2 ሳሙኤል 10 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 10:1-19

ዳዊት አሞናውያንን ድል አደረገ

10፥1-19 ተጓ ምብ – 1ዜና 19፥1-19

1ከዚህ በኋላ የአሞናውያን ንጉሥ ሞተ፤ ልጁ ሐኖንም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ። 2ዳዊትም፣ “አባቱ ቸርነትን እንዳደረገልኝ ሁሉ፣ እኔም ለናዖስ ልጅ ለሐኖን ወሮታውን ልክፈል” ሲል ዐሰበ። ስለዚህ ስለ አባቱ ሞት የተሰማውን ሐዘን እንዲገልጹለት ዳዊት መልክተኞችን ላከ።

የዳዊት ሰዎች ወደ አሞናውያን ምድር በደረሱ ጊዜ፣ 3የአሞናውያን መኳንንት ጌታቸውን ሐኖንን፣ “ዳዊት የተሰማውን ሐዘን ለመግለጽ ሰዎች መላኩ አባትህን ለማክበር አስቦ ይመስልሃል? የላካቸው ሰዎች ከተማዪቱን እንዲመረምሩ፣ እንዲሰልሉና እንዲያጠፏት አይደለምን?” አሉት። 4ስለዚህ ሐኖን የዳዊትን ሰዎች ይዞ፣ የእያንዳንዳቸውን ጢም በከፊል ላጨ፣ ልብሳቸውንም ወገባቸው ድረስ አሳጥሮ በመቍረጥ መልሶ ሰደዳቸው።

5ዳዊት ይህን በሰማ ጊዜ፣ ሰዎቹ እጅግ ዐፍረው ስለ ነበር መልክተኞቹን ላከባቸው፤ ንጉሡም፣ “ጢማችሁ እስኪያድግ በኢያሪኮ ቈዩና ከዚያ በኋላ ተመለሱ” አላቸው።

6አሞናውያን፣ ዳዊት እንደ ጠላቸው ባወቁ ጊዜ፣ ከቤትሮዖብና ከሱባ ሃያ ሺሕ ሶርያውያን እግረኛ ወታደሮችን እንዲሁም ንጉሥ መዓካን ከአንድ ሺሕ ሰዎቹ ጋር ደግሞም ከጦብ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ሰዎች ቀጠሩ።

7ዳዊት ይህን ሲሰማ፣ ኢዮአብን ከመላው ተዋጊ ሰራዊት ጋር ላከው። 8አሞናውያን ወጥተው በከተማቸው መግቢያ በር ላይ ተሰለፉ፤ የሱባና የረአብ ሶርያውያን እንዲሁም የጦብና የመዓካ ሰዎች ለብቻ ሜዳው ላይ ተሰለፉ።

9ኢዮአብም ከፊትና ከኋላው ጦር እንደ ከበበው ባየ ጊዜ፣ በእስራኤል ጀግንነታቸው ከታወቀው ጥቂቶቹን መርጦ በሶርያውያን ግንባር አሰለፋቸው። 10የቀሩትን ሰዎች ደግሞ በወንድሙ በአቢሳ ሥር መድቦ በአሞናውያን ግንባር አሰለፋቸው።

11ኢዮአብም እንዲህ አለ፤ ሶርያውያን የሚያይሉብኝ ከሆነ አንተ መጥተህ ትረዳኛለህ፤ አሞናውያን የሚያይሉብህ ከሆነ እኔ መጥቼ እረዳሃለሁ። 12እንግዲህ በርታ፤ ለሕዝባችንና ለአምላካችን ከተሞች በጀግንነት እንዋጋ፤ እግዚአብሔርም በፊቱ መልካም መስሎ የታየውን ያድርግ።

13ከዚያም ኢዮአብና አብሮት የነበረው ሰራዊት ሶርያውያንን ለመውጋት ወደ ፊት ገሠገሠ፤ ሶርያውያንም ከፊቱ ሸሹ። 14ሶርያውያን መሸሻቸውን አሞናውያን ባዩ ጊዜ፣ እነርሱም ከአቢሳ ፊት ሸሽተው ወደ ከተማዪቱ ውስጥ ገቡ። ስለዚህም ኢዮአብ አሞናውያንን መውጋቱን አቁሞ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።

15ሶርያውያን በእስራኤላውያን እንደ ተሸነፉ ባዩ ጊዜ፣ እንደ ገና ተሰባሰቡ። 16አድርአዛር መልክተኞችን ሰድዶ ከወንዙ10፥16 የኤፍራጥስ ወንዝ ነው። ማዶ ያሉትን ሶርያውያን አስመጣ፤ እነርሱም በአድርአዛር ሰራዊት አዛዥ በሶባክ መሪነት ወደ ኤላም ሄዱ።

17ዳዊት ይህን በሰማ ጊዜ፣ መላውን እስራኤልን ሰበሰበ፤ ከዚያም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ወደ ዔላም ሄደ። ሶርያውያንም ለጦርነት ተሰልፈው ዳዊትን በግንባር ገጠሙት፤ 18ይሁን እንጂ ከእስራኤል ፊት ሸሹ፤ ዳዊትም ሰባት መቶ ሠረገለኞችንና አርባ ሺሕ እግረኛ ወታደሮች10፥18 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም እንዲሁም (1ዜና 19፥18 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የዕብራይስጡ፣ ፈረሰኞች ይላል። ገደለባቸው። እንዲሁም የሰራዊታቸውን አዛዥ ሶባክን አቍስሎት ስለ ነበር፣ እዚያው ሞተ። 19በአድርአዛር ሥር የነበሩት ነገሥታት ሁሉ በእስራኤል መሸነፋቸውን ባዩ ጊዜ ከእስራኤላውያን ጋር ሰላም መሠረቱ፤ ተገዙላቸውም።

ስለዚህም ሶርያውያን ከዚያ በኋላ አሞናውያንን መርዳት ፈሩ።

New International Reader’s Version

2 Samuel 10:1-19

David Wins the Victory Over the Ammonites

1The king of Ammon died. His son Hanun became the next king after him. 2David thought, “I’m going to be kind to Hanun. His father Nahash was kind to me.” So David sent messengers to Hanun. He wanted them to tell Hanun how sad he was that Hanun’s father had died.

David’s messengers went to the land of Ammon. 3The Ammonite commanders spoke to their master Hanun. They said, “David has sent messengers to tell you he is sad. They say he wants to honor your father. But the real reason they’ve come is to look the city over. They want to destroy it.” 4So Hanun grabbed David’s messengers. He shaved off half of each man’s beard. He cut their clothes off just below the waist and left them half naked. Then he sent them away.

5David was told about it. So he sent messengers to his men because they were filled with shame. King David said to them, “Stay at Jericho until your beards grow out again. Then come back here.”

6The Ammonites realized that what they had done had made David very angry with them. So they hired 20,000 Aramean soldiers who were on foot. The soldiers came from Beth Rehob and Zobah. The Ammonites also hired the king of Maakah and 1,000 men. And they hired 12,000 men from Tob.

7David heard about it. So he sent Joab out with the entire army of Israel’s fighting men. 8The Ammonites marched out. They took up their battle positions at the entrance of their city gate. The Arameans of Zobah and Rehob gathered their troops together in the open country. So did the men of Tob and Maakah.

9Joab saw that there were lines of soldiers in front of him and behind him. So he chose some of the best troops in Israel. He sent them to march out against the Arameans. 10He put the rest of the men under the command of his brother Abishai. Joab sent them to march out against the Ammonites. 11He said, “Suppose the Arameans are too strong for me. Then you must come and help me. But suppose the Ammonites are too strong for you. Then I’ll come and help you. 12Be strong. Let’s be brave as we fight for our people and the cities of our God. The Lord will do what he thinks is best.”

13Then Joab and the troops with him marched out to attack the Arameans. They ran away from him. 14The Ammonites realized that the Arameans were running away. So they ran away from Abishai. They went inside the city. After Joab had fought against the Ammonites, he went back to Jerusalem.

15The Arameans saw that they had been driven away by Israel. So they brought their troops together. 16Hadadezer had some Arameans brought from east of the Euphrates River. They went to Helam under the command of Shobak. He was the commander of Hadadezer’s army.

17David was told about it. So he gathered the whole army of Israel together. They went across the Jordan River to Helam. The Arameans lined up their soldiers to go to war against David. They began to fight against him. 18But then they ran away from Israel. David killed 700 of their chariot riders. He killed 40,000 of their soldiers who were on foot. He also struck down Shobak, the commander of their army. Shobak died there. 19All the kings who were under the rule of Hadadezer saw that Israel had won the battle over them. So they made a peace treaty with the Israelites. They were brought under Israel’s rule.

After that, the Arameans were afraid to help the Ammonites anymore.