2 ሳሙኤል 20 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 20:1-26

ሳቤዔ በዳዊት ላይ ዐመፀ

1በዚህ ጊዜ የቢክሪ ልጅ ስሙ ሳቤዔ የተባለ አንድ ምናምንቴ ብንያማዊ በዚያ ነበረ፤ እርሱም መለከት ነፍቶ እንዲህ ሲል ጮኸ፤ “እኛ ከዳዊት ድርሻ የለንም፤ ከእሴይም ልጅ ርስት የለንም፤ እስራኤል ሆይ፤ እያንዳንድህ ወደ ድንኳንህ ተመለስ!”

2ስለዚህ የእስራኤል ሰው ሁሉ ዳዊትን ከድቶ የቢክሪን ልጅ ሳቤዔን ተከተለ። የይሁዳ ሰዎች ግን ከዮርዳኖስ አንሥቶ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ከንጉሣቸው ሳይለዩ አብረውት ሄዱ።

3ዳዊት ኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መንግሥቱ በተመለሰ ጊዜ፤ ቤተ መንግሥቱን እንዲጠብቁ ትቷቸው የሄደውን ዐሥሩን ቁባቶቹን ወሰደ፤ በአንድ ቤትም ውስጥ እንዲጠበቁ አደረገ። ቀለብ ሰጣቸው፤ ይሁን እንጂ ወደ እነርሱ አልገባም ነበር፤ እነርሱም እስከ ሞቱበት ጊዜ ድረስ መበለት ሆነው፣ ለብቻቸው ተገልለው ተቀመጡ።

4ከዚያም ንጉሡ አሜሳይን፣ “የይሁዳ ሰዎች ሁሉ በሦስት ቀን ውስጥ፣ ወደ እኔ እንዲመጡ ጥራልኝ፤ አንተ ራስህም ተገኝ” አለው። 5አሜሳይ ይሁዳን ለመጥራት ሄደ፤ ነገር ግን ንጉሡ ከወሰነው ጊዜ በላይ ቈየ።

6ዳዊትም አቢሳን፣ “ከአቤሴሎም ይልቅ አሁን የቢክሪ ልጅ ሳቤዔ የበለጠ ጕዳት ሊያደርስብን ስለሆነ የጌታህን ሰዎች ይዘህ አሳድደው፤ አለዚያ የተመሸገ ከተማ አግኝቶ ያመልጠናል” አለው። 7ስለዚህ የኢዮአብ ሰዎች፣ ከሊታውያን፣ ፈሊታውያን እንዲሁም ሌሎች ኀያላን ጦረኞች በሙሉ በአቢሳ አዛዥነት ወጡ፤ ከኢየሩሳሌም የወጡትም የቢክሪ ልጅ ሳቤዔን ለማሳደድ ነበር።

8በገባዖን ከታላቁ ቋጥኝ አጠገብ ሳሉ፣ አሜሳይ ሊገናኛቸው መጣ፤ ኢዮአብ የጦር ሜዳ ልብሱን ለብሶ ሰይፉን ከነሰገባው በወገቡ ላይ ታጥቆ ነበር፤ ወደ ፊት ራመድ እንዳለም ሰይፉ ከሰገባው ወጥቶ ወደቀ።

9ኢዮአብም አሜሳይን፣ “ወንድሜ ሆይ፤ እንደ ምንድን ነህ?” አለው፤ ከዚያም አሜሳይን የሚስም መስሎ በቀኝ እጁ ጢሙን ያዘው። 10አሜሳይ ግን በኢዮአብ እጅ ሰይፍ መኖሩን ልብ ስላላለ ጥንቃቄ አላደረገም፤ ስለዚህ ኢዮአብ ሰይፉን ሆዱ ላይ ሻጠበት፤ አንጀቱም መሬት ላይ ተዘረገፈ፤ ከዚያም ኢዮአብ መድገም ሳያስፈልገው፣ አሜሳይ በዚያው ሞተ። ከዚህ በኋላ ኢዮአብና ወንድሙ አቢሳ፣ የቢክሪን ልጅ ሳቤዔን ማሳደድ ጀመሩ።

11በአሜሳይ ሬሳ አጠገብ ከቆሙት ከኢዮአብ ሰዎች አንዱ፤ “ኢዮአብን የሚወድድ፣ የዳዊትም የሆነ ሁሉ ኢዮአብን ይከተል!” አለ። 12በዚህን ጊዜ የአሜሳይ ሬሳ በደም ተጨማልቆ በመንገዱ መካከል ወድቆ ነበር፤ በዚያ የሚያልፈው ሰራዊት ሁሉ መቆሙን ያ ሰው አየ፤ ወደ ሬሳው የደረሰው ሰራዊት ሁሉ መቆሙን በተረዳ ጊዜም፣ የአሜሳይን ሬሳ ከመንገድ ወደ ዕርሻ ፈቀቅ አድርጎ ልብስ ጣል አደረገበት። 13የአሜሳይ ሬሳ ከመንገድ ላይ ከተነሣ በኋላ ሕዝቡ ሁሉ ኢዮአብን ተከትሎ የቢክሪን ልጅ ሳቤዔን ሊያሳድድ ሄደ።

14ሳቤዔም በእስራኤል ነገዶች ሁሉ መካከል ዐልፎ ወደ አቤል ቤትማዓካና ወደ መላው የቢክሪያውያን ግዛት መጣ፤ የቢክሪ ሰዎችም ተሰብስበው ተከተሉት። 15ከኢዮአብ ጋር ያለውም ሰራዊት መጥቶ፣ ሳቤዔን በአቤል ቤትመዓካ በኩል ከበበው፤ በስተ ውጭም እስከ ከተማዪቱ ግንብ ጫፍ ድረስ ዙሪያውን የዐፈር ድልድል ሠሩ፤ ግንቡን ለመናድ በኀይል በሚደበድቡበት ጊዜ፣ 16አንዲት ብልኅ ሴት ድምፅዋን ከፍ አድርጋ፣ “ስሙ! ስሙ! ለኢዮአብ የምነግረው ነገር ስላለ ወደዚህ እንዲመጣ ንገሩት” አለቻቸው። 17ኢዮአብ ወደ እርሷ ሄደ፤ እርሷም፣ “ኢዮአብ አንተ ነህ?” ስትል ጠየቀችው።

እርሱም፣ “አዎን እኔ ነኝ” ብሎ መለሰላት።

እርሷም፣ “እንግዲህ አገልጋይህ የምትለውን አድምጥ” አለችው።

እርሱም፣ “እሺ፣ አደምጣለሁ” አላት።

18ከዚያ በመቀጠልም እንዲህ አለች፤ “በቀድሞው ጊዜ ሰዎች፣ ‘ምክርን ከአቤል ጠይቁ’ ይሉ ነበር፤ ታዲያ እንዳሉትም ይፈጸም ነበር፤ 19በእስራኤል ሰላማዊና ታማኝ ከሆኑ ሰዎች መካከል አንዷ እኔ ነኝ፤ አንተ በእስራኤል እናት የሆነችውን ከተማ ለማጥፋት ትሻለህ፤ የእግዚአብሔርን ርስት ለመዋጥ የፈለግኸው ለምንድን ነው?”

20ኢዮአብም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ይህስ ከእኔ ይራቅ! መዋጡና ማጥፋቱ አሁንም ከእኔ ይራቅ! 21ነገሩስ እንዲህ አይደለም፤ የኰረብታማው የኤፍሬሙ አገር ሰው፣ የቢክሪ ልጅ ሳቤዔ እጁን በንጉሡ በዳዊት ላይ አንሥቷል፤ እናንተ ይህን ሰው ብቻ ስጡኝ እንጂ እኔ ከተማዪቱን ትቼ እሄዳለሁ” አላት።

ሴቲቱም ኢዮአብን፣ “የሰውየው ራስ ተቈርጦ በግንቡ ላይ ይወረወርልሃል” አለችው።

22ከዚህም በኋላ ሴቲቱ ብልኅነት የተሞላበት ምክሯን ይዛ ወደ ሕዝቡ ሁሉ ሄደች፤ እነርሱም የቢክሪን ልጅ የሳቤዔን ራስ ቈርጠው ለኢዮአብ ወረወሩለት፤ ስለዚህ ኢዮአብ መለከቱን ነፋ፤ ሰዎቹም ከከተማዪቱ ርቀው በየአቅጣጫው ተበታተኑ፤ እያንዳንዳቸውም ወደየቤታቸው ሄዱ፤ ኢዮአብም ወደ ንጉሡ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።

23ኢዮአብ በእስራኤል ሰራዊት ሁሉ ላይ የበላይ ሆነ፤

የዮዳሄ ልጅ በናያስ ደግሞ በከሊታውያንና በፈሊያታውያን ላይ አለቃ ሆነ።

24አዶኒራም20፥24 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ቅጆች (እንዲሁም 1ነገ 4፥6 እና 5፥14 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ አይራም ይላል። በግዳጅ ሥራ ላይ ለተሰማሩት ሰዎች አለቃ ሆነ፤

የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ ደግሞ ታሪክ ጸሓፊ ሆነ፤

25ሱሳ ጸሓፊ፣

ሳዶቅና አብያታር ካህናት ነበሩ፤

26እንዲሁም የኢያዕር ሰው ዒራስ የዳዊት አማካሪ ነበር።

Thai New Contemporary Bible

2ซามูเอล 20:1-26

เชบากบฏ

1มีผู้ก่อความไม่สงบคนหนึ่งชื่อเชบาบุตรบิครีชาวเบนยามินเผอิญอยู่ที่นั่น เขาเป่าแตรเขาสัตว์และร้องตะโกนว่า

“เราไม่มีส่วนอะไรกับดาวิด

เราไม่เกี่ยวข้องอะไรกับบุตรเจสซี!

พี่น้องอิสราเอลทั้งหลายเอ๋ย จงกลับบ้านกันเถิด!”

2คนอิสราเอลทั้งปวงจึงทิ้งดาวิดไปติดตามเชบาบุตรบิครี แต่คนยูดาห์อยู่เคียงข้างกษัตริย์ของตน ตามเสด็จตลอดทางจากแม่น้ำจอร์แดนสู่กรุงเยรูซาเล็ม

3เมื่อดาวิดเสด็จมาถึงวังในเยรูซาเล็ม พระองค์ทรงกักตัวสนมทั้งสิบซึ่งทรงทิ้งไว้ให้คอยรักษาวังนั้นไว้ที่ตำหนักแห่งหนึ่ง และให้ได้รับการเลี้ยงดูตามความต้องการ แต่กษัตริย์ไม่ได้รับเป็นสนมอีกต่อไป นางสนมเหล่านั้นจึงถูกกักอยู่ในฐานะแม่ม่ายจนวันตาย

4จากนั้นกษัตริย์ตรัสสั่งอามาสาว่า “จงระดมพลยูดาห์มาที่นี่ภายในสามวัน แล้วตัวเจ้าก็จงมาด้วย” 5แต่เมื่ออามาสาออกไประดมพลยูดาห์ เขาใช้เวลาเกินกว่าที่กษัตริย์กำหนดไว้

6ดาวิดตรัสกับอาบีชัยว่า “เชบาบุตรบิครีจะเป็นภัยต่อเรายิ่งกว่าอับซาโลมเสียอีก จงนำคนของเราตามล่าเอาตัวเขามา ก่อนที่เขาจะหนีเข้าเมืองป้อมปราการพ้นมือเราไปได้” 7คนของโยอาบ คนเคเรธี และคนเปเลท กับนักรบแกล้วกล้าทั้งหลายจึงยกออกไปจากกรุงเยรูซาเล็มภายใต้การนำของอาบีชัยเพื่อตามล่าเชบาบุตรบิครี

8ขณะที่พวกเขามาถึงศิลาใหญ่แห่งกิเบโอน อามาสามาพบกับพวกเขาที่นั่น โยอาบแต่งชุดออกศึก คาดดาบสั้นพร้อมฝักไว้ที่เอว เขาก้าวเข้าไปทักทายอามาสาและแอบชักดาบสั้นออกจากฝัก

9โยอาบพูดว่า “เป็นอย่างไรบ้างน้องชาย?” แล้วใช้มือขวาจับหนวดของอามาสาทำท่าเหมือนจะจูบ 10อามาสาไม่ทันสังเกตดาบสั้นในมือโยอาบ โยอาบจึงแทงเข้าที่ท้องจนไส้ทะลักออกมาที่พื้น โดยไม่ต้องแทงซ้ำ อามาสาตายคาที่ แล้วโยอาบกับอาบีชัยน้องชายก็ตามล่าเชบาบุตรบิครีต่อไป

11ทหารคนหนึ่งของโยอาบยืนข้างร่างของอามาสาและกล่าวว่า “ผู้ใดชื่นชอบโยอาบและผู้ใดเป็นฝ่ายดาวิด จงตามโยอาบมา” 12ส่วนอามาสานอนจมกองเลือดอยู่กลางถนน และเมื่อทหารคนนั้นเห็นทหารทั้งหมดหยุดดูศพของอามาสา เขาจึงลากศพจากถนนไปทิ้งไว้กลางทุ่งและโยนเสื้อผ้าคลุมไว้ 13เมื่อกำจัดร่างของอามาสาออกไปให้พ้นทางแล้ว ทุกคนต่างก็สมทบกับโยอาบ ออกตามล่าเชบาบุตรบิครี

14ฝ่ายเชบาเดินทางไปทั่วทุกเผ่าของอิสราเอลไปยังอาเบลเบธมาอาคาห์20:14 หรืออาเบลจนถึงเบธมาอาคาห์เช่นเดียวกับข้อ 15 และทั่วภูมิภาคของชาวเบไรต์ซึ่งรวมตัวกันมาติดตามเขา 15กองกำลังของโยอาบมาโอบล้อมเชบาในอาเบลเบธมาอาคาห์ ก่อเชิงเทินใหญ่ต่อกับกำแพงเมือง แล้วเริ่มทลายกำแพง 16หญิงเจ้าปัญญาคนหนึ่งร้องบอกจากตัวเมืองว่า “โปรดฟังหน่อยเถิด เรียกท่านโยอาบมาทางนี้ ดิฉันขอพูดด้วย” 17เมื่อโยอาบมาถึง หญิงนั้นถามว่า “ท่านคือโยอาบหรือ?”

เขาตอบว่า “ใช่”

นางกล่าวว่า “โปรดฟังสิ่งที่ผู้รับใช้ของท่านจะพูด”

โยอาบตอบว่า “เราฟังอยู่”

18นางกล่าวต่อไปว่า “เคยมีคำกล่าวไว้ว่า ‘ไปเอาคำตอบกับอาเบล’ แล้วเรื่องก็เรียบร้อย 19เราเป็นพวกที่รักสันติและจงรักภักดีในอิสราเอล ท่านกำลังพยายามทำลายเมืองแม่ของอิสราเอล เหตุใดท่านจึงต้องการที่จะกลืนกินมรดกขององค์พระผู้เป็นเจ้า?”

20โยอาบตอบว่า “ขอให้เรื่องนี้ห่างไกลจากเรา! เราไม่เคยคิดที่จะกลืนกินหรือทำลายเมืองนี้เลย! 21เราต้องการแต่เพียงได้ตัวคนที่ชื่อเชบาบุตรบิครีจากแดนเทือกเขาแห่งเอฟราอิมซึ่งกบฏต่อกษัตริย์ดาวิด หากเจ้าเอาตัวชายคนนี้มาให้ เราก็จะถอนกำลังไปจากเมืองนี้”

หญิงนั้นตอบว่า “เราจะโยนหัวเขาข้ามกำแพงลงมาให้ท่าน”

22หญิงนั้นจึงไปหาพวกชาวเมือง และให้คำปรึกษาอย่างฉลาดหลักแหลม พวกเขาก็ตัดศีรษะเชบาบุตรบิครีโยนลงมาให้โยอาบ โยอาบจึงเป่าแตรเขาสัตว์เรียกกองทหารให้แยกย้ายจากเมืองนั้นกลับบ้าน ส่วนโยอาบกลับมาเข้าเฝ้ากษัตริย์ที่กรุงเยรูซาเล็ม

23โยอาบเป็นผู้บัญชาการกองทัพทั้งหมดของอิสราเอล เบไนยาห์บุตรเยโฮยาดาเป็นผู้บัญชาการ คนเคเรธีและคนเปเลท 24อาโดนีรัม20:24 ภาษาฮีบรูว่าอาโดรัม(ดู1พกษ.4:6 และ 5:14)เป็นผู้ดูแลคนงานโยธา เยโฮชาฟัทบุตรอาหิลูดเป็นอาลักษณ์หลวง 25เชวาเป็นราชเลขา ศาโดกกับอาบียาธาร์เป็นปุโรหิต 26และอิราแห่งยาอีร์เป็นปุโรหิตของดาวิด