1 ነገሥት 20 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 20:1-43

ቤን ሀዳድ ሰማርያን ወጋ

1በዚህ ጊዜ የሶርያ ንጉሥ ቤን ሀዳድ መላ ሰራዊቱን በአንድነት አሰባሰበ፤ ከእርሱም ጋር ሠላሳ ሁለት ነገሥታት ከነፈረሶቻቸውና ከነሠረገሎቻቸው አብረውት ነበሩ፤ ወጥቶም ሰማርያን ከብቦ ወጋት። 2ወደ ከተማዪቱም መልእክተኞች በመላክ የእስራኤልን ንጉሥ አክዓብን እንዲህ አለው፤ “ቤን ሀዳድ እንዲህ ይላል፤ 3‘ብርና ወርቅህ የእኔ ነው፤ የሚያማምሩት ሚስቶችህና ልጆችህም የእኔ ናቸው።’ ”

4የእስራኤልም ንጉሥ፣ “ንጉሥ ጌታዬ ሆይ፤ ልክ እንዳልኸው ነው፤ እኔም ሆንሁ የእኔ የሆነው ሁሉ የአንተ ነው” ሲል መለሰለት።

5መልክተኞቹም እንደ ገና መጥተው እንዲህ አሉት፤ “ቤን ሀዳድ የሚለው ይህ ነው፤ ‘ብርህንና ወርቅህን፣ ሚስቶችህንና ልጆችህን እንድትሰጠኝ ልኬብህ ነበር፤ 6ሆኖም ነገ በዚሁ ጊዜ ቤተ መንግሥትህንና የሹማምትህን ቤቶች እንዲበረብሩ፣ ሹማምቴን እልካቸዋለሁ። እነርሱም ማናቸውንም ለአንተ ዋጋ ያለውን ሁሉ በእጃቸው በማስገባት ይወስዱታል።’ ”

7የእስራኤልም ንጉሥ የአገሩን ሽማግሌዎች ሁሉ ጠርቶ፣ “ይህ ሰው እንዴት ጠብ እንደሚፈልግ ታያላችሁ፤ ሚስቶቼንና ልጆቼን፣ ብሬንና ወርቄን እንዳስረክበው በጠየቀኝ ጊዜ አልከለከልሁትም” አላቸው።

8ሽማግሌዎቹና ሕዝቡም ሁሉ፣ “የሚልህን አትቀበለው፤ የጠየቀህንም እሺ አትበለው” አሉት።

9ስለዚህ ለቤን ሀዳድ መልእክተኞች፣ “ለጌታዬ ለንጉሡ፣ ‘እኔ ባሪያህ በመጀመሪያ ያልኸኝን ሁሉ አደርጋለሁ፤ ያሁኑን ጥያቄህን ግን ልፈጽመው አልችልም’ ብላችሁ ንገሩት” አላቸው። መልእክተኞቹም ይህንኑ ይዘው ተመለሱ።

10ከዚያም ቤን ሀዳድ፣ “ለሚከተለኝ ሰው ሁሉ የሰማርያ ዐፈር አንዳንድ ዕፍኝ የሚዳረስ ሳይሆን ቢቀር፣ አማልክት ይህን ያድርጉብኝ፤ ከዚህ የባሰም ያምጡብኝ” ሲል ሌሎች መልክተኞችን ወደ አክዓብ ላከ።

11የእስራኤልም ንጉሥ፣ “ ‘ታጥቆ ለጦርነት የሚወጣ ሰው የጦር ትጥቁን እንደ ፈታ ሰው መደንፋት የለበትም’ ብላችሁ ንገሩት” አላቸው።

12ቤን ሀዳድ ይህን መልእክት የሰማው አብረውት የነበሩት ነገሥታት በድንኳኖቻቸው20፥12 ወይም ሱኮት በ16 ላይም እንደዚሁ፤ ውስጥ ሆነው በሚጠጡበት ጊዜ ነበር፤ ቤን ሀዳድ ሰዎቹን፣ “በሉ ለጦርነት ተዘጋጁ” አላቸው፤ ስለዚህ ከተማዪቱን ለመውጋት ተዘጋጁ።

አክዓብ ቤን ሀዳድን ድል አደረገ

13በዚያን ጊዜ አንድ ነቢይ ወደ እስራኤል ንጉሥ ወደ አክዓብ መጥቶ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ይህን ብዙ ሰራዊት ታያለህን? ዛሬ በእጅህ አሳልፌ እሰጥሃለሁ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ታውቃለህ’ ” አለው።

14አክዓብም፣ “ይህን የሚያደርገው ማን ነው?” ሲል ጠየቀ።

ነቢዩም፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ይህን የሚያደርጉት የየአውራጃው አዛዥ የሆኑ ወጣት መኰንኖች ናቸው’ ” አለው።

“ታዲያ ጦርነቱን የሚጀምረው ማን ነው?” ሲል ጠየቀ።

ነቢዩም፣ “አንተው ትጀምራለህ” ብሎ መለሰ።

15ስለዚህ አክዓብ የየአውራጃው አዛዥ የሆኑትን ሁለት መቶ ሠላሳ ሁለት ወጣት መኰንኖች ጠራ፤ ከዚያም የቀሩትን እስራኤላውያን ሰበሰበ፤ እነዚህም በአጠቃላይ ሰባት ሺሕ ነበሩ። 16እነርሱም ቤን ሀዳድና ከእርሱ ጋር ተባብረው የነበሩት ሠላሳ ሁለቱ ነገሥታት በድንኳኖቻቸው ውስጥ ሰክረው ሳለ እኩለ ቀን ላይ መጡ። 17በግንባር ቀደምትነት የወጡት ግን፣ የየአውራጃው አዛዥ የሆኑት ወጣት መኰንኖች ነበሩ።

በዚህ ጊዜ ቤን ሀዳድ ሰላዮች ልኮ ነበርና እነርሱም፣ “ሰዎች ከሰማርያ ወጥተው ወደዚህ በመምጣት ላይ ናቸው” ብለው ነገሩት።

18እርሱም፣ “አመጣጣቸው ለሰላምም ይሁን ለጦርነት ከነሕይወታቸው ይዛችሁ አምጧቸው” አለ።

19የየአውራጃው አዛዥ የሆኑ ወጣት መኰንኖችም ሰራዊቱን አስከትለው ከከተማዪቱ ወጡ፤ 20እያንዳንዱም በፊቱ የገጠመውን ጠላት ገደለ፤ ሶርያውያን ሸሹ፤ እስራኤላውያንም ያሳድዷቸው ጀመር። የሶርያ ንጉሥ ቤን ሀዳድ ግን በፈረሱ ላይ ሆኖ ከጥቂት ፈረሰኞቹ ጋር አመለጠ። 21የእስራኤል ንጉሥ አክዓብም ወደ ፊት በመግፋት ፈረሶችንና ሠረገሎችን ማረከ፤ በሶርያውያንም ላይ ከባድ ጕዳት አደረሰባቸው።

22ከዚያም በኋላ ነቢዩ ወደ እስራኤል ንጉሥ መጥቶ፣ “በሚመጣው የጸደይ ወራት የሶርያ ንጉሥ ተመልሶ ይመጣብሃልና በርታ፤ ምን ማድረግ እንዳለብህም ዕወቅ” አለው።

23በዚያኑ ጊዜም የሶርያ ንጉሥ ሹማምት እንዲህ ሲሉ መከሩት፤ “አማልክታቸው የኰረብታ አማልክት ናቸው፤ ያየሉብንም ከዚህ የተነሣ ነው። በሜዳ ላይ ብንገጥማቸው ግን እኛ እንደምናይልባቸው አያጠራጥርም። 24እንግዲህ እንዲህ አድርግ፤ ነገሥታቱን በሙሉ ከአዛዥነታቸው አስነሣ፤ በቦታቸውም ሌሎች ሹማምት አድርግ። 25ከእስራኤል ጋር በሜዳው ላይ እንዲጋጠም በፈረሱ ፈንታ ፈረስ፣ በሠረገላው ፈንታ ሠረገላ በመተካት፣ እንደ ተደመሰሰው ያለ ሰራዊት አቋቁም፤ ከዚያ በኋላ ከእነርሱ ይበልጥ እኛ እንደምንበረታ አያጠራጥርም።” ንጉሡም ባቀረቡት ሐሳብ ተስማማ፤ እንዳሉትም አደረገ።

26በተከታዩም የጸደይ ወራት ቤን ሀዳድ ሶርያውያንን አሰባስቦ እስራኤልን ለመውጋት ወደ አፌቅ ወጣ። 27እስራኤላውያንም እንደዚሁ ተሰብስበው ስንቅ ከተሰጣቸው በኋላ ሊገጥሟቸው ተሰልፈው ወጡ። ሶርያውያን አገር ምድሩን ሞልተውት ሳለ፣ እስራኤላውያን ግን እንደ ሁለት ትንንሽ የፍየል መንጋ ሆነው ከፊት ለፊታቸው ሰፈሩ።

28የእግዚአብሔርም ሰው ወጥቶ ለእስራኤል ንጉሥ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሶርያውያን እግዚአብሔር የኰረብታ እንጂ የሸለቆ አምላክ አይደለም ብለዋልና ይህን ስፍር ቍጥር የሌለው ሰራዊት በእጅህ አሳልፌ እሰጥሃለሁ፤ አንተም እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ታውቃለህ’ ” አለው።

29በየሰፈሩበትም ቦታ ሰባት ቀን ከተፋጠጡ በኋላ በሰባተኛው ቀን ጦርነት ገጠሙ። እስራኤላውያንም በአንዲት ጀምበር ከሶርያውያን ሰራዊት መቶ ሺሕ እግረኛ ገደሉ። 30የቀሩት ወደ አፌቅ ከተማ ሸሹ፤ በዚያም በሃያ ሰባቱ ሺሕ ላይ ቅጥሩ ተንዶ ወደቀባቸው። ቤን ሃዳድም ወደ ከተማዪቱ ሸሽቶ በመሄድ ወደ አንዲት እልፍኝ ገብቶ ተደበቀ።

31ሹማምቱም፣ “የእስራኤል ቤት ነገሥታት መሓሪዎች መሆናቸውን ሰምተናል፤ አሁንም እንነሣና በወገባችን ላይ ማቅ ታጥቀን፣ በራሳችን ላይ ገመድ ጠምጥመን ወደ እስራኤል ንጉሥ እንሂድ፤ ምናልባትም ሕይወትህን ያተርፋት ይሆናል” አሉት።

32እነርሱም በወገባቸው ላይ ማቅ ታጥቀው፣ በራሳቸው ላይ ገመድ ጠምጥመው ወደ እስራኤል ንጉሥ በመሄድ፣ “አገልጋይህ ቤን ሀዳድ፣ ‘እባክህ በሕይወት እንድኖር ፍቀድልኝ’ ብሎ ይለምንሃል” አሉት።

ንጉሡም፣ “እስካሁን በሕይወት አለን? ወንድሜ እኮ ነው” አለ።

33ሰዎቹም ይህን በደግ በመተርጐም ቃሉን ከአፉ ቀበል አድርገው፤ “አዎን ቤን ሀዳድ ወንድምህ ነው” አሉት።

ንጉሡም፣ “በሉ ሂዱና አምጡት” አላቸው፤ ቤን ሃዳድም በመጣ ጊዜ፣ አክዓብ ሠረገላው ላይ እንዲወጣ አደረገው።

34ቤን ሃዳድም፣ “አባቴ ከአባትህ የወሰዳቸውን ከተሞች እመልሳለሁ፤ አባቴ በሰማርያ እንዳደረገው ሁሉ፣ አንተም በደማስቆ የራስህን ገበያ ማቋቋም ትችላለህ” አለው።

አክዓብም፣ “እንግዲያውስ ስምምነት አድርገን በነጻ እለቅቅሃለሁ” አለው፤ ስለዚህም ከእርሱ ጋር የውል ስምምነት አድርጎ ለቀቀው።

አንድ ነቢይ በአክዓብ ላይ ፈረደ

35ከነቢያት ልጆች አንዱ ጓደኛውን በእግዚአብሔር ቃል ታዞ፣ “ምታኝ” አለው፤ ሰውየው ግን ፈቃደኛ አልሆነም።

36ስለዚህም ነቢዩ፣ “ለእግዚአብሔር ባለ መታዘዝህ፣ ከእኔ ተለይተህ እንደ ሄድህ አንበሳ ይገድልሃል” አለው። ሰውየው ከሄደ በኋላ አንበሳ አግኝቶ ገደለው።

37ነቢዩም ሌላ ሰው አግኝቶ፣ “እባክህ ምታኝ” አለው። ስለዚህ ያ ሰው መትቶ አቈሰለው። 38ከዚያም ነቢዩ ሄዶ ከመንገድ ዳር በመቆም፣ ንጉሡን ይጠባበቅ ጀመር። የራሱን መጠምጠሚያ ወደ ታች አውርዶ ዐይኖቹን በመሸፈንም፣ ማንነቱ እንዳይታወቅ አደረገ። 39ንጉሡ በዚያ በሚያልፍበትም ጊዜ፣ ነቢዩ ጠርቶት እንዲህ አለው፤ “እኔ አገልጋይህ በተፋፋመው ጦርነት መካከል ገብቼ ሳለሁ፣ አንድ ሰው ምርኮኛ ይዞ መጥቶ ‘ይህን ሰው ጠብቅ፤ ቢያመልጥ በገመዱ ትገባለህ ወይም አንድ መክሊት20፥39 34 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር ትከፍላለህ’ አለኝ። 40‘ታዲያ እኔ አገልጋይህ ሥራ በዝቶብኝ ወዲያ ወዲህ ስል ሰውየው አምልጦ ሄደ።’ ”

የእስራኤልም ንጉሥ፣ “ራስህ ፈርደሃል፤ ይኸው ይፈጸምብሃል” አለው።

41ከዚያም ነቢዩ መጠምጠሚያውን በፍጥነት ከዐይኑ ላይ አነሣ፤ የእስራኤልም ንጉሥ ያ ሰው ከነቢያት አንዱ መሆኑን ዐወቀ። 42ነቢዩም ንጉሡን አለው፤ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ፈጽሞ ይገደል20፥42 የዕብራይስጡ ቃል ሰውን ወይም ቍስን ፈጽሞ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠት የሚለውን ያመለክታል። ያልሁትን ሰው ለቅቀኸዋልና በገመዱ ትገባለህ፤ በሕዝቡም ፈንታ ያንተ ሕዝብ በገመዱ ይገባል።’ ” 43የእስራኤልም ንጉሥ ተበሳጭቶና ተቈጥቶ ሰማርያ ወዳለው ቤተ መንግሥቱ ሄደ።

Persian Contemporary Bible

اول پادشاهان 20:1-43

بنهدد به سامره حمله می‌كند

1در اين هنگام بنهدد، پادشاه سوريه، لشكر خود را بسيج كرد و با سی و دو پادشاه ديگر متحد شده به كمک عرابه‌های جنگی و سواره نظام آنها سامره، پايتخت اسرائيل را محاصره كرد. 2‏-3سپس اين پيغام را برای اخاب، پادشاه اسرائيل به شهر فرستاد: «بنهدد پادشاه از تو می‌خواهد كه هر چه طلا و نقره داری با بهترين زنان و فرزندانت برای او بفرستی.»

4اخاب جواب داد: «بسيار خوب قربان، من با هر چه دارم، در اختيار شما هستم.»

5طولی نكشيد كه قاصدان بنهدد با پيغامی ديگر برگشتند و به اخاب گفتند: «بنهدد پادشاه دستور می‌دهد كه نه فقط بايد تمام طلا و نقره و زنان و فرزندانت را به من بدهی، 6بلكه فردا در همين وقت مأموران خود را می‌فرستم تا كاخ سلطنتی تو و خانه‌های افراد تو را جستجو كنند و هر چه بخواهند بردارند.»

7اخاب بزرگان اسرائيل را احضار كرد و گفت: «ببينيد بنهدد چه می‌خواهد! با اينكه قبلاً به او گفته‌ام كه حاضرم زنان و فرزندان و تمام موجودی طلا و نقرهٔ خود را به او بدهم، ولی او باز ما را در تنگنا گذاشته است.»

8بزرگان قوم، همگی به اخاب گفتند: «درخواستش را قبول نكن.»

9پس اخاب به فرستادگان بنهدد گفت: «به آقايم پادشاه سوريه بگوييد كه هر چه را بار اول خواسته است، حاضرم به او بدهم، ولی درخواست دومش را قبول نمی‌كنم.» قاصدان برگشتند و جواب اخاب را به بنهدد دادند.

10آنگاه بنهدد، پادشاه سوريه برای اخاب چنين پيغام فرستاد: «اگر شهر سامره را با خاک يكسان نكنم، خدايان همان بلا را به سر من بياورند كه من می‌خواهم به سر تو بياورم.»

11پادشاه اسرائيل به او جواب داد: «خواهيم ديد در جنگ چه كسی پيروز می‌شود!»

12جواب اخاب وقتی به بنهدد رسيد كه او با پادشاهان ديگر در خيمه‌های خود ميگساری می‌كردند. بنهدد به فرماندهان خود دستور داد كه آمادهٔ حمله شوند. پس در برابر شهر صف‌آرايی نمودند.

اخاب بنهدد را شكست می‌دهد

13در همين وقت يک نبی نزد اخاب پادشاه رفت و اين پيغام را از جانب خداوند به او رسانيد: «آيا اين قوای بزرگ دشمن را می‌بينی؟ من همين امروز همهٔ آنان را به تو تسليم می‌كنم تا بدانی كه من خداوند هستم!»

14اخاب پرسيد: «خداوند اين كار را چگونه انجام می‌دهد؟»

نبی جواب داد: «خداوند می‌فرمايد كه بوسيلهٔ فرماندهانی كه زير دست حاكمان اسرائيل هستند اين كار را انجام خواهد داد.»

اخاب پرسيد: «چه كسی اول بايد جنگ را شروع كند؟»

نبی جواب داد: «خودت.»

15پس اخاب فرماندهان را كه دويست و سی و دو نفر بودند احضار كرد و سپاه هفت هزار نفری خود را سان ديد. 16‏-17نزديک ظهر، در حالی که بنهدد و سی و دو پادشاه همراه او هنوز در خيمه‌ها سرگرم باده‌نوشی بودند فرماندهان اسرائيل از پايتخت خارج شدند.

ديده‌بانان بنهدد به او خبر دادند و گفتند: «عده‌ای سرباز از سامره بيرون آمده‌اند.»

18بنهدد دستور داد: «خواه برای صلح آمده باشند خواه برای جنگ، آنها را زنده دستگير كنيد.»

19‏-20در اين هنگام سربازان اسرائيلی به دنبال فرماندهانشان از شهر خارج شده، به دشمن حمله كردند و به كشتن آنها پرداختند. سربازان سوريه پا به فرار گذاشتند و اسرائیلی‌ها آنها را تعقيب كردند، ولی بنهدد سوار بر اسب شده، همراه چند سوار ديگر از دست اسرائیلی‌ها فرار كرد. 21در اين جنگ تلفات سنگينی به لشكر سوريه وارد آمد و تمام عرابه‌ها و اسبان ايشان به دست اخاب افتاد.

22پس از اين پيروزی، آن نبی باز نزد اخاب آمد و گفت: «سپاه خود را دوباره برای جنگ آماده كن زيرا سال ديگر پادشاه سوريه باز به تو حمله خواهد كرد.»

23مقامات سوری به بنهدد گفتند: «خدايان اسرائيلی خدايان کوهها هستند و به همين علت اسرائیلی‌ها پيروز شدند. ولی ما می‌توانيم در دشتهای هموار، آنها را به آسانی شكست بدهيم. 24اين بار فرماندهی جنگ را به جای آن سی و دو پادشاه، به سرداران بسپار. 25سپاه ديگری به جای سپاه از دست رفته فراهم‌آور و به تعداد قبلی اسب و عرابه آماده كن تا در دشتهای هموار با آنها بجنگيم. بدون شک آنان را شكست خواهيم داد.» بنهدد، پادشاه سوريه طبق پيشنهاد آنان عمل كرد. 26او در آغاز سال جديد، لشكر سوريه را بسيج كرد و باز به جنگ اسرائيل رفت. ولی اين بار دشت افيق را برای جنگ انتخاب كرد. 27اسرائيل هم سپاه خود را بسيج كرده، به ميدان جنگ فرستاد. اسرائيلی‌ها در برابر سپاه بزرگ سوريه كه سراسر آن دشت را پر كرده بود، مثل دو گله كوچک بزغاله به نظر می‌رسيدند.

28باز همان نبی با پيام خداوند نزد اخاب، پادشاه اسرائيل آمد و چنين گفت: «چون سوريها می‌گويند: خداوند شما، خدای كوههاست نه خدای دشتها، بنابراين، من بار ديگر تو را ياری می‌كنم اين سپاه بزرگ دشمن را شكست دهی تا بدانيد كه من خداوند هستم!»

29نيروهای دو طرف هفت روز در برابر هم اردو زدند و در روز هفتم جنگ را شروع كردند. قوم اسرائيل در همان روز اول جنگ تعداد صد هزار سرباز پيادهٔ دشمن را كشتند. 30بقيهٔ سربازان سوريه به شهر افيق گريختند. ولی در آنجا حصار شهر به روی آنها افتاد و بيست و هفت هزار سرباز ديگر نيز هلاک شدند. ولی بنهدد توانست به داخل شهر فرار كند و در اتاق خانه‌ای پنهان شود.

31افراد بنهدد به او گفتند: «ما شنيده‌ايم كه پادشاهان اسرائيل بسيار باگذشت و مهربان هستند. پس اجازه بده پلاس بر كمر و ريسمانها به دور گردن ببنديم و نزد اخاب، پادشاه اسرائيل برويم تا شايد از كشتن تو چشم‌پوشی كند.»

32پس پلاس بر كمر و ريسمان به دور گردن بستند و نزد اخاب، پادشاه اسرائيل رفتند و به او گفتند: «بندهٔ تو بنهدد تقاضا می‌كند كه او را نكشيد.»

اخاب، پادشاه اسرائيل جواب داد: «مگر او هنوز زنده است؟ او برادر من است!»

33افراد بنهدد اين را به فال نيک گرفتند و گفتند: «بلی، بنهدد برادر شماست!»

پادشاه اسرائيل به ايشان گفت: «برويد او را بياوريد.» وقتی بنهدد پيش اخاب آمد، اخاب او را سوار عرابهٔ مخصوص خود كرد.

34بنهدد به او گفت: «شهرهايی را كه پدر من از پدرت گرفته به تو پس می‌دهم. تو هم می‌توانی در دمشق برای خود مراكز تجارت ايجاد كنی، همانطور كه پدرم اين كار را در سامره كرد.» اخاب اين پيشنهاد را پذيرفت و با بنهدد پيمان بست و او را رها كرد.

پيشگويی مرگ اخاب

35روزی يكی از انبيا به فرمان خداوند به دوستش گفت: «با شمشير ضربه‌ای به من بزن!» ولی آن مرد اين كار را نكرد. 36پس آن نبی به او گفت: «چون دستور خداوند را اطاعت نكردی، وقتی از اينجا بروی، شيری تو را خواهد دريد.» و همينطور هم شد.

37بعد آن نبی به يک نفر ديگر گفت: «ضربه‌ای به من بزن!» آن مرد ضربه‌ای به او زد و مجروحش كرد. 38سپس آن نبی با دستمالی صورتش را پوشاند تا شناخته نشود و سر راه پادشاه منتظر ايستاد. 39وقتی اخاب پادشاه رسيد، آن نبی او را صدا زد و گفت: «ای پادشاه، من در ميدان جنگ بودم كه سربازی، اسيری را پيش من آورد و گفت: مواظب اين مرد باش. اگر فرار كرد يا بايد هفتاد و چهار كيلو نقره بدهی يا كشته خواهی شد. 40وقتی سرگرم كارهايم بودم، آن اسير فرار كرد.»

پادشاه گفت: «تو مقصری و خودت مجازات خود را تعيين كردی.»

41آنگاه آن نبی دستمال را از صورتش برداشت و پادشاه او را شناخت كه يكی از انبياست. 42او به پادشاه گفت: «خداوند می‌فرمايد: چون بنهدد را كه من می‌خواستم هلاک شود آزاد كردی، بايد خودت به جای او كشته شوی و افراد تو به جای افراد او نابود شوند.»

43پس اخاب غمگين و ناراحت به كاخ سلطنتی خود كه در شهر سامره بود، بازگشت.