1 ቆሮንቶስ 16 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 16:1-24

ለቅዱሳን የተደረገ የገንዘብ መዋጮ

1አሁን ደግሞ ለቅዱሳን ስለሚደረገው ገንዘብ ማሰባሰብ፤ ለገላትያ አብያተ ክርስቲያናት በሰጠሁት ትእዛዝ መሠረት አድርጉ። 2ገንዘብ ማሰባሰብ የሚደረገው እኔ በምመጣበት ጊዜ እንዳይሆን፣ ከእናንተ እያንዳንዱ እንደ ገቢው መጠን በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን እየለየ ያስቀምጥ። 3በምመጣበት ጊዜ እናንተ ለመረጣችኋቸው ሰዎች የመሸኛ ደብዳቤ ሰጥቼ ስጦታችሁን ወደ ኢየሩሳሌም እንዲያደርሱ እልካቸዋለሁ። 4የእኔ መሄድ የሚያስፈልግ ከሆነ አብረውኝ ይሄዳሉ።

የሐዋርያው ዕቅድ

5በመቄዶንያ በኩል ማለፌ ስለማይቀር፣ መቄዶንያ ከደረስሁ በኋላ ወደ እናንተ እመጣለሁ። 6ወደምሄድበት ወደ ማናቸውም ስፍራ በጕዞዬ እንድትረዱኝ፣ እናንተ ዘንድ እቈይ ይሆናል፤ ምናልባትም ክረምቱን ከእናንተ ጋር እሰነብት ይሆናል። 7አሁን እግረ መንገዴን ሳልፍ ልጐበኛችሁ አልፈልግም፤ ጌታ ቢፈቅድ ረዘም ላለ ጊዜ እናንተ ዘንድ ለመሰንበት ተስፋ አደርጋለሁ። 8ነገር ግን እስከ በዓለ አምሳ በኤፌሶን እቈያለሁ፤ 9ምክንያቱም ታላቅ የሥራ በር ተከፍቶልኛል፤ ብዙ ተቃዋሚዎችም አሉብኝ።

10ጢሞቴዎስ ወደ እናንተ ከመጣ፣ አብሯችሁ ያለ ፍርሀት እንዲቀመጥ አድርጉ፤ እርሱም እንደ እኔ የጌታን ሥራ የሚሠራ ነውና። 11ስለዚህ ማንም አይናቀው፤ በሰላም ወደ እኔ እንዲመለስ ርዱት፤ መመለሱንም ከወንድሞች ጋር እየጠበቅን ነው።

12ስለ ወንድማችን ስለ አጵሎስ ደግሞ፣ ከወንድሞች ጋር ወደ እናንተ እንዲመጣ አጥብቄ ለምኜው ነበር፤ እርሱ ግን አሁን ለመምጣት አልፈለገም፤ ሲመቸው ግን ይመጣል።

13ንቁ፤ በእምነት ጽኑ፤ በርቱ፤ ጠንክሩ፤ 14የምታደርጉትን ሁሉ በፍቅር አድርጉ።

15የእስጢፋኖስ ቤተ ሰዎች በአካይያ የመጀመሪያዎቹ አማኞች እንደ ሆኑና ቅዱሳንንም ለማገልገል ራሳቸውን እንደ ሰጡ ታውቃላችሁ። ወንድሞች ሆይ፤ ይህን እለምናችኋለሁ፤ 16እንደ እነርሱ ላሉትና ከእነርሱም ጋር በአገልግሎት ለሚደክሙ ሁሉ ታዘዙ።

17እስጢፋኖስ፣ ፈርዶናጥስና አካይቆስ በመምጣታቸው ደስ ብሎኛል፤ ምክንያቱም እናንተ እዚህ ባለመኖራችሁ የጐደለኝን አሟልተዋል፤ 18የእኔንም የእናንተንም መንፈስ አሳርፈዋልና። ስለዚህ እንደነዚህ ያሉት ሰዎች መታወቅ ይገባቸዋል።

የመሰናበቻ ቃል

19በእስያ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

አቂላና ጵርስቅላ16፥19 በግሪኩ ጵርስቃየጵርስቅላ ሌላው አጠራር ነው።፣ በቤታቸውም ያለችው ቤተ ክርስቲያን የከበረ ሰላምታ በጌታ ያቀርቡላችኋል።

20ወንድሞች ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

እርስ በርሳችሁ በተቀደሰ አሳሳም ሰላምታ ተሰጣጡ።

21ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ የጻፍሁላችሁ እኔ ጳውሎስ ነኝ።

22ጌታን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን። ጌታ ሆይ፤ ና!16፥22 በአራማይክ ጌታ ሆይ፤ ና ማለት ማራናታ ማለት ነው።

23የጌታ ኢየሱስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።

24ፍቅሬ በክርስቶስ ኢየሱስ ከሁላችሁ ጋር ነው፤ አሜን።16፥24 አንዳንድ ቅጆች አሜን የሚለው የላቸውም።

Het Boek

1 Korinthiërs 16:1-24

Laatste richtlijnen

1Volg voor de collecte voor de arme gelovigen de richtlijnen die ik de gemeenten van Galatië heb gegeven. 2Die komen hierop neer, dat ieder van u elke zondag iets opzij moet leggen van wat hij heeft verdiend. Bewaar het tot ik bij u kom. 3Dan ligt het geld tenminste klaar en kan ik de mannen die u daarvoor aanwijst, deze gift naar Jeruzalem laten brengen. Ik zal hun enkele aanbevelingsbrieven meegeven, 4maar het kan ook zijn dat ik het de moeite waard vind zélf met hen mee te gaan. 5Nadat ik in Macedonië ben geweest, kom ik bij u. Want ik wil eerst naar Macedonië gaan 6en daarna een tijdje bij u blijven, misschien wel de hele winter. In dat geval kunt u mij meegeven wat ik voor mijn volgende reis nodig heb, al weet ik nu nog niet waar ik naar toe zal gaan. 7Deze keer wil ik niet alleen maar even bij u aankomen. Ik zou graag wat langer blijven als de Here het goed vindt. 8Ik blijf echter nog tot Pinksteren in Efeze, 9want hier liggen geweldige kansen om voor de Here te werken, al is de tegenstand ook niet gering.

10Als Timotheüs bij u komt, schrik hem dan niet af. Laat hij zich bij u thuisvoelen, want hij werkt net zo goed voor de Here als ik. 11Kijk niet op hem neer, maar help hem goed op weg, zodat hij naar mij toe kan komen. De broeders en ik kijken echt naar hem uit.

12Ik heb onze broeder Apollos dringend gevraagd met de andere broeders naar u toe te gaan. Maar hij wilde nu niet. Als hij later in de gelegenheid is, zal hij zeker komen.

13Wees op uw hoede, houd stand in het geloof, wees moedig en sterk. 14Wat u ook doet, doe het uit liefde. 15U kent Stefanas en zijn gezin wel. Zij waren de eersten in Achaje die gelovig werden en zetten zich volledig voor hun medegelovigen in. 16Ik wil graag dat u zich door hen laat leiden en door allen die zich voor u inspannen.

17Ik ben heel blij dat Stefanas, Fortunatas en Achaïcus hier zijn gekomen. Nu mis ik u niet meer zo erg. 18Zij hebben mij gerustgesteld en bemoedigd en u ook, natuurlijk. U moet zulke mannen waarderen.

19Alle gemeenten in Asia groeten u. Ook van Aquila en Prisca en de gemeente die in hun huis samenkomt, wil ik de hartelijke, christelijke groeten overbrengen. 20Alle broeders en zusters groeten u. Groet elkaar broederlijk, warm en hartelijk.

21De laatste groet schrijf ik zelf. 22Als iemand de Here niet liefheeft, is hij vervloekt. De Here Jezus komt terug! 23Ik wens u de genade van de Here Jezus toe. 24Mijn hart gaat uit naar u allen die bij Christus Jezus horen.