2 ቆሮንቶስ 11 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

2 ቆሮንቶስ 11:1-33

ጳውሎስና ሐሰተኞች ሐዋርያት

1ጥቂቱን ሞኝነቴን እንደምትታገሡኝ ተስፋ አደርጋለሁ፤ በርግጥም እየታገሣችሁኝ ነው። 2በእግዚአብሔር ቅናት እቀናላችኋለሁ፤ እናንተን እንደ ንጽሕት ድንግል ለክርስቶስ ለማቅረብ ለአንድ ባል ዐጭቻችኋለሁና። 3ነገር ግን እባብ ሔዋንን በተንኰል እንዳሳታት ምናልባት የእናንተም ልቡና ተበላሽቶ ለክርስቶስ ካላችሁ ቅንነትና ንጽሕና እንዳትወሰዱ እሠጋለሁ። 4ምክንያቱም አንድ ሰው ወደ እናንተ መጥቶ እኛ ከሰበክንላችሁ ኢየሱስ ሌላ ኢየሱስ ቢሰብክላችሁ፣ ወይም ከተቀበላችሁት መንፈስ የተለየ መንፈስ ብትቀበሉ፣ ወይም ከተቀበላችሁት ወንጌል የተለየ ወንጌል ብትቀበሉ፣ ነገሩን በዝምታ ታልፉታላችሁ ማለት ነው። 5እኔ ግን “ታላላቅ ሐዋርያት” ከሚባሉት በምንም የማንስ አይመስለኝም። 6የንግግር ችሎታ ባይኖረኝም እንኳ፣ ዕውቀት ግን አለኝ፤ ይህንም በሁሉ መንገድ በሚገባ ግልጽ አድርገንላችኋል።

7እናንተ ከፍ እንድትሉ ራሴን ዝቅ አድርጌ የእግዚአብሔርን ወንጌል ያለ ዋጋ ለእናንተ መስበኬ እንደ ኀጢአት ተቈጥሮብኝ ይሆን? 8እናንተን ለማገልገል ስል ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ርዳታ በመቀበሌ እነርሱን ዘርፌአቸዋለሁ። 9ከእናንተም ጋር ሳለሁ አንዳች ባስፈለገኝ ጊዜ፣ ከመቄዶንያ የመጡ ወንድሞች የሚያስፈልገኝን ስለ ሰጡኝ ለማንም ሸክም አልሆንሁም። በእናንተ ላይ በምንም ነገር ሸክም እንዳልሆን ተጠንቅቄአለሁ፤ ወደ ፊትም እጠነቀቃለሁ። 10የክርስቶስ እውነት በውስጤ እስካለ ድረስ፣ በአካይያ አውራጃ ይህን ትምክሕቴን ማንም ሊገታው አይችልም። 11ይህን የምለው ለምንድን ነው? ስለማልወድዳችሁ ነውን? እንደምወድዳችሁ እግዚአብሔር ያውቃል። 12ከእኛ ጋር እኩል ለመሆን በሥራቸው እየተመኩ ቀን የሚጠብቁትን ሰዎች ምክንያት ለማሳጣት አሁን የማደርገውን ወደ ፊትም አደርጋለሁ።

13እንደነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት ለመምሰል ራሳቸውን የሚለዋውጡ፣ ሐሰተኞች ሐዋርያትና አታላዮች ሠራተኞች ናቸው። 14ይህም የሚያስደንቅ ነገር አይደለም፤ ምክንያቱም ሰይጣን ራሱ የብርሃን መልአክ ለመምሰል ራሱን ይለዋውጣል። 15እንግዲህ የእርሱ አገልጋዮች፣ የጽድቅ አገልጋዮች ለመምሰል ራሳቸውን ቢለውጡ የሚያስገርም አይደለም፤ ፍጻሜአቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል።

ጳውሎስ በደረሰበት መከራ ይመካል

16እንደ ገና ይህን እላለሁ፤ ማንም ሰው እንደ ሞኝ አይቍጠረኝ፤ እናንተም የምትቈጥሩኝ ከሆነ፣ እኔም በጥቂቱ እንድመካ እንደ ሞኝ ተቀበሉኝ። 17እንደዚህ ልበ ሙሉ ሆኜ የምናገረው እንደ ሞኝ እንጂ እንደ ጌታ ፈቃድ አይደለም። 18ብዙዎች በዓለማዊ ነገር ስለሚመኩ እኔም ደግሞ እመካለሁ። 19እናንተም ብልኆች ስለ ሆናችሁ ሞኞችን በደስታ ትታገሣላችሁ፤ 20ማንም ተነሥቶ ባሪያ ቢያደርጋችሁ፣ ቢበዘብዛችሁ፣ ለጥቅሙ ሲል ቢጠጋችሁ፣ ቢንቀባረርባችሁ ወይም ፊታችሁን በጥፊ ቢመታችሁ ትታገሣላችሁ። 21እኛ ግን ለዚያ እጅግ ደካሞች መሆናችንን እያፈርሁ እናገራለሁ።

ማንም በድፍረት በሚመካበት ነገር ሁሉ እኔም ደፍሬ መመካት እንደምችል እንደ ሞኝ እናገራለሁ። 22እነርሱ ዕብራውያን ናቸውን? እኔም ነኝ፤ እስራኤላውያን ናቸውን? እኔም ነኝ፤ የአብርሃም ዘር ናቸውን? እኔም ነኝ። 23የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸውን? አእምሮውን እንደ ጣለ ሰው ልናገርና እኔ እበልጣቸዋለሁ፤ ደግሞም ብዙ ጊዜ በሥራ ደክሜአለሁ፤ ብዙ ጊዜ ታስሬአለሁ፤ ብዙ ጊዜ ተገርፌአለሁ፤ ብዙ ጊዜ ለሞት ተቃርቤአለሁ። 24አይሁድ ለአርባ ጅራፍ አንድ የቀረው አምስት ጊዜ ገርፈውኛል። 25ሦስት ጊዜ በዱላ ተደብድቤአለሁ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ ተወግሬአለሁ፤ ሦስት ጊዜ የመርከብ አደጋ ደርሶብኛል፤ አንድ ሌሊትና ቀን በባሕር ላይ ዐድሬአለሁ፤ 26ብዙ ጊዜ በጕዞ ተንከራትቻለሁ፤ ደግሞም ለወንዝ ሙላት አደጋ፣ ለወንበዴዎች አደጋ፣ ለገዛ ወገኖቼ አደጋ፣ ለአሕዛብ አደጋ፣ ለከተማ አደጋ፣ ለገጠር አደጋ፣ ለባሕር አደጋ እንዲሁም ለሐሰተኞች ወንድሞች አደጋ ተጋልጬ ነበር። 27ብዙ ጥሬአለሁ፤ ብዙ ደክሜአለሁ፤ ብዙ ጊዜ እንቅልፍ አጥቻለሁ፤ ተርቤአለሁ፤ ተጠምቻለሁ፤ ብዙ ጊዜ ምግብ ሳልቀምስ ኖሬአለሁ፤ በብርድና በዕራቍትነት ተቈራምጃለሁ። 28ሌላውን ነገር ሳልቈጥር፣ ዕለት ዕለት የሚያስጨንቀኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሐሳብ ነው። 29ደካማ ማን ነው? እኔስ አብሬ አልደክምምን? በኀጢአት የሚሰናከል ማን ነው? እኔስ አልቈጭምን?

30መመካት ካለብኝ፣ ደካማነቴን በሚያሳዩ ነገሮች እመካለሁ። 31ለዘላለም የተመሰገነው የጌታ የኢየሱስ አምላክና አባት እንደማልዋሽ ያውቃል። 32ደማስቆ ሳለሁ ከንጉሥ አርስጦስዮስ በታች የሆነው ገዥ ሊያስይዘኝ ፈልጎ፣ የደማስቆ ሰዎችን ከተማ ያስጠብቅ ነበር። 33ነገር ግን በግንቡ መስኮት በኩል በቅርጫት አውርደውኝ ከእጁ አመለጥሁ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס השנייה אל-הקורנתים 11:1-33

1אני מקווה שתתייחסו אלי בסבלנות גם אם אני מדבר בטיפשות.

אנא, סלחו לי והניחו לי לומר את אשר על לבי. 2אני דואג לכם דאגה עמוקה כאלוהים עצמו; אתם כבתולה טהורה שהארשתי לאיש אחד, למשיח. 3אך אני חושש שמא תסטו יום אחד ממסירותכם הטהורה למשיח, כשם שחווה רומתה על־ידי הנחש בגן העדן. 4אתם מתנהגים כפתאים ומאמינים לכל מה שאומרים לכם, גם אם מישהו מכריז לכם על ישוע השונה מזה שהכרזנו, או על רוח ששונה מרוח הקודש שקיבלתם, או על דרך שונה לישועה. אכן, אתם מוכנים להאמין לכל דבר!

5סבורני שאיני נופל במאומה מ”שליחים“ מיוחדים אלה! 6אולי אינני נואם מעולה, אך אני יודע לפחות על מה אני מדבר, כפי שהוכחנו לכם פעמים רבות.

7האם חטאתי כשהשפלתי את עצמי (כדי לרומם אתכם!) ובישרתי לכם את בשורת האלוהים ללא תשלום? 8קהילות אחרות תמכו בי בעת שעבדתי למענכם. כן, לקחתי את כספם כדי לעזור לכם. 9בכל עת שהותי עמכם לא ביקשתי מכם פרוטה; האחים שבאו ממקדוניה סיפקו את כל צרכי. מעולם לא ביקשתי מכם דבר, וגם להבא לא אבקש. 10בשם אמת המשיח בי, אני מבטיח שאתגאה על כך בכל יוון! 11מדוע? האם משום שאיני אוהב אתכם? אלוהים יודע שאני אוהב אתכם! 12אעשה זאת כדי לסכור את פיהם של אלה שמתפארים וטוענים: ”אנחנו עושים את עבודת אלוהים בדיוק כמו פולוס וטימותיוס!“

13אנשים אלה הינם שליחי־שקר, רמאים שמתחפשים לשליחי המשיח. 14אך איני מתפלא על כך! אם השטן עצמו יכול להתחפש למלאך אור, 15אין פלא שמשרתיו יכולים להתחפש למשרתי צדק. אך לבסוף הם יקבלו את העונש שמגיע להם על מעלליהם.

16אני חוזר ואומר, אל תחשבוני לשוטה, אך גם אם אתם חושבים אותי לשוטה, הקשיבו לי בכל זאת והניחו לי להתגאות כמוהם. 17גאווה זאת לא ניתנה לי מאת המשיח, שכן אני נוהג כשוטה. 18אך מאחר שרבים מתגאים על הישגיהם האנושיים, גם אני אתגאה כמוהם. 19אתם חושבים את עצמכם לחכמים גדולים, אך אתם מקשיבים ברצון לשוטים האלה. 20לא אכפת לכם אם הם משעבדים אתכם, מנצלים אתכם, מכשילים אתכם, סוטרים על פניכם או מתנשאים עליכם. 21אני מתבייש להודות שאיני חזק או נועז כמוהם. אך בכל מה שהם יכולים להתגאות, אני שוב מדבר כשוטה, גם אני יכול להתגאות! 22האם הם עברים? גם אני. האם הם ישראלים? גם אני. זרע אברהם? גם אני. 23האם הם משרתי המשיח? אולי אני מדבר כשוטה, אך אני משרת טוב מהם! עמלתי קשה מהם, הושלכתי לכלא פעמים רבות מהם, הוכיתי יותר, ועמדתי לפני המוות פעמים רבות יותר. 24חמש פעמים הלקוני היהודים שלושים־ותשע מלקות. 25שלוש פעמים הולקיתי בשוטים, פעם אחת נסקלתי באבנים, שלוש פעמים נטרפה ספינתי, ופעם נסחפתי עשרים־וארבע שעות בים הפתוח. 26במסעותיי הרבים והמעייפים ניצלתי מסכנת שיטפונות, מידי שודדים, מידי היהודים ומידי הגויים. הותקפתי על־ידי המון בערים שונות, ניצלתי ממוות במדבר, מטביעה בים ומאנשים שהתחזו כמאמינים משיחיים. 27עמלתי וטרחתי ולילות רבים לא עצמתי עין. פעמים רבות רעבתי וצמאתי; כן, הייתי ללא אוכל, לבוש או קורת־גג.

28מלבד כל אלה אני נושא עמי דאגה מתמדת לשלום הקהילות. 29כאשר מישהו שוגה, אני חש בצערו. כאשר מישהו חוטא, לבי כואב.

30אם עלי להתגאות, אני בוחר להתגאות בדברים שמראים את חולשתי. 31האלוהים ואבי המשיח אדוננו, יבורך שמו לעולמים, יודע שאני דובר אמת. 32בהיותי בדמשק, המושל מטעם המלך ארטס הפקיד שומרים על שערי העיר כדי לתפסני, 33אך הורדתי בסל דרך פתח בחומה ונמלטתי מידיו.