2 ሳሙኤል 8 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 8:1-18

ዳዊት የተቀዳጃቸው ድሎች

8፥1-14 ተጓ ምብ – 1ዜና 18፥1-13

1ከዚህ በኋላ ዳዊት ፍልስጥኤማውያንን ድል አደረጋቸው፤ በቍጥጥሩም ሥር አዋላቸው፤ ሜቴግ አማ የተባለችውንም ከተማ ከፍልስጥኤማውያን ቍጥጥር ነጻ አደረጋት።

2እንዲሁም ዳዊት ሞዓባውያንን ድል አደረገ፤ በመሬት ላይ አጋድሞ በገመድ ለካቸው፤ በገመድ ከተለኩትም ሁለት እጅ ሲገድል፣ አንድ እጅ ግን በሕይወት ይተው ነበር። ስለዚህ ሞዓባውያን የዳዊት ተገዦች ሆኑ፤ ገበሩለትም።

3ከዚህም በቀር ዳዊት በኤፍራጥስ ወንዝ አጠገብ ያለውን ግዛት መልሶ ለመያዝ በሄደ ጊዜ፣ የሱባን ንጉሥ የረአብን ልጅ አድርአዛርን ወጋው። 4ዳዊትም አንድ ሺሕ ሠረገሎች፣ ሰባት ሺሕ ፈረሰኞችና8፥4 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም (እንዲሁም የሙት ባሕር ጥቅልልና 1ዜና 18፥4 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ሰባት መቶ ሠረገለኞቹን ይላል። ሃያ ሺሕ እግረኞች ማረከበት። ቍጥራቸው መቶ የሆነ የሠረገላ ፈረሶች ብቻ ሲቀሩ ሌሎቹን በሙሉ ቋንጃቸውን ቈረጠ።

5የደማስቆዎቹ ሶርያውያን የሱባን ንጉሥ አድርአዛርን ለመርዳት በመጡ ጊዜ ዳዊት ሃያ ሁለት ሺሕ ሰው ገደለባቸው። 6ከዚያም የደማስቆ ክፍል በሆነው የሶርያውያን ግዛት የጦር ሰፈሮችን አቋቋመ፤ ሶርያውያን ተገዙለት፤ ገበሩለትም። እግዚአብሔርም ዳዊት በሄደበት ሁሉ ድልን ሰጠው።

7ዳዊት የአድርአዛር ሹማምት ያነገቧቸውን የወርቅ ጋሻዎች ወስዶ ወደ ኢየሩሳሌም አመጣቸው። 8ንጉሡ ዳዊት ቤጣህና8፥8 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 18፥8 ይመ)፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ ቴባ ይላሉ። ቤሮታይ ከተባሉ ከአድርአዛር ከተሞችም እጅግ ብዙ ናስ አጋዘ።

9የሐማት ንጉሥ ቶዑ፣ ዳዊት መላውን የአድርአዛርን ሰራዊት ማሸነፉን በሰማ ጊዜ፣ 10ቶዑ ከአድርአዛር ጋር ሁልጊዜ ይዋጋ ስለ ነበር፣ ሰላምታና በአድርአዛር ላይ ስለ ተቀዳጀውም ድል የደስታ መግለጫ እንዲያቀርብለት፣ ልጁን ዮራምን ወደ ንጉሥ ዳዊት ላከው፤ እርሱም የብር፣ የወርቅና የናስ ዕቃ ይዞ መጣ።

11ንጉሥ ዳዊትም፣ ቀድሞ ካስገበራቸው መንግሥታት ሁሉ በገባለት ብርና ወርቅ እንዳደረገው፣ እነዚህንም ዕቃዎች ለእግዚአብሔር ቀደሳቸው። 12የገበሩትም መንግሥታት ኤዶምና8፥12 አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ (እንዲሁም 1ዜና 18፥11 ይመ)፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ አራም ይላሉ። ሞዓብ፣ አሞናውያን፣ ፍልስጥኤማውያንና አማሌቃውያን ነበሩ። እንዲሁም ከሱባ ንጉሥ ከረአብ ልጅ ከአድርአዛር የወሰደውን ምርኮ ለእግዚአብሔር ቀደሰ።

13ዳዊት የጨው ሸለቆ በተባለው ስፍራ ዐሥራ ስምንት ሺሕ ኤዶማውያንን8፥13 ጥቂት የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና የሱርስቱ ቅጅ (እንዲሁም 1ዜና 18፥11 ይመ)፤ ከዚህ ጋር ይስማማል አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ አራም ይላሉ። ገድሎ ከተመለሰ በኋላ ስሙ ገነነ።

14በመላው ኤዶም የጦር ሰፈሮችን አቋቋመ፤ ኤዶማውያን ሁሉ ለዳዊት ተገዙ፤ እግዚአብሔርም ዳዊት በሄደበት ስፍራ ሁሉ ድልን ሰጠው።

የዳዊት ሹማምት

8፥15-18 ተጓ ምብ – 1ዜና 18፥14-17

15ዳዊት በመላው እስራኤል ላይ ነገሠ፤ ለሕዝቡም ሁሉ ፍትሕና ርትዕ አሰፈነላቸው። 16የጽሩያ ልጅ ኢዮአብ የሰራዊቱ አለቃ ሲሆን፣ የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥም ታሪክ ጸሓፊ ነበረ። 17እንዲሁም የአኪጦብ ልጅ ሳዶቅና የአብያታር ልጅ አቢሜሌክ ካህናት ሲሆኑ፣ ሠራያ ጸሓፊ ነበረ፤ 18የዮዳሔ ልጅ በናያስ የከሪታውያንና የፈሊታውያን አለቃ ሲሆን፣ የዳዊት ወንዶች ልጆች ደግሞ የቤተ መንግሥት አማካሪዎች8፥18 ወይም ካህናት ተብሎ መተርጐም ይችላል። ነበሩ።

O Livro

2 Samuel 8:1-18

As vitórias de David

(1 Cr 18.1-14)

1Depois disto, David venceu e submeteu os filisteus, tirando das mãos deles Metegue-Amá, a sua maior cidade.

2Também conquistou Moabe. Dividiu as suas vítimas, fazendo-as deitarem-se lado a lado, em fileiras. Depois de medir com uma fita, dois terços de cada fila eram condenados a morrer; o terço restante era poupado, para serem servos de David; pagaram-lhe um tributo anualmente, daí em diante.

3Conquistou o domínio do rei Hadadezer, filho de Reobe, rei de Zobá, numa batalha junto ao rio Eufrates, porque Hadadezer tinha tentado retomar o poder. 4David capturou 1700 cavaleiros e 20 000 soldados. Inutilizou os cavalos dos seus carros de combate, à exceção de uma centena que guardou para seu próprio uso.

5Quando os arameus vieram de Damasco para socorrer Hadadezer, David matou 22 000 deles. 6David pôs várias guarnições militares em Damasco, e os arameus tornaram-se seus súbditos, pagando-lhe um tributo anual. O Senhor concedia-lhe sempre vitórias, para onde quer que se virasse. 7Trouxe também para Jerusalém os escudos de ouro que os oficiais do rei Hadadezer usavam, 8assim como uma grande quantidade de bronze de Beta e de Berotai, cidades do rei Hadadezer.

9Quando o rei Toú de Hamate ouviu narrar todas as vitórias de David sobre o exército de Hadadezer, 10enviou o seu filho Jorão para felicitá-lo, visto que Hadadezer e Toú eram inimigos. Jorão trouxe-lhe presentes de prata, ouro e bronze. 11-12David consagrou tudo isso ao Senhor, assim como os despojos de prata e ouro que trouxera dos combates contra Aram, Moabe, Amon, os filisteus, Amaleque e o rei Hadadezer, filho de Reobe, rei de Zobá.

13David tornou-se muito famoso. Depois disso, ainda destruiu 18 000 edomitas8.13 Alguns manuscritos, além da Septuaginta, têm edomitas (cf 1 Cr 18.12); mas a maior parte dos manuscritos hebreus têm arameus. no vale do Sal. 14Colocou também guarnições militares através da terra de Edom, de forma que toda essa nação foi obrigada a pagar tributo a Israel. O Senhor tornou-o vitorioso para onde quer que se dirigisse.

Os oficiais de David

(2 Sm 20.23-26; 1 Cr 18.14-17)

15David reinou com justiça sobre Israel, dirigindo as causas do seu povo com toda a equidade. 16Joabe, filho de Zeruía, era o general do seu exército. O seu secretário para os assuntos da governação era Jeosafá, filho de Ailude. 17Zadoque, filho de Aitube, e Aimeleque, filho de Abiatar, eram os sacerdotes; Seraías era o secretário particular do rei. 18Benaia, filho de Jeoiada, era o chefe da guarda pessoal do rei, formada por cretenses e peleteus. Os filhos do rei eram seus assistentes.