1 ጴጥሮስ 5 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ጴጥሮስ 5:1-14

ለሽማግሌዎችና ለጕልማሶች የተሰጠ ምክር

1እንግዲህ ከእነርሱ ጋር እኔም ሽማግሌና የክርስቶስ መከራ ምስክር የሆንሁ፣ እንዲሁም ወደ ፊት የሚገለጠው ክብር ተካፋይ የምሆን፣ በመካከላችሁ ያሉትን ሽማግሌዎች እመክራቸዋለሁ፤ 2በእናንተ ኀላፊነት ሥር ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ የምትጠብቁትም ከእግዚአብሔር እንደሚጠበቅባችሁ በግድ ሳይሆን በፈቃደኝነት፣ ለጥቅም በመስገብገብ ሳይሆን ለማገልገል ባላችሁ ጽኑ ፍላጎት ይሁን፤ 3እንዲሁም በዐደራ ለተሰጣችሁ መንጋ መልካም ምሳሌ በመሆን እንጂ በላያቸው በመሠልጠን አይሁን። 4የእረኞች አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማይጠፋውን አክሊል ትቀበላላችሁ።

5ጕልማሶች ሆይ፤ እናንተም እንዲሁ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርስ በመከባበር ትሕትናን ልበሱ፤ ምክንያቱም፣

“እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤

ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።”

6ስለዚህ እርሱ በወሰነው ጊዜ ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከእግዚአብሔር ብርቱ እጅ በታች ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ 7እርሱ ስለ እናንተ ስለሚያስብ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።

8ራሳችሁን የምትገዙ ሁኑ፣ ንቁም፤ ጠላታችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን በመፈለግ እንደሚያገሣ አንበሳ ወዲያ ወዲህ ይዞራልና። 9በዓለም ዙሪያ ያሉት ወንድሞቻችሁ ተመሳሳይ መከራ እንደሚቀበሉ ዐውቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት።

10በክርስቶስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ፣ ለጥቂት ጊዜ መከራ ከተቀበላችሁ በኋላ እርሱ ራሱ መልሶ ያበረታችኋል፤ አጽንቶም ያቆማችኋል። 11ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን፤ አሜን።

የስንብት ሰላምታ

12እንደ ታማኝ ወንድም በምቈጥረው በስልዋኑስ5፥12 ወይም ሲላስ አማካይነት ይህን ዐጭር መልእክት ጽፌላችኋለሁ፤ የጻፍሁላችሁም ልመክራችሁና ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን ልመሰክርላችሁ ብዬ ነው። በዚህ ጸጋ ጸንታችሁ ቁሙ።

13ከእናንተ ጋር የተመረጠችው፣ በባቢሎን የምትገኘው5፥13 በአንዳንድ ጥንታዊ ቅጆች ላይ በባቢሎን የምትገኘው ቤተ ክርስቲያን ይላሉ። ሰላምታ ታቀርብላችኋለች፤ እንዲሁም ልጄ ማርቆስ ሰላምታ ያቀርብላችኋል።

14በፍቅር አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።

በክርስቶስ ላላችሁ ለሁላችሁ ሰላም ይሁን።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

彼得前书 5:1-14

劝勉长老

1我是基督受苦的见证人,将分享以后所显明的荣耀。我以长老的身份劝你们中间做长老的: 2务要牧养上帝托付给你们的羊群,按着上帝的旨意甘心乐意地照顾他们,不是出于勉强,不是为了谋利,而是出于热诚。 3不要辖制托付给你们的羊群,而是要做群羊的榜样。 4等到大牧长显现的时候,你们必得到永不衰残的荣耀冠冕。

5你们年轻的要顺服年长的,大家都要存谦卑的心彼此服侍。因为上帝阻挡骄傲的人,恩待谦卑的人。 6所以你们要在上帝大能的手下谦卑,时候到了,祂必擢升你们。 7你们要把一切忧虑卸给上帝,因为祂眷顾你们。

8你们务要谨慎,警醒,因为你们的仇敌魔鬼好像咆哮的狮子四处游走,寻找可以吞吃的猎物。 9你们要以坚固的信心抵挡它,要知道世界各地的弟兄姊妹在遭受同样的苦难。 10你们忍受短暂的苦难之后,广施恩典、在基督里呼召你们享受祂永远荣耀的上帝必亲自复兴你们,使你们刚强、笃定、坚立。 11愿权能归给祂,直到永永远远。阿们!

问候

12在忠心的弟兄西拉的帮助下,我简单地写了这封信劝勉你们,并证明这是上帝真实的恩典。你们务要在这恩典上站稳。

13巴比伦和你们一同蒙拣选的教会问候你们,我的儿子马可也问候你们。 14你们要以爱心彼此亲吻问候。

愿平安归给你们所有在基督里的人!