1 ሳሙኤል 5 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 5:1-12

ታቦቱ ወደ አሽዶድና ወደ አቃሮን ተወሰደ

1ፍልስጥኤማውያን የእግዚአብሔርን ታቦት ከማረኩ በኋላ፣ ከአቤንኤዘር ወደ አሽዶድ ወሰዱት። 2ከዚያም ወደ ዳጎን ቤተ ጣዖት አግብተው፣ በዳጎን አጠገብ አኖሩት። 3የአሽዶድም ሰዎች በማግስቱም ማለዳ ተነሥተው ሲመለከቱ እነሆ፣ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት መሬት ላይ በግንባሩ ተደፍቶ አገኙት። ከዚያም አንሥተው ወደ ቦታው መለሱት። 4በሚቀጥለው ቀን ጧት ተነሥተው ሲመለከቱ፣ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት፣ መሬት ላይ በግንባሩ ተደፍቶ ነበር፤ ራሱና እጆቹ ተሰባብረው በደጃፉ ላይ የወደቁ ሲሆን፣ የቀረው ሌላው አካሉ ብቻ ነበር። 5የዳጎን ካህናትም ሆኑ ሌሎች በአሽዶድ ወዳለው የዳጎን ቤተ ጣዖት የሚገቡ ሁሉ እስከ ዛሬ ድረስ እግራቸው ደጃፉን እንዳይረግጥ ተራምደው የሚያልፉት በዚሁ ምክንያት ነው።

6የእግዚአብሔር እጅ በአሽዶድ ሕዝብና በአካባቢዋ ላይ ጠነከረ፤ እርሱም ጥፋት አመጣባቸው፤ በዕባጭም መታቸው5፥6 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት የቩልጊት ትርጕም ግን በምድራቸው ላይ ዐይጥ መታየት ጀመረ፤ እንዲሁም ሞትና ጥፋት በከተማዪቱ ዙሪያ ነበር ይላል።7የአሽዶድ ሰዎች ይህን ባዩ ጊዜ፣ “እጁ በእኛና በአምላካችን በዳጎን ላይ ጠንክሯልና የእስራኤል አምላክ ታቦት በእኛ ዘንድ መቈየት የለበትም” አሉ። 8ከዚህ በኋላ የፍልስጥኤማውያንን ገዦች በሙሉ ጠርተው፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ምን እናድርገው?” ሲሉ ጠየቁ።

እነርሱም፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ወደ ጌት ውሰዱት” አሏቸው። ስለዚህ የእስራኤልን አምላክ ታቦት ወሰዱት።

9ነገር ግን ታቦቱን ወደዚያ ከወሰዱት በኋላ የእግዚአብሔር እጅ በከተማዪቱ ላይ ሆነ፤ ታላቅ መሸበርም አመጣባቸው፤ ሕፃን ሽማግሌ ሳይል ሕዝቡን በዕባጭ መታ5፥9 ወይም ብልታቸውን አሳበጠባቸው10ስለዚህ የእግዚአብሔርን ታቦት ወደ አቃሮን ሰደዱት።

የእግዚአብሔር ታቦት እዚያ ሲገባም፣ የአቃሮን ሕዝብ፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ያመጡብን እኛንና ሕዝባችንን ለማስፈጀት ነው” በማለት ጮኹ። 11የእግዚአብሔር እጅ በርትቶባቸው ስለ ነበር፣ ሞት ከተማዪቱን እጅግ አስደንግጧት ነበርና ሕዝቡ የፍልስጥኤማውያንን ገዦች በሙሉ ጠርተው፣ “የእስራኤልን አምላክ ታቦት ከዚህ አርቁልን፤ ወደ ገዛ ስፍራው ይመለስ፤ አለዚያ እኛንም ሕዝባችንንም ይፈጃል” አሉ። 12ያልሞቱትን ደግሞ ዕባጩ ያሠቃያቸው ስለ ነበር፣ የከተማዪቱ ጩኸት እስከ ሰማይ ወጣ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

撒母耳记上 5:1-12

约柜在非利士人手中

1非利士人将掳来的上帝的约柜从以便以谢抬到亚实突城, 2把它抬进大衮庙,放在大衮神像旁边。 3第二天早上,亚实突人起来,发现大衮神像倒在耶和华的约柜前,面伏于地,他们就把大衮神像扶起来,放回原处。 4次日早上起来,他们又发现大衮神像倒在耶和华的约柜前,面伏于地,头和双手都在门槛处折断了,只剩下躯干。 5因此,大衮的祭司和所有进亚实突大衮庙的人至今都不踏庙的门槛。 6耶和华重重地惩罚亚实突及附近村庄的居民,使他们都患上毒疮。 7亚实突人见此情形,就说:“以色列上帝的约柜不能留在我们这里,因为上帝重重地惩罚我们和我们的大衮神。” 8亚实突人召集了非利士所有的首领,问他们:“我们如何处理以色列上帝的约柜?”他们答道:“把它送到迦特去。”于是,众人把以色列上帝的约柜送到迦特9约柜抵达迦特的时候,耶和华攻击那城,使那里的男女老少都患了毒疮,全城惊恐不已。 10于是,他们把约柜送往以革伦以革伦的人看见上帝的约柜到了,就惊叫道:“他们把以色列上帝的约柜带来是要害死我们和我们的人民!” 11他们派人召集非利士的首领,说:“把以色列上帝的约柜送回原处吧,免得它杀害我们和我们的人民。”因为上帝重重地惩罚他们,全城都笼罩在死亡的恐惧中。 12那些没有死的人都饱受毒疮的折磨,城中的哭喊声上达于天。