1 ሳሙኤል 7 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 7:1-17

1የቂርያትይዓሪም ሰዎችም መጥተው የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ወጡ፤ ከዚያም በኰረብታው ላይ ወዳለው ወደ አሚናዳብ ቤት ወሰዱት። የእግዚአብሔርን ታቦት እንዲጠብቅም ልጁን አልዓዛርን ቀደሱት።

የፍልስጥኤማውያን መሸነፍ

2ታቦቱ በቂርያትይዓሪም ከተቀመጠ ረዥም ጊዜ ሆነው፤ በአጠቃላይ ሃያ ዓመት ቈየ። የእስራኤል ሕዝብ ሁሉ አዘነ፤ እግዚአብሔርንም ፈለገ። 3ሳሙኤልም የእስራኤልን ቤት ሁሉ፣ “በፍጹም ልባችሁ ወደ እግዚአብሔር የምትመለሱ ከሆነ፣ ሌሎችን አማልክትና አስታሮትን ከመካከላችሁ አስወግዱ፤ ራሳችሁንም ለእግዚአብሔር አሳልፋችሁ ስጡ፤ እርሱንም ብቻ አምልኩ፤ እርሱም ከፍልስጥኤማውያን እጅ ይታደጋችኋል።” አላቸው። 4ስለዚህ እስራኤላውያን የበኣልንና የአስታሮትን አማልክት አስወግደው፣ እግዚአብሔርን ብቻ አመለኩ።

5ከዚያ በኋላ ሳሙኤል፣ “እስራኤልን ሁሉ በምጽጳ ሰብስቡ፤ እኔም ስለ እናንተ ወደ እግዚአብሔር እጸልያለሁ” አለ። 6እስራኤላውያን በምጽጳ በተሰበሰቡ ጊዜ፣ ውሃ ቀድተው በእግዚአብሔር ፊት አፈሰሱ፤ በዚያች ዕለት ጾሙ፤ በዚያም “እግዚአብሔርን በድለናል” ብለው ተናዘዙ። ሳሙኤልም በምጽጳ እስራኤልን ይፈርድ ነበር።

7እስራኤል በምጽጳ መሰብሰባቸውን ፍልስጥኤማውያን በሰሙ ጊዜ፣ የፍልስጥኤማውያን ገዦች ሊወጓቸው ወጡ፤ እስራኤላውያንም ይህን ሲሰሙ፣ ፍልስጥኤማውያንን ፈሩ፤ 8ሳሙኤልንም፣ “አምላካችን እግዚአብሔር ከፍልስጥኤማውያን እጅ ያድነን ዘንድ ስለ እኛ ወደ እርሱ መጸለይህን አታቋርጥ” አሉት። 9ሳሙኤልም አንድ የሚጠባ የበግ ግልገል ወስዶ ሙሉ ለሙሉ የሚቃጠል መሥዋዕት በማድረግ ለእግዚአብሔር አቀረበው፤ ስለ እስራኤልም ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ እግዚአብሔርም መለሰለት።

10ሳሙኤል የሚቃጠለውን መሥዋዕት በሚያሳርግበት ጊዜ፣ ፍልስጥኤማውያን እስራኤልን ለመውጋት ቀረቡ። ይሁን እንጂ በዚያ ዕለት እግዚአብሔር በፍልስጥኤማውያን ላይ ከባድ የነጐድጓድ ድምፅ ስላንጐዳጐደባቸው እጅግ ተሸበሩ፤ ድልም ተመተው ከእስራኤላውያን ፊት ሸሹ። 11እስራኤላውያንም ከምጽጳ ወጥተው ፍልስጥኤማውያንን በየመንገዱ እየገደሉ ከቤትካር በታች እስካለው ስፍራ ድረስ አሳደዷቸው።

12ከዚህ በኋላ ሳሙኤል አንድ ድንጋይ ወስዶ በምጽጳና በሼን መካከል አቆመው፤ ስሙንም “እግዚአብሔር እስከ አሁን ድረስ ረድቶናል” ሲል “አቤንኤዘር7፥12 አቤኔዘር ማለት የርዳታ ድንጋይ ማለት ነው።” ብሎ ጠራው። 13በዚህ ሁኔታ ፍልስጥኤማውያን ድል ስለ ተመቱ፣ የእስራኤልን ምድር ዳግመኛ አልወረሩም።

ሳሙኤል በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ፣ የእግዚአብሔር እጅ በፍልስጥኤማውያን ላይ ከብዳ ነበር። 14ፍልስጥኤማውያን ከእስራኤል የወሰዷቸው ከአቃሮን እስከ ጌት የነበሩ ከተሞች ለእስራኤል ተመለሱላት፤ ግዛታቸውም ከፍልስጥኤማውያን እጅ ነፃ ወጣች፤ በእስራኤልና በአሞራውያንም መካከል ሰላም ነበረ።

15ሳሙኤል በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ፣ እስራኤልን ይዳኝ ነበር። 16በየዓመቱ በቤቴል፣ በጌልገላና በምጽጳ እየተዘዋወረ፣ በእነዚህ ቦታዎች ሁሉ በእስራኤል ላይ ይፈርድ ነበር። 17ከዚያም በአርማቴም ወዳለው ቤቱ ይመለስ ነበር፤ በዚያም ደግሞ በእስራኤል ላይ ይፈርድ ነበር። በዚያም ለእግዚአብሔር መሠዊያ ሠራ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

撒母耳记上 7:1-17

1基列·耶琳人就下来把耶和华的约柜抬到山上,放在亚比拿达的家里,派他的儿子以利亚撒看守耶和华的约柜。

撒母耳征服非利士人

2约柜在基列·耶琳停留了二十年。那时,全体以色列人都痛悔地寻求耶和华。 3撒母耳对他们说:“如果你们全心归向耶和华,就要除掉你们那些外族的神明,包括亚斯她录神像,一心归向耶和华,单单事奉祂,祂必从非利士人手中救你们。” 4于是,他们除掉了巴力亚斯她录神像,单单事奉耶和华。

5撒母耳又说:“你们全体以色列人到米斯巴来,我会为你们向耶和华祈求。” 6他们就在那里聚集,打水倒在耶和华面前,并在当天禁食。他们说:“我们得罪了耶和华。”于是,撒母耳米斯巴以色列人的士师。 7非利士人听说以色列人在米斯巴聚集,他们的首领就率领军队来攻打以色列人。以色列人听见消息后,非常害怕。 8他们对撒母耳说:“请你为我们不停地呼求我们的上帝耶和华,求祂从非利士人手中拯救我们。” 9撒母耳把一只还在吃奶的羊献给耶和华作全牲燔祭。他为以色列人呼求耶和华,耶和华垂听了他的祈求。 10撒母耳正在献燔祭的时候,非利士人已经逼近了。那天,耶和华向非利士人发出雷霆之声,使他们陷入一片恐慌,败在了以色列人手下。 11以色列人从米斯巴一路追杀他们,直到伯·甲附近。

12撒母耳拿了一块石头放在米斯巴的中间,称之为以便以谢7:12 以便以谢”意思是“援助之石”。,说:“耶和华到如今都帮助我们。”

13这样非利士人被征服了,没有再侵犯以色列人。在撒母耳有生之年,耶和华一直严厉地对付非利士人。 14以色列人收复了从以革伦迦特之间被非利士人夺去的城邑,并夺回了这些城邑的周边地区。那时以色列人与亚摩利人和平共处。

15撒母耳一生做以色列人的士师。 16他每年都到伯利恒吉甲米斯巴各地巡回,审理以色列人的案件。 17之后,他才回到拉玛自己的家中,也在那里审理以色列人的案件,并为耶和华筑了一座祭坛。