ እናንተ እንዲመጡና ከዚህ በፊት ለመስጠት ቃል የገባችሁትን ስጦታ አጠናቅቃችሁ እንድትጠብቋቸው፣ እነርሱን መለመን አስፈላጊ ሆኖ አግኝቻለሁ፤ እንግዲህ በልግስና ለመስጠት ያሰባችሁት ነገር በግዴታ ሳይሆን በፈቃደኝነት የተዘጋጀ ይሆናል።

በልግስና መስጠት

6ይህን አስታውሱ፤ ጥቂት የዘራ ጥቂት ያጭዳል፤ ብዙ የዘራ ብዙ ያጭዳል። 7እያንዳንዱ ሰው በቅሬታ ወይም በግዴታ ሳይሆን፣ በልቡ ያሰበውን ያህል ይስጥ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ሰው ይወድዳል። 8ሁልጊዜ በሁሉ ነገር የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ እንድትተርፉ፣ እግዚአብሔር ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል፤ 9ይህም፣

“በተነ፤ ለድኾችም ሰጠ፤

ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል”

ተብሎ እንደ ተጻፈው ነው።

10ለዘሪ ዘርን፣ ለመብላት እንጀራን የሚሰጥ እርሱ የምትዘሩትን አትረፍርፎ ይሰጣችኋል፤ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያበዛላችኋል። 11ሁልጊዜ በልግስና መስጠት እንድትችሉ በሁሉ ነገር ያበለጽጋችኋል፤ ልግስናችሁም በእኛ በኩል የሚደርሳቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ለማመስገን ምክንያት ይሆናቸዋል።

12ይህ የምትሰጡት አገልግሎት የቅዱሳንን ጕድለት የሚያሟላ ብቻ ሳይሆን፣ ብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር የሚቀርብበት ነው። 13የክርስቶስን ወንጌል ተቀብላችሁ ስለ ታዘዛችሁና ለእነርሱም ሆነ ለሌሎች ስላሳያችሁት ልግስና ሰዎች ተፈትኖ ስላለፈው አገልግሎታችሁ እግዚአብሔርን ያከብራሉ፤ 14ስለ እናንተም በሚጸልዩበት ጊዜ እግዚአብሔር ከሰጣችሁ ታላቅ ጸጋ የተነሣ ይናፍቋችኋል። 15በቃላት ሊገለጥ ስለማይቻል ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

哥林多後書 9:1-15

1關於捐助聖徒的事,其實我不必再寫信提醒你們, 2因我知道你們的熱心。我向馬其頓教會的人誇耀你們,說亞該亞人的捐款在一年前就預備好了,你們的熱心激勵了許多人。 3現在我先派這幾位弟兄到你們那裡,以便你們把捐款預備好,正如我所說的那樣,免得我們在這件事上誇耀你們的話成了虛言。 4因為萬一有馬其頓的人與我同去,發現你們並沒有準備好,不但我們會因如此信任你們而羞愧,你們也會無地自容。 5因此,我認為有必要請那幾位弟兄先去你們那裡,將你們從前認捐的款項收集妥當,這樣就表明你們的捐贈是出於甘心樂意,而不是出於勉強。

甘心樂意地捐助

6要記住:「少種的少收,多種的多收。」 7各人心裡想捐多少就捐多少,不要勉強,不要為難。因為捐得甘心樂意的人才是上帝所喜愛的。 8上帝能夠將各樣的恩典多多賜給你們,使你們在各方面常常富足有餘,可以多行各樣的善事。 9正如聖經上說:

「他慷慨施捨、賙濟窮人,

他的仁義永遠長存。」

10賜農夫種子又賜人糧食的上帝,必加倍賜給你們種子,使你們收穫更多仁義的果子, 11叫你們事事豐裕,可以多多施捨。這樣,從我們這裡得到你們幫助的人便會向上帝獻上感恩。 12因為這件善事不單可以幫助經濟困難的聖徒,也使許多人對上帝充滿感恩。 13通過這件善事,他們會把榮耀歸給上帝,因為看見你們信服基督的福音,慷慨地幫助他們及眾人。 14他們也會因上帝賜給你們的豐盛恩典而熱切地為你們禱告。 15感謝上帝,祂的恩賜真是無以言表!