2 ሳሙኤል 6 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 6:1-23

ታቦቱ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ

6፥1-11 ተጓ ምብ – 1ዜና 13፥1-14

6፥12-19 ተጓ ምብ – 1ዜና 15፥25–16፥3

1ዳዊት እንደ ገና ከእስራኤል የተመረጡ በአጠቃላይ ሠላሳ ሺሕ ሰዎች ሰበሰበ። 2እርሱና አብረውት ያሉት ሰዎች ሁሉ በታቦቱ ላይ ባለው ኪሩቤል ላይ በተቀመጠው በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔርም ስም6፥2 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ ስም የሚለውን አይጨምርም። የተጠራውን የእግዚአብሔርን ታቦት ከዚያ ለማምጣት በይሁዳ ወዳለችው ወደ በኣል ሄዱ። 3የእግዚአብሔርንም ታቦት በአዲስ ሠረገላ ላይ አኑረው፣ በኰረብታ ላይ ካለው ከአሚናዳብ ቤት አውጥተው አመጡ፤ ሠረገላውን ይነዱ የነበሩትም የአሚናዳብ ልጆች ዖዛና አሒዮ ሲሆኑ፣ 4የእግዚአብሔርም ታቦት በሠረገላው ላይ ሆኖ6፥4 የሙት ባሕር ጥቅልልና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቲኩ ቅጅ ግን፣ ኰረብታው ላይ ካለው ከአቢናዳብ ቤት ከእግዚአብሔር ታቦት ጋር አመጡት ይላል።፣ አሒዮ ፊት ፊት ይሄድ ነበር። 5ዳዊትና የእስራኤል ቤት በሙሉ በዝማሬ፣ በበገና፣ በመሰንቆ፣ በከበሮ፣ በጸናጽልና በቃጭል ባለ ኀይላቸው ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ያሸበሽቡ ነበር።

6ወደ ናኮን ዐውድማ ሲደርሱም በሬዎቹ ስለ ተደናቀፉ፣ ዖዛ እጁን ዘርግቶ የእግዚአብሔርን ታቦት ያዘ። 7ዖዛ በድፍረት ይህን ስላደረገ፣ የእግዚአብሔር ቍጣ በላዩ ላይ ነደደ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር ቀሠፈው፤ እርሱም በእግዚአብሔር ታቦት አጠገብ እዚያው ሞተ።

8የእግዚአብሔር ቍጣ ዖዛንን ስለ ሰበረው፣ ዳዊት ተከፋ፤ ያም ቦታ እስከ ዛሬ ድረስ ፔሬዝ ዖዛ6፥8 ፔሬዝ ዖዛ ማለት ዑዛንን መሰባበር ማለት ነው ተብሎ ይጠራል።

9ዳዊት በዚያን ቀን እግዚአብሔርን ስለ ፈራ “የእግዚአብሔር ታቦት እንዴት ወደ እኔ ይመጣል?” አለ። 10ስለዚህ ዳዊት የእግዚአብሔር ታቦት አብሮት እንዲሆን ወደ ዳዊት ከተማ ይዞት ለመሄድ አልፈለገም፤ በዚህ ፈንታ አቅጣጫ ለውጦ የጌት ሰው ወደ ሆነው ወደ አቢዳራ ቤት ወሰደው። 11የእግዚአብሔርም ታቦት የጌት ሰው በሆነው በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀመጠ፤ እግዚአብሔርም አቢዳራንና ቤተ ሰቡን ሁሉ ባረከ።

12በዚህ ጊዜ፣ “በእግዚአብሔር ታቦት ምክንያት የአቢዳራን ቤተ ሰውና ያለውን ሁሉ እግዚአብሔር ባረከለት” ብለው ለዳዊት ነገሩት። ስለዚህ ዳዊት ወደዚያው ወርዶ፣ የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ዳዊት ከተማ በታላቅ ደስታ አመጣው። 13እነዚያ የእግዚአብሔርን ታቦት ተሸክመው የነበሩት ሰዎች ስድስት ርምጃ በሄዱ ቍጥር፣ አንድ በሬና አንድ የሠባ ጥጃ ይሠዋ ነበር። 14ዳዊትም የበፍታ ኤፉድ በወገቡ ታጥቆ በሙሉ ኀይሉ በእግዚአብሔር ፊት ይጨፍር ነበር። 15እንዲህ ባለ ሁኔታም ዳዊትና መላው የእስራኤል ቤት ሆይ እያሉና ቀንደ መለከቱን እየነፉ የእግዚአብሔርን ታቦት አመጡ።

16የእግዚአብሔር ታቦት ወደ ዳዊት ከተማ ሲገባ፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል በመስኮት ሆና ትመለከት ነበር፤ ንጉሥ ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ሲዘልልና ሲያሸበሽብ ባየችው ጊዜ በልቧ ናቀችው።

17ከዚያም የእግዚአብሔርን ታቦት አምጥተው፣ ዳዊት በተከለለት ድንኳን ውስጥ አግብተው በተዘጋጀለት ስፍራ አኖሩት፤ ዳዊትም የሚቃጠል መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕት6፥17 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። በእግዚአብሔር ፊት አቀረበ። 18ዳዊት የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረቱን መሥዋዕት ካቀረበ በኋላ ሕዝቡን በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም ባረከ። 19የእስራኤል ወገን ለሆነው ለሕዝቡ ሁሉ፣ ለወንዱም ለሴቱም ለእያንዳንዱ ሰው አንዳንድ እንጀራ፣ አንዳንድ ሙዳ ሥጋና አንዳንድ የዘቢብ ጥፍጥፍ ሰጠ፤ ከዚህ በኋላ ሁሉም ወደየቤቱ ሄደ።

20ዳዊት ቤተ ሰቡን ለመመረቅ ወደ ቤቱ በተመለሰ ጊዜ፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል ልትቀበለው ወጥታ፣ “ዛሬ የእስራኤል ንጉሥ በመኳንንቱ ገረዶች ፊት እንደ አንድ ተራ ሰው ዕራቍቱን መታየቱ ክብሩ ሆኖ ነው!” አለችው።

21ዳዊትም እንዲህ አላት፤ “አዎን ከአባትሽና በቤቱ ካሉት ሁሉ አስበልጦ በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ ገዥ አድርጎ በመረጠኝ በእግዚአብሔር ፊት አሸብሽቤአለሁ፤ አሁንም አሸበሽባለሁ። 22እንዲያውም ከዚህ ይልቅ ራሴን በፊቱ ዝቅ አደርጋለሁ፤ ከዚህም የባሰ የተናቅሁ እሆናለሁ፤ ነገር ግን በጠቀስሻቸው ገረዶች ፊት እከብራለሁ።”

23የሳኦልም ልጅ ሜልኮል እስከሞተችበት ጊዜ ድረስ ልጅ አልወለደችም ነበር።

O Livro

2 Samuel 6:1-23

A arca é trazida para Jerusalém

(1 Cr 15.1-29)

1David mobilizou 30 000 dos melhores soldados de Israel. 2E foram juntos até Baalá de Judá, a fim de trazer de volta a arca de Deus que está consagrada ao Senhor dos exércitos, cujo trono está acima dos querubins. 3-4A arca foi colocada sobre um carro novo e levada da casa de Abinadabe, que ficava numa colina. Era conduzida pelos filhos deste último, Uzá e Aiô. Aiô ia à frente. 5Era seguido por David e pelos outros líderes de Israel que agitavam alegremente ramos de faia, na presença do Senhor, e tocavam liras, harpas, tamborins, pandeiretas e címbalos.

6No entanto, quando chegaram à eira de Nacom, os bois tropeçaram e Uzá estendeu o braço para segurar a arca. 7A ira do Senhor acendeu-se contra ele e Deus matou-o por causa do seu gesto. E ficou ali estendido ao lado da arca de Deus. 8David ficou muito contristado por causa do que o Senhor fizera e deu àquele lugar o nome Perez-Uzá (brecha de Uzá). Ainda hoje é assim chamado.

9O rei ficou com medo do Senhor e interrogava-se: “Como poderei trazer a arca do Senhor até mim?” 10Por isso, resolveu não transportá-la para a Cidade de David, mas levá-la antes para a casa de Obede-Edom, originário de Gate. 11Esta ficou ali por três meses e o Senhor abençoou a Obede-Edom e a toda a sua casa e família.

12Quando o rei soube que o Senhor tinha abençoado Obede-Edom, toda a sua família e bens, por causa da arca de Deus, decidiu ir à casa de Obede-Edom e ordenou que transportassem a arca de Deus com grande alegria para a Cidade de David. 13A cada seis passos que os transportadores da arca davam, paravam e esperavam que se oferecesse o sacrifício de um boi e de um bezerro cevado. 14David dançava perante o Senhor com toda a exuberância, vestido com a veste sacerdotal6.14 No hebraico, éfode de linho. Peça de vestuário habitualmente usada pelos sacerdotes, aqui provavelmente usada por devoção.. 15Foi dessa maneira que Israel trouxe para o seu local próprio a arca do Senhor. Tudo isto acompanhado de brados de júbilo e toques de trombetas.

16Quando a arca do Senhor se aproximou da Cidade de David, Mical, a filha de Saul, que estava observando da janela, viu David a saltar e a dançar na presença do Senhor e desprezou-o no seu íntimo.

17Puseram pois a arca do Senhor numa tenda, no lugar que David tinha preparado. Depois David ofereceu holocaustos e ofertas de paz ao Senhor. 18No final destas ofertas David abençoou o povo em nome do Senhor dos exércitos. 19Distribuiu por cada um, homens e mulheres, um pão, um bolo de tâmaras e um bolo de uvas. Quando tudo terminou todos se retiraram.

20David regressou a casa para abençoar a sua família. No entanto, Mical veio ao seu encontro e exclamou com um tom irónico: “Que ar glorioso tinha hoje o rei de Israel, expondo-se aos olhos das raparigas, ao longo das ruas, como um vadio qualquer!”

21David respondeu-lhe: “Estive a dançar diante do Senhor, que me escolheu em lugar do teu pai e da tua família, e me nomeou chefe de Israel, o povo do Senhor! 22Não me importo de me humilhar mais e rebaixar, como tu dizes, pois sei que mesmo assim serei respeitado pelas raparigas a quem te referias!”

23E Mical não teve filhos durante toda a sua vida.