1 ሳሙኤል 26 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 26:1-25

ዳዊት ለሁለተኛ ጊዜ ሳኦልን ከመግደል ታቀበ

1የዚፍ ሰዎች ሳኦል ወዳለበት ወደ ጊብዓ መጥተው፣ “እነሆ፤ ዳዊት በየሴሞን ትይዩ በሚገኘው በኤኬላ ኰረብታ ተደብቋል” ብለው ነገሩት።

2ስለዚህ ሳኦል ተነሣ፤ ከእስራኤል የተመረጡትን ሦስት ሺሕ ሰዎችን ይዞ፣ ዳዊትን ፍለጋ ወደ ዚፍ ምድረ በዳ ወረደ። 3ሳኦልም በየሴሞን ትይዩ በሚገኘው በኤኬላ ኰረብታ ላይ በመንገድ ዳር ሰፈረ፤ ዳዊት ግን በምድረ በዳ ነበር። ዳዊትም ሳኦል እዚያ ድረስ እንደ ተከተለው ባወቀ ጊዜ፣ 4ሰላዮች ልኮ በትክክል ሳኦል መምጣቱን አረጋገጠ።

5ዳዊትም ተነሥቶ ሳኦል ወደ ሰፈረበት ቦታ ሄደ፤ ሳኦልና የሰራዊቱ አለቃ፣ የኔር ልጅ አበኔር የተኙበትን ስፍራ አየ። ሳኦል በሰፈሩ መካከል ተኝቶ ሳለ፣ ሰራዊቱ በዙሪያው ሰፍሮ ነበር።

6ዳዊትም ኬጢያዊውን አቢሜሌክንና የጽሩያን ልጅ የኢዮአብን ወንድም አቢሳን፣ “ወደ ሳኦል ሰፈር አብሮኝ የሚወርድ ማነው?” ሲል ጠየቃቸው።

አቢሳም፣ “እኔ አብሬህ እወርዳለሁ” አለ።

7ስለዚህ ዳዊትና አቢሳ በሌሊት ሰራዊቱ ወዳለበት ሄዱ። እነሆ፤ ሳኦል በሰፈሩ ውስጥ ተኝቶ ጦሩም ራስጌው አጠገብ በመሬት ላይ ተተክሎ ነበር፤ አበኔርና ወታደሮቹም በዙሪያው ተኝተው ነበር።

8አቢሳም ዳዊትን፣ “ዛሬ እግዚአብሔር ጠላትህን በእጅህ ላይ ጥሎታል፤ አሁንም እኔ አንድ ጊዜ በጦር ወግቼ ከመሬት ጋር ላጣብቀው፤ መድገምም አያስፈልገኝም” አለው።

9ዳዊት ግን አቢሳን እንዲህ አለው፤ “አትግደለው! እግዚአብሔር በቀባው ላይ እጁን አንሥቶ ከበደል ነጻ የሚሆን ማን ነው? 10ሕያው እግዚአብሔርን! እግዚአብሔር ራሱ ይቀሥፈዋል፤ ወይም ቀኑ ደርሶ ይሞታል፤ ወይም በጦርነት ይሞታል። 11እግዚአብሔር በቀባው ላይ እጄን ከማንሣት እግዚአብሔር ይጠብቀኝ! ነገር ግን በራስጌው አጠገብ ያለውን ጦርና የውሃ መያዣውን ያዝና እንሂድ።”

12ስለዚህ ዳዊት በሳኦል ራስጌ አጠገብ የነበረውን ጦርና የውሃውን መያዣ ወሰደ፤ ከዚያም ሄዱ፤ ይህን ያየም ሆነ ያወቀ ወይም የነቃ ማንም አልነበረም። ከእግዚአብሔር ዘንድ ከባድ እንቅልፍ ስለ ወደቀባቸው ሁሉም ተኝተው ነበርና።

13ከዚህ በኋላ ዳዊት ወደ ማዶ ተሻግሮ በኰረብታው ጫፍ ላይ ራቅ ብሎ ቆመ፤ በመካከላቸውም ሰፊ ርቀት ነበር። 14ዳዊት ሰራዊቱንና የኔርን ልጅ አብኔርን፣ “አበኔር ሆይ፣ አትመልስልኝምን?” ሲል ተጣራ።

አበኔርም፣ “በንጉሡ ላይ የምትጮኽ አንተ ማነህ?” በማለት መለሰ።

15ዳዊትም እንዲህ አለ፤ “አንተ ብርቱ ሰው ነህ? በእስራኤልስ ዘንድ አንተን የሚመስል ማን ነው? እነሆ፤ አንድ ሰው ንጉሡን ጌታህን ለመግደል መጥቶ ነበር፤ ታዲያ አንተ ንጉሥ ጌታህን ያልጠበቅኸው ስለ ምንድን ነው? 16ያደረግኸው መልካም አይደለም፤ ሕያው እግዚአብሔርን! አንተና ሰዎችህ ሞት ይገባችኋል፤ እግዚአብሔር የቀባውን ጌታችሁን አልጠበቃችሁምና። እስቲ ተመልከት፤ በራስጌው የነበሩት የንጉሡ ጦርና የውሃ መያዣ የት አሉ?”

17ሳኦል የዳዊትን ድምፅ ለይቶ ስላወቀ፣ “ልጄ ዳዊት ሆይ፤ ይህ ድምፅህ ነውን?” አለው። ዳዊትም፣ “ንጉሥ ጌታዬ ሆይ፤ አዎን ድምፄ ነው” ሲል መለሰ፤ 18በመቀጠልም፣ “ጌታዬ አገልጋዩን የሚያሳድደው ስለ ምንድን ነው? ምን አደረግሁ? ምን በደልስ ፈጸምሁ? 19አሁንም ንጉሥ ጌታዬ የባሪያውን ቃል ያድምጥ፤ እግዚአብሔር በእኔ ላይ አነሣሥቶህ እንደ ሆነ፣ ቍርባን ይቀበል፤ ነገር ግን ይህን ያደረጉት ሰዎች ከሆኑ፣ በእግዚአብሔር ፊት የተረገሙ ይሁኑ፤ ‘ሂድ ሌሎችን አማልክት አምልክ’ ብለው በእግዚአብሔር ርስት ድርሻ እንዳይኖረኝ ዛሬ አሳድደውኛልና። 20አንድ ሰው በተራራ ላይ ቆቅ እንደሚያድን የእስራኤልም ንጉሥ ቍንጫ ለመፈለግ ስለ ወጣ፣ ደሜ ከእግዚአብሔር ፊት ርቆ በምድር ላይ እንዲፈስ አታድርግ።”

21ሳኦልም፣ “በድያለሁ፤ ልጄ ዳዊት ሆይ፤ ተመለስ፤ ዛሬ ነፍሴ በፊትህ ስለ ከበረች፣ ከእንግዲህ ወዲያ አልጐዳህም፤ በርግጥ የሞኝ ሥራ ሠርቻለሁ፤ እጅግ ሲበዛም ተሳስቻለሁ” አለ።

22ዳዊትም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “የንጉሥ ጦር እነሆ፤ ከወጣቶችህ አንዱ መጥቶ ይውሰዳት። 23እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ ሰው እንደ ጽድቁና እንደ ታማኝነቱ ይክፈለው። እኔ ግን ዛሬ እግዚአብሔር አንተን በእጄ አሳልፎ ሰጥቶኝ ሳለ እግዚአብሔር በቀባው ላይ እጄን አላነሣሁም። 24እነሆ፤ ዛሬ ሕይወትህ በፊቴ እንደ ከበረች ሁሉ፣ የእኔም ሕይወት በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረች ትሁን፤ ከመከራም ሁሉ ያድነኝ።”

25ከዚያም ሳኦል ዳዊትን፣ “ልጄ ዳዊት ሆይ፤ የተባረክህ ሁን፤ ታላቅ ነገር ታደርጋለህ፤ በርግጥም ይከናወንልሃል” አለው።

ስለዚህም ዳዊት ወደሚሄድበት ሄደ፤ ሳኦልም ወደ ቤቱ ተመለሰ።

Swedish Contemporary Bible

1 Samuelsboken 26:1-25

David skonar Saul än en gång

1Männen från Sif gick nu till Saul i Giva och berättade att David gömde sig på Hakilahöjden mitt emot Jeshimon. 2Saul drog då i väg med sina 3 000 utvalda israelitiska soldater till Siföknen för att jaga honom. 3Han slog läger på Hakilahöjden längs vägen, mitt emot Jeshimon. David som befann sig i öknen förstod att Saul hade följt efter honom.

4David sände ut spejare och fick bekräftat att Saul verkligen kommit dit. 5Sedan gav han sig i väg till Sauls läger. Där såg han var kung Saul låg och sov bredvid sin härförare Avner, Ners son, längst inne i lägret, medan soldaterna låg runt omkring honom.

6”Vem av er vill följa med mig dit in till Sauls läger?” frågade David hettiten Achimelek och Avishaj, Serujas son, Joavs26:6 Joav och Avishaj var Davids systersöner. Joav blev senare ledare för hela Israels armé. bror. ”Jag går med dig”, sa Avishaj. 7Och så gick David och Avishaj till hären på natten, där de fann Saul sovande med spjutet nerstucket i marken nära huvudet. Avner och soldaterna låg runt omkring honom.

8”Gud har nu utlämnat din fiende åt dig”, sa Avishaj till David. ”Låt mig få spetsa fast honom vid marken med mitt spjut! Jag lär inte behöva mer än ett försök.” 9”Nej!” sa David. ”Du får inte döda honom, för vem kan ostraffat angripa Herrens smorde?” 10David fortsatte: ”Så sant Herren lever, Herren kommer att slå honom: antingen dör han när hans tid är inne eller genom att han faller i strid. 11Herren förbjude att jag skulle lyfta min hand mot hans smorde! Men ta Sauls spjut som står vid hans huvud och hans vattenkruka, så går vi!” 12Och så tog David spjutet och vattenkrukan vid Sauls huvud. Sedan lämnade de lägret utan att någon sett dem. Ingen av Sauls män vaknade, för Herren lät dem sova tungt.

13När David efter en stund klättrat upp på bergssluttningen på andra sidan lägret och var på betryggande avstånd, 14ropade han mot hären och Avner, Ners son: ”Avner! Svara mig!” ”Vem är det som ropar på kungen?” frågade Avner.

15David svarade: ”Du är ju en man utan like i hela Israel. Varför vakar du då inte över din herre och kung, när någon kommer för att döda honom? 16Det är verkligen illa! Så sant Herren lever borde ni dö för att ni inte vakat över er herre, Herrens smorde. Säg mig nu, var är kungens spjut och var är vattenkrukan som stod vid hans huvud?”

17Då kände Saul igen Davids röst och ropade: ”Är det du, min son David?”

David svarade: ”Ja, herre, det är det, min herre och kung! 18Varför jagar du mig? Vad har jag gjort? Har jag gjort något ont? 19Lyssna nu på mig, din tjänare, du min herre och kung! Om det är Herren som har eggat upp dig mot mig, då tar han väl emot ett offer, men om det är människor som driver dig till det, så kommer Guds förbannelse att drabba dem. De har ju drivit mig från min arvedel i Herrens land och de har velat få mig till att tillbe andra gudar. 20Låt nu inte mitt blod utgjutas långt borta från Herrens närhet. Israels kung har ju dragit ut för att jaga en loppa som man jagar rapphöns bland bergen.”

21Då bekände Saul: ”Jag har syndat. Kom tillbaka hem, min son! Jag ska inte längre försöka skada dig, för du har räddat mitt liv i dag. Jag har gjort fel och handlat dåraktigt.”

22”Här är ditt spjut, herre”, svarade David. ”Låt en av dina unga män komma hit och hämta det! 23Herren belönar var och en efter hans rättfärdighet och trohet. Herren överlämnade dig åt mig i dag, men jag lyfte inte min hand mot Herrens smorde. 24Ditt liv var dyrbart för mig i dag, så må mitt liv på samma sätt vara dyrbart för Herren och må han rädda mig ur alla mina svårigheter!”

25Då sa Saul till David: ”Du ska vara välsignad, min son David! Du ska i framtiden utföra hjältedåd och vinna stora segrar!” Sedan gick David sin väg och Saul återvände hem.