1 ዜና መዋዕል 4 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 4:1-43

ሌሎቹ የይሁዳ ጐሣዎች

1የይሁዳ ዘሮች፤

ፋሬስ፣ ኤስሮም፣ ከርሚ፣ ሆር፣ ሦባል።

2የሦባል ልጅ ራያ ኢኤትን ወለደ፤ ኢኤት ደግሞ አሑማይንና ላሃድን ወለደ፤ እነዚህም የጾርዓውያን ጐሣዎች ናቸው።

3የኤጣም ወንዶች ልጆች4፥3 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ቅጆች (እንዲሁም ቩልጌት ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ አባት ይላል እነዚህ ናቸው፤

ኢይዝራኤል፣ ይሽማ፣ ይደባሽ። እኅታቸው ሃጽሌልፎኒ ትባላለች። 4ፋኑኤል ጌዶርን ወለደ፤ ኤጽር ደግሞ ሑሻምን ወለደ4፥4 ቃል በቃል ሲተረጐም አባት ሆነ ማለት ነው፤ ይህም ምናልባት፣ አባት ማለት፣ የጐሣው፣ እንዝላት፣ እንጅላት ወይም፣ መሠረት መሆኑን የሚያመለክት ነው። እነዚህ የኤፍራታ የበኵር ልጅና የቤተ ልሔም አባት የሆነው የሆር ዘሮች ናቸው።

5የቴቁሔ አባት አሽሑር፣ ሔላና ነዕራ የተባሉ ሁለት ሚስቶች ነበሩት።

6ነዕራም አሑዛምን፣ ኦፌርን፣ ቴምኒን፣ አሐሽታሪን ወለደችለት፤ የነዕራ ዘሮች እነዚህ ነበሩ።

7የሔላ ወንዶች ልጆች፤

ዴሬት፣ ይጽሐር፣ ኤትናን ናቸው። 8የቆጽ ወንዶች ልጆች ዓኑብ፣ ጾቤባና፣ የሃሩም ልጅ የአሐርሔል ጐሳዎች ናቸው።

9ያቤጽ ከወንድሞቹ ይልቅ የተከበረ ሰው ነበረ፤ እናቱም “በጣር የወለድሁት” ስትል ስሙን ያቤጽ አለችው። 10ያቤጽም፣ “አቤቱ፤ እንድትባርከኝ፣ ግዛቴንም እንድታሰፋልኝ እለምንሃለሁ፤ እጅህ ከእኔ ጋር ትሁን፤ ከሥቃይና ከጕዳትም ጠብቀኝ” በማለት ወደ እስራኤል አምላክ ጮኸ። እግዚአብሔርም የለመነውን ሰጠው።

11የሹሐ ወንድም ክሉብ ምሒርን ወለደ፤ ምሒርም ኤሽቶን ወለደ። 12ኤሽቶን ቤትራፋንና ፋሴሐን ወለደ፤ የዒር ናሐሽን ከተሞች የቈረቈረ እርሱ ነው4፥12 ወይም፣ የዒር ናሐሽ አባት ነው። እነዚህ የሬካ ሰዎች ናቸው።

13የቄኔዝ ወንዶች ልጆች፤

ጎቶንያል፣ ሠራያ።

የጎቶንያል ወንዶች ልጆች፤

ሐታት፣ መዖኖታይ4፥13 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የቩልጌት ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ መዖኖታይ የሚለውን አይጨምርም።14መዖኖታይ ደግሞ ዖፍራን ወለደ።

ሠራያ የኢዮአብ አባት ሲሆን፣ ኢዮአብ ጌሐራሺምን4፥14 ጌሐራሺም ማለት የእደ ጥበብ ሸለቆ ማለት ነው። ወለደ፤ የጥበበ እድ ባለሙያዎች ስለ ነበሩ ይህ ስም ተሰጣቸው።

15የዮፎኔ ልጅ የካሌብ ወንዶች ልጆች፤

ዒሩ፣ ኤላ፣ ነዓም።

የኤላ ልጅ፤

ቄኔዝ።

16የይሃሌልኤል ወንዶች ልጆች፤

ዚፍ፣ ዚፋ፣ ቲርያ፣ አሣርኤል።

17የዕዝራ ወንዶች ልጆች፤

ዬቴር፣ ሜሬድ፣ ዔፌር፣ ያሎን።

ከሜሬድ ሚስቶች አንዲቱ ማርያምን፣ ሸማይንና የኤሽትምዓን አባት ይሽባን ወለደች። 18አይሁዳዊት ሚስቱም የጌዶርን አባት ዮሬድን፣ የሦኮን አባት ሔቤርን፣ የዛኖዋን አባት ይቁቲኤልን ወለደች፤ እነዚህም ሜሬድ ያገባት የፈርዖን ልጅ የቢትያ ልጆች ናቸው።

19የሆዲያ ሚስት የነሐም እኅት ወንዶች ልጆች፤

የገርሚው የቅዒላ አባት፣ ማዕካታዊው ኤሽትሞዓ።

20የሺሞን ወንዶች ልጆች፤

አምኖን፣ ሪና፣ ቤንሐናን፣ ቲሎን። የይሺዒ ዘሮች፤ ዞሔትና ቤንዞሔት።

21የይሁዳ ልጅ የሴሎም ወንዶች ልጆች፤

የሌካ አባት ዔር፣ የመሪሳና በቤት አሽቤዓ የበፍታ ጨርቅ ሠሪ የሆኑት ጐሣዎች አባት ለዓዳ፣

22ዮቂም፣ የኮዜባ ሰዎች፣ ኢዮአስ፣ ሞዓብን የገዛ ሣራፍና ያሹቢሌሔም። ታሪካቸውም ጥንታዊነት ያለው ነው። 23ሰዎቹ በነጣዒምና በጋዴራ የሚቀመጡ ሸክላ ሠሪዎች ነበሩ፤ በዚያም በመቀመጥ ለንጉሡ ሸክላ ይሠሩ ነበር።

ስምዖን

4፥28-33 ተጓ ምብ – ኢያ 19፥2-10

24የስምዖን ዘሮች፤

ነሙኤል፣ ያሚን፣ ያሪን፣ ዛራ፣ ሳኡል፤

25ሰሎም የሳኡል ልጅ ነው፤ መብሳም የሰሎም ልጅ ነው፤

ማስማዕ ደግሞ የመብሳም ልጅ ነው።

26የማስማዕ ዘሮች፤

ልጁ ሃሙኤል፣ ልጁ ዘኩር፣ ልጁ ሰሜኢ።

27ሰሜኢ ዐሥራ ስድስት ወንዶችና ስድስት ሴቶች ልጆች ነበሩት፤ ወንድሞቹ ግን ብዙ ልጆች አልነበሯቸውም፤ ስለዚህ ጐሣቸው በሙሉ እንደ ይሁዳ ሕዝብ ብዙ አልነበረም። 28የኖሩባቸውም ቦታዎች እነዚህ ናቸው፦ ቤርሳቤህ፣ ሞላዳ፣ ሐጻርሹዓል፣ 29ቢልሃ፣ ዔጼም፣ ቶላድ፣ 30ቤቱኤል፣ ሔርማ፣ ጺቅላግ፣ 31ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሲም፣ ቤት ቢሪ፣ ሽዓራይም፤ እስከ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ድረስ የኖሩት በእነዚህ ከተሞች ነው። 32በአካባቢያቸው የሚገኙት መንደሮች ደግሞ ኤጣም፣ ዐይን፣ ሬሞን፣ ቶኬን፣ ዓሻን የተባሉ አምስት ከተሞች ናቸው፤ 33በእነዚህም ከተሞች ዙሪያ እስከ ባኣል የሚዘልቁ መንደሮች ነበሩ፤ መኖሪያቸው በዚሁ ሲሆን፣ የትውልድ መዝገብም አላቸው።

34ሞሾባብ፣ የምሌክ፣

የአሜስያስ ልጅ ኢዮስያስ፣ 35ኢዮኤል፣

የዮሺብያ ልጅ፣ የሠራያ ልጅ፣ የዓሢኤል ልጅ ኢዩ

36እንዲሁም ኤልዩዔናይ፣ ያዕቆባ፣ የሾሐያ፣

ዓሣያ፣ ዓዲዔል፣ ዩሲምኤል፣ በናያስ፣

37የሺፊ ልጅ ዚዛ፣ የአሎን ልጅ፣ የይዳያ ልጅ፣ የሺምሪ ልጅ፣ የሸማያ ልጅ።

38እነዚህ ስማቸው ከላይ የተዘረዘረው ሰዎች የየጐሣቸው መሪዎች ነበሩ፤ የየቤተ ሰባቸውም ብዛት እጅግ በጣም እየጨመረ ሄደ፤ 39እነርሱም ለከብቶቻቸው ግጦሽ ፍለጋ ከሸለቆው በስተ ምሥራቅ እስካለው እስከ ጌዶር መግቢያ ድረስ ዘልቀው ሄዱ። 40በዚያም ለምለምና ያማረ የግጦሽ ቦታ አገኙ፤ ምድሪቱም ሰፊ፣ ሰላምና ጸጥታ የሰፈነባት ነበረች። በቀድሞ ዘመን በዚህ ምድር ይኖሩ የነበሩት አንዳንድ የካም ዘሮች ናቸው።

41እነዚህ ስማቸው ከላይ የተዘረዘረው ወደዚህ ቦታ የመጡት በይሁዳ ንጉሥ በሕዝቅያስ ዘመን ነበረ፤ እነርሱም በድንኳኖቻቸው ውስጥ በነበሩት በካም ወገኖችና በምዑናውያን ላይ አደጋ በመጣል ፈጽመው አጠፏቸው4፥41 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል።፤ ይህም እስከ ዛሬ ድረስ በግልጽ ይታያል። ለመንጎቻቸው በቂ የግጦሽ ቦታ ስላገኙም፣ በዚያ መኖር ጀመሩ። 42ከእነዚሁ አምስት መቶ የሚሆኑ የስምዖን ወገኖች በይሽዒ ልጆች በፈላጥያ፣ በነዓርያ፣ በረፋያና በዑዝኤል ተመርተው የሴይርን ኰረብታማ አገር ወረሩ። 43አምልጠው የቀሩትን አማሌቃውያን ፈጅተው እስከ ዛሬ በዚያው ይኖራሉ።

New International Version – UK

1 Chronicles 4:1-43

Other clans of Judah

1The descendants of Judah:

Perez, Hezron, Karmi, Hur and Shobal.

2Reaiah son of Shobal was the father of Jahath, and Jahath the father of Ahumai and Lahad. These were the clans of the Zorathites.

3These were the sons4:3 Some Septuagint manuscripts (see also Vulgate); Hebrew father of Etam:

Jezreel, Ishma and Idbash. Their sister was named Hazzelelponi. 4Penuel was the father of Gedor, and Ezer the father of Hushah.

These were the descendants of Hur, the firstborn of Ephrathah and father4:4 Father may mean civic leader or military leader; also in verses 12, 14, 17, 18 and possibly elsewhere. of Bethlehem.

5Ashhur the father of Tekoa had two wives, Helah and Naarah.

6Naarah bore him Ahuzzam, Hepher, Temeni and Haahashtari. These were the descendants of Naarah.

7The sons of Helah:

Zereth, Zohar, Ethnan, 8and Koz, who was the father of Anub and Hazzobebah and of the clans of Aharhel son of Harum.

9Jabez was more honourable than his brothers. His mother had named him Jabez,4:9 Jabez sounds like the Hebrew for pain. saying, ‘I gave birth to him in pain.’ 10Jabez cried out to the God of Israel, ‘Oh, that you would bless me and enlarge my territory! Let your hand be with me, and keep me from harm so that I will be free from pain.’ And God granted his request.

11Kelub, Shuhah’s brother, was the father of Mehir, who was the father of Eshton. 12Eshton was the father of Beth Rapha, Paseah and Tehinnah the father of Ir Nahash.4:12 Or of the city of Nahash These were the men of Rekah.

13The sons of Kenaz:

Othniel and Seraiah.

The sons of Othniel:

Hathath and Meonothai.4:13 Some Septuagint manuscripts and Vulgate; Hebrew does not have and Meonothai. 14Meonothai was the father of Ophrah.

Seraiah was the father of Joab,

the father of Ge Harashim.4:14 Ge Harashim means valley of skilled workers. It was called this because its people were skilled workers.

15The sons of Caleb son of Jephunneh:

Iru, Elah and Naam.

The son of Elah:

Kenaz.

16The sons of Jehallelel:

Ziph, Ziphah, Tiria and Asarel.

17The sons of Ezrah:

Jether, Mered, Epher and Jalon.

One of Mered’s wives gave birth to Miriam, Shammai and Ishbah the father of Eshtemoa. 18These were the children of Pharaoh’s daughter Bithiah, whom Mered had married.

His wife from the tribe of Judah gave birth to Jered the father of Gedor, Heber the father of Soko, and Jekuthiel the father of Zanoah.

19The sons of Hodiah’s wife, the sister of Naham:

the father of Keilah the Garmite, and Eshtemoa the Maakathite.

20The sons of Shimon:

Amnon, Rinnah, Ben-Hanan and Tilon.

The descendants of Ishi:

Zoheth and Ben-Zoheth.

21The sons of Shelah son of Judah:

Er the father of Lekah, Laadah the father of Mareshah and the clans of the linen workers at Beth Ashbea,

22Jokim, the men of Kozeba, and Joash and Saraph, who ruled in Moab and Jashubi Lehem. (These records are from ancient times.) 23They were the potters who lived at Netaim and Gederah; they stayed there and worked for the king.

Simeon

24The descendants of Simeon:

Nemuel, Jamin, Jarib, Zerah and Shaul;

25Shallum was Shaul’s son, Mibsam his son and Mishma his son.

26The descendants of Mishma:

Hammuel his son, Zakkur his son and Shimei his son.

27Shimei had sixteen sons and six daughters, but his brothers did not have many children; so their entire clan did not become as numerous as the people of Judah. 28They lived in Beersheba, Moladah, Hazar Shual, 29Bilhah, Ezem, Tolad, 30Bethuel, Hormah, Ziklag, 31Beth Markaboth, Hazar Susim, Beth Biri and Shaaraim. These were their towns until the reign of David. 32Their surrounding villages were Etam, Ain, Rimmon, Token and Ashan – five towns – 33and all the villages around these towns as far as Baalath.4:33 Some Septuagint manuscripts (see also Joshua 19:8); Hebrew Baal These were their settlements.

And they kept a genealogical record:

34Meshobab; Jamlech;

Joshah son of Amaziah; 35Joel;

Jehu son of Joshibiah, the son of Seraiah, the son of Asiel;

36also Elioenai; Jaakobah; Jeshohaiah;

Asaiah; Adiel; Jesimiel; Benaiah;

37and Ziza son of Shiphi, the son of Allon, the son of Jedaiah, the son of Shimri, the son of Shemaiah.

38The men listed above by name were leaders of their clans.

Their families increased greatly, 39and they went to the outskirts of Gedor to the east of the valley in search of pasture for their flocks. 40They found rich, good pasture, and the land was spacious, peaceful and quiet. Some Hamites had lived there formerly.

41The men whose names were listed came in the days of Hezekiah king of Judah. They attacked the Hamites in their dwellings and also the Meunites who were there and completely destroyed4:41 The Hebrew term refers to the irrevocable giving over of things or persons to the Lord, often by totally destroying them. them, as is evident to this day. Then they settled in their place, because there was pasture for their flocks. 42And five hundred of these Simeonites, led by Pelatiah, Neariah, Rephaiah and Uzziel, the sons of Ishi, invaded the hill country of Seir. 43They killed the remaining Amalekites who had escaped, and they have lived there to this day.