1 ቆሮንቶስ 15 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 15:1-58

የክርስቶስ ትንሣኤ

1አሁንም ወንድሞች ሆይ፤ የሰበክሁላችሁንና የተቀበላችሁትን፣ ደግሞም ጸንታችሁ የቆማችሁበትን ወንጌል ላሳስባችሁ እወድዳለሁ፤ 2የሰበክሁላችሁን ቃል አጥብቃችሁ ብትይዙ፣ በዚህ ወንጌል ትድናላችሁ፤ አለዚያ ያመናችሁት በከንቱ ነው።

3እኔ የተቀበልሁትንና ከሁሉ በላይ የሆነውን15፥3 ወይም፤ ከሁሉ በፊት ለእናንተ አስተላልፌአለሁ፤ ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞተ፤ 4ተቀበረ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈውም በሦስተኛው ቀን ተነሣ፤ 5ከዚያም ለኬፋ15፥5 ጴጥሮስን ማለት ነው። ታየ፤ ቀጥሎም ለዐሥራ ሁለቱ ታየ፤ 6ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ በላይ ለሚሆኑ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነዚህም አብዛኛዎቹ በሕይወት አሉ፤ አንዳንዶቹ ግን አንቀላፍተዋል። 7ከዚያም ለያዕቆብ ታየ፤ በኋላም ለሐዋርያት በሙሉ ታየ፤ 8ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምቈጠር ለእኔ ደግሞ ታየ።

9እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ፣ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ እንኳ የማይገባኝ ነኝ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን አሳድጃለሁ፤ 10ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ አሁን የሆንሁትን ሆኛለሁ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋ ከንቱ አልሆነም፤ እንዲያውም ከሁሉም በላይ በትጋት ሠርቻለሁ፤ ዳሩ ግን እኔ ሳልሆን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው። 11እንግዲህ እኔም ሆንሁ እነርሱ የምንሰብከው ይህንኑ ነው፤ እናንተም ያመናችሁት ይህንኑ ነው።

የሙታን ትንሣኤ

12ክርስቶስ ከሙታን እንደ ተነሣ የሚሰበክ ከሆነ፣ ከእናንተ አንዳንዶቹ እንዴት የሙታን ትንሣኤ የለም ይላሉ? 13የሙታን ትንሣኤ ከሌለማ ክርስቶስም አልተነሣም ማለት ነዋ! 14ክርስቶስም ካልተነሣ ስብከታችን ዋጋ ቢስ ነው፤ እምነታችሁም ከንቱ ነው። 15ከዚህም በላይ፣ እግዚአብሔር ክርስቶስን ከሞት አስነሥቶታል ብለን በመመስከራችን፣ ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን የማይነሡ ከሆነ፣ ክርስቶስንም አላስነሣውም ማለት ነው፤ 16ምክንያቱም ሙታን ካልተነሡ፣ ክርስቶስም አልተነሣም። 17ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ነው፤ እናንተም እስከ አሁን ድረስ ከነኀጢአታችሁ አላችሁ ማለት ነው። 18እንዲህም ከሆነ፣ በክርስቶስ ያንቀላፉት ጠፍተዋል ማለት ነው። 19ክርስቶስን ተስፋ ያደረግነው ለዚህች ሕይወት ብቻ ከሆነ፣ ከሰው ሁሉ ይልቅ የምናሳዝን ነን።

20ነገር ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት ሁሉ በኵራት ሆኖ በርግጥ ከሙታን ተነሥቷል። 21ሞት በአንድ ሰው በኩል እንደ መጣ፣ የሙታንም ትንሣኤ በአንድ ሰው በኩል ሆኗልና። 22ሰዎች ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ፣ እንደዚሁም ሰዎች ሁሉ በክርስቶስ ሕያዋን ይሆናሉ፤ 23ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ተራ ይሆናል፤ መጀመሪያ በኵራት የሆነው ክርስቶስ፣ ከዚያም በኋላ እርሱ ሲመጣ የክርስቶስ የሆኑት። 24ከዚያም ግዛትን፣ ሥልጣንና ኀይልን ሁሉ ከደመሰሰ በኋላ መንግሥትን ለእግዚአብሔር አብ ሲያስረክብ፣ ያን ጊዜ ፍጻሜ ይሆናል። 25ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ ሥር እስከሚያደርግ ድረስ ሊነግሥ ይገባዋልና። 26የሚደመሰሰውም የመጨረሻው ጠላት ሞት ነው፤ 27“ሁሉን ነገር ከእግሩ ሥር አስገዝቶለታል” ተብሏልና፤ ነገር ግን፣ ሁሉን ነገር አስገዛለት ሲል፣ ሁሉ ነገር በክርስቶስ ሥር እንዲገዛ ያደረገውን እግዚአብሔርን እንደማይጨምር ግልጽ ነው። 28ሁሉ ከተገዛለት በኋላ እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ እንዲሆን ወልድ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ለእርሱ ይገዛል።

29ትንሣኤ ከሌለማ ለሞቱ ሰዎች ብለው የሚጠመቁት ምን እያደረጉ ነው? ሙታን ከቶ የማይነሡ ከሆነ፣ ሰዎች ለእነርሱ ብለው ለምን ይጠመቃሉ? 30እኛስ ብንሆን ዘወትር ለአደጋ የምንጋለጠው ለምንድን ነው? 31ወንድሞች ሆይ፤ እኔ በየቀኑ እሞታለሁ፤ ይህንም በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ በእናንተ ላይ ባለኝ ትምክሕት አረጋግጣለሁ። 32በኤፌሶን ከአራዊት ጋር የታገልሁት ለሰው አስተያየት ብቻ ከሆነ ትርፌ ምንድን ነው? ሙታን የማይነሡ ከሆነ፣

“ነገ ስለምንሞት፣

እንብላ፣ እንጠጣ፤”

እንደሚሉት መሆናችን ነው። 33አትሳቱ፤ “መጥፎ ጓደኝነት መልካሙን ጠባይ ያበላሻል።” 34ወደ ሰከነ ልቦናችሁ ተመለሱ፤ ኀጢአትንም አትሥሩ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና፤ ይህንም የምለው ላሳፍራችሁ ነው።

የትንሣኤ አካል

35ነገር ግን፣ “ሙታን እንዴት ይነሣሉ? የሚመጡትስ በምን ዐይነት አካል ነው?” የሚል ሰው ሊኖር ይችላል። 36አንተ ሞኝ! የምትዘራው ካልሞተ ሕይወት አያገኝም። 37የምትዘራውም የስንዴ ወይም የሌላ ዐይነት ዘር ቅንጣት ብቻ እንጂ ወደ ፊት የምታገኘውን አካል አይደለም። 38እግዚአብሔር ግን እንደ ፈቀደ አካልን ይሰጠዋል፤ ለእያንዳንዱም የዘር ዐይነት የራሱን አካል ይሰጠዋል። 39ሥጋ ሁሉ አንድ አይደለም፤ የሰው ሥጋ አንድ ነው፤ የእንስሳት ሥጋ ሌላ ነው፤ የዓሣ ሥጋ ሌላ ዐይነት ነው። 40እንዲሁም ሰማያውያን አካላት አሉ፤ ምድራውያን አካላት አሉ፤ ነገር ግን የሰማያዊ አካላት ክብር አንድ ነው፤ የምድራዊም አካላት ክብር ሌላ ነው። 41የፀሓይ ክብር አንድ ዐይነት ነው፤ የጨረቃ ክብር ሌላ ነው፤ የከዋክብት ደግሞ ሌላ ነው፤ የአንዱም ኮከብ ክብር ከሌላው ኮከብ ክብር ይለያል።

42የሙታን ትንሣኤም እንደዚሁ ነው፤ የሚበሰብስ አካል ይዘራል፤ የማይበሰብስ አካል ሆኖ ይነሣል፤ 43በውርደት ይዘራል፤ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል በኀይል ይነሣል፤ 44ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፤ መንፈሳዊ አካል ይነሣል።

ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ። 45ስለዚህ፣ “የመጀመሪያው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ” ተብሎ ተጽፏል፤ የኋለኛው አዳም ግን ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ። 46ነገር ግን በመጀመሪያ የመጣው መንፈሳዊው ሳይሆን ፍጥረታዊው ነው፤ ከዚያም በኋላ መንፈሳዊው መጣ። 47የመጀመሪያው ሰው ከምድር የተገኘ ምድራዊ ነው፤ የኋለኛው ግን ከሰማይ ነው። 48ከምድር የሆኑት እንደ ምድራዊው ናቸው፤ ከሰማይ የሆኑትም እንደ ሰማያዊው ናቸው። 49የምድራዊውን ሰው መልክ እንደ ለበስን፣ የሰማያዊውን ሰው መልክ ደግሞ እንለብሳለን።15፥49 አንዳንድ የጥንት ቅጆች እንልበስ ይላሉ።

50ወንድሞች ሆይ፤ ይህን እነግራችኋለሁ፤ ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም፤ የሚጠፋውም የማይጠፋውን አይወርስም። 51እነሆ፤ አንድ ምስጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም፤ ነገር ግን ሁላችንም እንለወጣለን፤ 52ይህም የሚሆነው የመጨረሻው መለከት ሲነፋ ድንገት በቅጽበተ ዐይን ነው። መለከት ይነፋል፤ ሙታን የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ፤ እኛም እንለወጣለን። 53የሚጠፋው የማይጠፋውን፣ የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና። 54የሚጠፋው የማይጠፋውን፣ የሚሞተውም የማይሞተውን በሚለብስበት ጊዜ፣ “ሞት በድል ተዋጠ” ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።

55እንዲሁም፣ “ሞት ሆይ፤ ድል መንሣትህ የት አለ?

ሞት ሆይ፤ መንደፊያህስ የት አለ?”

56የሞት መንደፊያ ኀጢአት ነው፤ የኀጢአትም ኀይል ሕግ ነው። 57ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድልን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።

58ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ።

Thai New Contemporary Bible

1โครินธ์ 15:1-58

พระเยซูคริสต์ทรงคืนพระชนม์

1พี่น้องทั้งหลาย ข้าพเจ้าอยากเตือนท่านให้ระลึกถึงข่าวประเสริฐที่ข้าพเจ้าได้ประกาศแก่ท่าน ซึ่งท่านได้รับไว้และตั้งมั่นอยู่บนฐานนี้ 2ถ้าท่านยึดมั่นในถ้อยคำที่ข้าพเจ้าประกาศแก่ท่าน ท่านก็จะรอดโดยข่าวประเสริฐนี้ มิฉะนั้นท่านก็เชื่อโดยเปล่าประโยชน์

3เพราะเรื่องที่ข้าพเจ้าได้รับมานั้นเป็นเรื่องที่สำคัญที่สุด15:3 หรือเป็นประการแรก และข้าพเจ้าได้ถ่ายทอดให้ท่านคือ พระคริสต์ทรงวายพระชนม์เพราะบาปของเราตามที่เขียนไว้ในพระคัมภีร์ 4ทรงถูกฝังไว้และในวันที่สามพระเจ้าทรงให้พระองค์เป็นขึ้นจากตายตามที่พระคัมภีร์ระบุไว้ 5และทรงปรากฏแก่เปโตร15:5 ภาษากรีกว่าเคฟาส จากนั้นปรากฏแก่อัครทูตทั้งสิบสองคน 6ต่อมาพระองค์ทรงปรากฏแก่พวกพี่น้องกว่าห้าร้อยคนในคราวเดียว ซึ่งส่วนใหญ่ยังมีชีวิตอยู่ แม้บางคนได้ล่วงลับไปแล้ว 7จากนั้นพระองค์ทรงปรากฏแก่ยากอบและแก่อัครทูตทั้งปวง 8และในท้ายที่สุดพระองค์ทรงปรากฏแก่ข้าพเจ้าด้วย ผู้เป็นเหมือนทารกที่คลอดผิดปกติ

9เพราะข้าพเจ้าเป็นผู้น้อยที่สุดในหมู่อัครทูตและไม่คู่ควรแม้กระทั่งจะได้ชื่อว่าอัครทูต เพราะข้าพเจ้าได้ข่มเหงคริสตจักรของพระเจ้า 10แต่โดยพระคุณของพระเจ้าข้าพเจ้าจึงเป็นอย่างที่เป็นอยู่นี้ และพระคุณของพระองค์ที่มีต่อข้าพเจ้านั้นไม่ใช่ว่าจะไร้ผล ข้าพเจ้าทำงานหนักยิ่งกว่าพวกเขาทั้งปวง แต่ไม่ใช่ข้าพเจ้าเองเป็นคนทำ พระคุณของพระเจ้าซึ่งดำรงอยู่กับข้าพเจ้าต่างหากที่ทำ 11ฉะนั้นไม่ว่าจะเป็นข้าพเจ้าหรือพวกเขา นี่คือสิ่งที่เราประกาศและนี่คือสิ่งที่ท่านได้เชื่อ

การเป็นขึ้นจากตาย

12แต่ถ้าเราประกาศว่าพระคริสต์ทรงเป็นขึ้นจากตาย เหตุใดพวกท่านบางคนยังกล่าวว่าไม่มีการเป็นขึ้นจากตาย? 13ถ้าไม่มีการเป็นขึ้นจากตายแล้ว พระคริสต์เองก็ไม่ได้เป็นขึ้นจากตายด้วย 14และถ้าพระคริสต์ไม่ได้เป็นขึ้นจากตาย คำเทศนาของเราก็ไร้ค่าและความเชื่อของท่านก็ไร้ค่า 15ยิ่งไปกว่านั้นกลายเป็นว่าเราเป็นพยานเท็จเรื่องพระเจ้า เพราะเราเป็นพยานว่าพระเจ้าทรงให้พระคริสต์เป็นขึ้นจากตาย แต่ถ้าความจริงคือพระเจ้าไม่ได้ทรงให้คนตายเป็นขึ้นมา พระองค์ก็ไม่ได้ทรงให้พระคริสต์เป็นขึ้นมา 16เพราะถ้าพระเจ้าไม่ทรงให้คนตายเป็นขึ้นแล้ว พระองค์ย่อมไม่ทรงให้พระคริสต์เป็นขึ้นเช่นกัน 17และถ้าพระองค์ไม่ได้ทรงให้พระคริสต์เป็นขึ้นจากตาย ความเชื่อของท่านก็ไร้ผล ท่านยังคงอยู่ในบาปของตน 18แล้วบรรดาผู้ที่ล่วงลับไปในพระคริสต์ก็พินาศไปด้วย 19ถ้าเรามีความหวังในพระคริสต์เพียงเพื่อชีวิตนี้ เราก็น่าสมเพชกว่าคนทั้งปวง

20แต่นี่ทรงให้พระคริสต์เป็นขึ้นจากตายจริงๆ เป็นผลแรกของบรรดาผู้ที่ล่วงลับไป 21เพราะในเมื่อความตายสืบเนื่องมาจากมนุษย์คนเดียว การเป็นขึ้นจากตายก็สืบเนื่องมาจากมนุษย์คนเดียวเช่นกัน 22เพราะว่าในอาดัมคนทั้งปวงตายฉันใด ในพระคริสต์คนทั้งปวงจะได้รับชีวิตฉันนั้น 23แต่จะเป็นไปตามลำดับคือ พระคริสต์ผู้เป็นผลแรก จากนั้นบรรดาคนของพระองค์เมื่อพระองค์เสด็จมา 24แล้วจุดจบก็มาถึงเมื่อพระองค์ทรงถวายอาณาจักรแด่พระเจ้าพระบิดา หลังจากที่ทรงทำลายเทพผู้ปกครองอาณาจักร เทพผู้ทรงอำนาจ และเทพผู้ทรงเดชานุภาพทั้งปวง 25เพราะพระองค์จะต้องครอบครองจนกว่าพระองค์จะได้สยบศัตรูทั้งสิ้นไว้ใต้พระบาทของพระองค์ 26ศัตรูตัวสุดท้ายที่ต้องทรงทำลายคือความตาย 27เพราะพระองค์ “ได้ทรงทำให้ทุกสิ่งอยู่ใต้พระบาทของพระองค์”15:27 สดด.8:6 ที่ว่า “ทุกสิ่ง” อยู่ใต้พระองค์นี้เป็นที่ชัดเจนว่าไม่รวมถึงพระเจ้าเองผู้ทรงให้ทุกสิ่งอยู่ภายใต้พระคริสต์ 28เมื่อพระองค์ทรงกระทำเช่นนี้แล้ว พระบุตรเองจะอยู่ภายใต้พระเจ้าผู้ทรงทำให้ทุกสิ่งอยู่ภายใต้พระองค์ เพื่อพระเจ้าจะทรงอยู่เหนือ15:28 ภาษากรีกว่าทรงเป็นทุกสิ่งในทุกสิ่ง

29เมื่อเป็นเช่นนั้น ถ้าไม่มีการเป็นขึ้นจากตายแล้ว บรรดาผู้ที่รับบัพติศมาสำหรับคนตายจะทำอย่างไร? ถ้าคนตายไม่คืนชีวิต ทำไมยังมีคนรับบัพติศมาเพื่อผู้ตาย? 30และสำหรับเรา ทำไมเราจึงต้องเผชิญภยันตรายอยู่ทุกเวลา? 31ข้าพเจ้าตายทุกวัน พี่น้องทั้งหลาย ข้าพเจ้าหมายความเช่นนั้น สิ่งนี้แน่นอนเหมือนที่ข้าพเจ้าภาคภูมิใจในพวกท่านในพระเยซูคริสต์องค์พระผู้เป็นเจ้าของเรา 32ถ้าข้าพเจ้าต่อสู้กับพวกสัตว์ป่าในเอเฟซัสเพียงเพื่อเหตุผลของมนุษย์ ข้าพเจ้าได้อะไร? หากพระเจ้าไม่ได้ให้คนตายเป็นขึ้นมา

“ให้เรากินและดื่ม

เพราะพรุ่งนี้เราก็ตายแล้ว”15:32 อสย.22:13

33อย่าให้ใครชักจูงให้หลงผิดเลย “เพื่อนเลวย่อมทำให้อุปนิสัยที่ดีเสื่อมทรามไป” 34จงกลับมีสติสัมปชัญญะอย่างที่ควรเถิดและเลิกทำบาป เพราะมีบางคนไม่รู้จักพระเจ้าเลย ที่ข้าพเจ้าพูดเช่นนี้ก็เพื่อให้ท่านละอายใจ

กายที่เป็นขึ้นจากตาย

35แต่บางคนอาจจะถามว่า “คนตายเป็นขึ้นมาได้อย่างไร? เมื่อเป็นขึ้นร่างกายของเขาจะเป็นแบบไหน?” 36ช่างเขลาเสียจริง! สิ่งที่ท่านหว่านลงจะไม่มีชีวิตขึ้นมา ถ้าสิ่งนั้นไม่ตายเสียก่อน 37เมื่อท่านหว่าน ท่านไม่ได้ปลูกต้นที่โตเต็มที่แล้ว แต่ท่านปลูกแค่เมล็ด ไม่ว่าจะเป็นเมล็ดข้าวสาลีหรือเมล็ดพืชใดๆ 38แต่พระเจ้าประทานลำต้นตามที่ได้ทรงกำหนดไว้ และพระองค์ประทานลำต้นของมันเองให้แก่เมล็ดแต่ละชนิด 39เนื้อทั้งปวงไม่เหมือนกัน เนื้อมนุษย์ก็อย่างหนึ่ง สัตว์ต่างๆ ก็อีกอย่างหนึ่ง สัตว์ปีกสัตว์น้ำก็อีกอย่างหนึ่ง 40กายก็มีทั้งแบบสวรรค์และแบบฝ่ายโลกเช่นกัน แต่สง่าราศีของกายแบบสวรรค์ก็อย่างหนึ่ง และสง่าราศีของกายแบบฝ่ายโลกก็อีกอย่างหนึ่ง 41สง่าราศีของดวงอาทิตย์เป็นแบบหนึ่ง ดวงจันทร์ก็อีกแบบหนึ่ง และดวงดาวก็อีกแบบหนึ่ง อันที่จริงสง่าราศีของดาวแต่ละดวงก็ต่างกัน

42การเป็นขึ้นมาของคนตายก็เช่นกัน กายที่หว่านลงนั้นเสื่อมสลายได้ ที่เป็นขึ้นมาใหม่จะไม่เสื่อมสลาย 43ที่หว่านลงนั้นไร้ศักดิ์ศรี ที่เป็นขึ้นเปี่ยมด้วยศักดิ์ศรี ที่หว่านลงนั้นอ่อนแอ ที่เป็นขึ้นทรงพลัง 44ที่หว่านลงนั้นเป็นกายธรรมชาติ ที่เป็นขึ้นเป็นกายวิญญาณ

ถ้ามีกายธรรมชาติย่อมมีกายวิญญาณด้วย 45จึงมีเขียนไว้ว่า “อาดัมมนุษย์คนแรกจึงกลายเป็นผู้มีชีวิต”15:45 ปฐก.2:7 ส่วนอาดัมคนหลังเป็นวิญญาณผู้ให้ชีวิต 46กายวิญญาณไม่ได้มาก่อน แต่กายธรรมชาติมาก่อนและกายวิญญาณมาทีหลัง 47มนุษย์คนแรกมาจากธุลีดินของโลกนี้ มนุษย์คนที่สองมาจากสวรรค์ 48คนฝ่ายโลกเป็นอย่างไร ชาวโลกก็เป็นอย่างนั้น คนจากสวรรค์เป็นอย่างไร ชาวสวรรค์ก็เป็นอย่างนั้น 49และเราเกิดมามีลักษณะเหมือนกับคนฝ่ายโลกอย่างไร เราก็จะมี15:49 สำเนาต้นฉบับเก่าแก่บางสำเนาว่าดังนั้นให้เรามีลักษณะเหมือนกับคนจากสวรรค์อย่างนั้น

50พี่น้องทั้งหลาย ข้าพเจ้าขอประกาศว่าเนื้อและเลือดไม่อาจรับอาณาจักรของพระเจ้าเป็นมรดก และสิ่งที่เสื่อมสลายไม่อาจรับสิ่งที่ไม่เสื่อมสลายเป็นมรดก 51ฟังเถิด ข้าพเจ้าจะบอกข้อล้ำลึกแก่ท่าน คือเราจะไม่ล่วงลับกันทั้งหมด แต่พวกเราทั้งหมดจะได้รับการเปลี่ยนแปลง 52ชั่วแวบเดียวในพริบตาเดียว เมื่อเป่าแตรครั้งสุดท้าย เพราะเสียงแตรจะดังขึ้น คนตายจะถูกทำให้เป็นขึ้นแบบไม่เสื่อมสลายและเราจะได้รับการเปลี่ยนแปลง 53เพราะที่เสื่อมสลายต้องสวมที่ไม่เสื่อมสลาย และที่ตายได้ต้องสวมที่ไม่มีวันตาย 54เมื่อที่เสื่อมสลายนั้นสวมที่ไม่เสื่อมสลาย และที่ตายได้นั้นสวมที่ไม่มีวันตายแล้ว คำกล่าวที่ได้บันทึกไว้ก็จะเป็นจริงคือ “ความตายก็พ่ายแพ้ถูกกลืนหายไป”15:54 อสย.25:8

55“ความตายเอ๋ย ไหนล่ะชัยชนะของเจ้า?

ความตายเอ๋ย ไหนล่ะเหล็กไนของเจ้า?”15:55 ฮชย. 13:14

56เหล็กไนของความตายคือบาป และอานุภาพของบาปคือบทบัญญัติ 57แต่ขอบพระคุณพระเจ้า! พระองค์ประทานชัยชนะแก่เราโดยทางองค์พระเยซูคริสต์เจ้าของเรา

58เหตุฉะนั้นพี่น้องที่รักของข้าพเจ้า จงตั้งมั่นอยู่ อย่าให้สิ่งใดทำให้ท่านหวั่นไหว จงทุ่มเทอย่างเต็มที่ให้กับงานขององค์พระผู้เป็นเจ้า เพราะท่านรู้ว่าในองค์พระผู้เป็นเจ้า การงานของท่านจะไม่สูญเปล่า