1 ሳሙኤል 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 2:1-36

የሐና የምስጋና ጸሎት

1ሐናም እንዲህ ብላ ጸለየች፤

“ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፤

ቀንዴም2፥1 በዚህ ስፍራና በቍጥር 10 ላይ ቀንድ የጥንካሬ ምልክት ነው። በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤

አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤

በማዳንህ ደስ ይለኛልና።

2“እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ2፥2 ወይም አንድ ቅዱስ ማንም የለም፤

ከአንተም በቀር ሌላ የለም፤

እንደ አምላካችን ያለ ዐለት የለም።

3“ይህን ያህል በመታበይ አትናገሩ፤

እንዲህ ያለውም የእብሪት ቃል ከአፋችሁ አይውጣ፤

እግዚአብሔር አምላክ ዐዋቂ ነውና፤

ሥራም ሁሉ በእርሱ ይመዘናል።

4“የኀያላን ቀስቶች ተሰባብረዋል፤

ደካሞች ግን በኀይል ታጥቀዋል።

5ጠግበው የነበሩ ለእንጀራ ሲሉ ተገዙ፤

ተርበው የነበሩ ግን እንጀራ ጠገቡ፤

መካኒቱ ሰባት ልጆች ወልዳለች፤

ብዙ ወንዶች ልጆች ወልዳ የነበረችው ግን መከነች።

6እግዚአብሔር ይገድላል፤ ያድናልም፤

ወደ መቃብር2፥6 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል ያወርዳል፤ ያወጣልም።

7እግዚአብሔር ያደኸያል፤ ያበለጽጋልም፤

ያዋርዳል፤ ከፍ ከፍም ያደርጋል።

8እርሱ ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ምስኪኑንም ከጕድፍ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

ከመኳንንቱ ጋር ያስቀምጣቸዋል፤

የክብር ዙፋንም ያወርሳቸዋል።

“የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና፣

ዓለምን በእነርሱ ላይ አድርጓል።

9እርሱ የቅዱሳኑን እግር ይጠብቃል፤

ክፉዎች ግን በጨለማ ውስጥ ይጣላሉ።

“ሰው በኀይሉ ድል አያደርግም፤

10ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቃሉ፤

እርሱ ከሰማይ ያንጐደጕድባቸዋል፤

እግዚአብሔር እስከ ምድር ዳርቻ ይፈርዳል።

“ለንጉሡ ኀይልን ይሰጣል፤

የመሲሑንም ቀንድ ከፍ ከፍ ያደርጋል።”

11ከዚያ በኋላ ሕልቃና ወደ ቤቱ ወደ ራማ ሄደ፤ ብላቴናው ግን በካህኑ በዔሊ ፊት እግዚአብሔርን ያገለግል ነበር።

የዔሊ ልጆች ክፉ ድርጊት

12የዔሊ ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አይፈሩም ነበር። 13በዚያን ጊዜ ካህናቱ ከሕዝቡ ጋር ባላቸው ግንኙነት የሚፈጽሙት ወግ ነበር፤ ይኸውም ማንም ሰው መሥዋዕት በሚያቀርብበት ጊዜ፣ ሥጋው እየተቀቀለ ሳለ የካህኑ አገልጋይ ሦስት ጣት ያለውን ሜንጦ ይዞ ይመጣል፤ 14ወደ ድስቱ ወይም ወደ ቶፋው ወይም ወደ አፍላሉ፣ ወይም ወደ ምንቸቱ ይሰደዋል። ከዚያም ካህኑ ሜንጦው ያወጣውን ማናቸውንም ሥጋ ለራሱ ይወስደዋል። ወደ ሴሎ የሚመጡትን እስራኤላውያን ሁሉ የሚያስተናግዱት በዚህ ዐይነት ነበር። 15ነገር ግን ሥቡ ገና ከመቃጠሉ በፊት የካህኑ አገልጋይ መጥቶ መሥዋዕት የሚያቀርበውን ሰው፣ “ካህኑ ጥሬውን እንጂ የተቀቀለውን ሥጋ ከአንተ ስለማይቀበል፣ ለካህኑ የሚጠበስ ሥጋ ስጠኝ” ይለው ነበር።

16ሰውየውም፣ “በመጀመሪያ ሥቡ ይቃጠል፤ ከዚያ በኋላ የምትፈልገውን ትወስዳለህ” ቢለው እንኳ አገልጋዩ፣ “አይሆንም፤ አሁኑኑ ስጠኝ፤ ያለዚያ በግድ እወስዳለሁ” ይለው ነበር።

17ለእግዚአብሔር የሚቀርበውን መሥዋዕት ይንቁ ስለ ነበር2፥17 ወይም የሚንቁ ሰዎች ስለ ነበሩ፣ ይህ የወጣቶቹ ኀጢአት በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ታላቅ ነበረ።

18ብላቴናው ሳሙኤል ግን ከበፍታ የተሠራ ኤፉድ ለብሶ በእግዚአብሔር ፊት ያገለግል ነበር። 19እናቱም ከባሏ ጋር ዓመታዊ መሥዋዕት ለማቅረብ በምትሄድበት ጊዜ ሁሉ ትንሽ መደረቢያ እየሠራች ይዛለት ትሄድ ነበር። 20ዔሊም፣ “በጸሎት ባገኘችውና ለእግዚአብሔር በሰጠችው ልጅ ምትክ እግዚአብሔር ከዚህችው ሴት ዘር ይስጥህ” እያለ ሕልቃናንና ሚስቱን ይመርቃቸው ነበር፤ ከዚያ በኋላ ወደ ቤታቸው ይመለሱ ነበር። 21እግዚአብሔርም ሐናን ባረካት፤ ፀነሰችም፤ ሦስት ወንዶች፣ ሁለት ሴቶች ልጆችም ወለደች። ብላቴናውም ሳሙኤል በእግዚአብሔር ፊት አደገ።

22በዚህ ጊዜ ዔሊ እጅግ አርጅቶ ነበር፤ ልጆቹም በመላው እስራኤል ያደርጉ የነበረውን፣ በመገናኛውም ድንኳን ደጃፍ ከሚያገለግሉ ሴቶች ጋር ዝሙት መፈጸማቸውን ሰማ። 23ስለዚህም እንዲህ አላቸው፤ “ስለምትፈጽሙት ክፉ ድርጊት ከመላው ሕዝብ እሰማለሁ፤ ለምን እንዲህ ያለ ነገር ታደርጋላችሁ? 24ልጆቼ ሆይ፤ ትክክል አይደላችሁም፤ በእግዚአብሔር ሕዝብ መካከል ተሠራጭቶ የምሰማባችሁ ወሬ ጥሩ አይደለም። 25አንድ ሰው ሌላውን ቢበድል፣ እግዚአብሔር2፥25 ወይም መሳፍንት ጣልቃ ገብቶ ይፈርዳል፤ ነገር ግን ሰው እግዚአብሔርን ቢበድል፣ ማን ይማልድለታል?” ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ስለ ፈለገ፣ ልጆቹ የአባታቸውን ተግሣጽ አልሰሙም።

26ብላቴናውም ሳሙኤል በአካልና በሞገስ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት እያደገ ሄደ።

በዔሊ ቤተ ሰብ ላይ የተነገረ ትንቢት

27በዚህ ጊዜ አንድ የእግዚአብሔር ሰው ወደ ዔሊ መጥቶ እንዲህ አለው፤ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የአባትህ ቤት በግብፅ ምድር በፈርዖን እጅ በነበረ ጊዜ ራሴን ገለጥሁለት? 28የእኔ ካህን እንዲሆን፣ ወደ መሠዊያዬ እንዲወጣ፣ ዕጣን እንዲያጥን፣ በፊቴም ኤፉድ እንዲለብስ ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ አባትህን መረጥሁት። ደግሞም እስራኤላውያን በእሳት የሚያቀርቡትን ቍርባን ሁሉ ለአባትህ ቤት ሰጠሁ። 29ታዲያ በማደሪያዬ እንዲቀርብ ያዘዝሁትን መሥዋዕትና ቍርባን የናቃችሁ ለምንድን ነው? አንተና ልጆችህ ሕዝቤ እስራኤል ካቀረበው ቍርባን ሁሉ ምርጥ ምርጡን በልታችሁ ራሳችሁን በማወፈር ከእኔ ይልቅ ልጆችህን የምታከብራቸው ስለ ምንድን ነው?’

30“ስለዚህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ቤትህና የአባትህ ቤት በፊቴ ለዘላለም ያገለግሉኝ ዘንድ ተስፋ ሰጥቼ ነበር፤’ አሁን ግን እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ይህን ከእንግዲህ አላደርገውም፤ የሚያከብሩኝን አከብራለሁ፤ የሚንቁኝም ፈጽሞ ይናቃሉ። 31እነሆ፤ በዘርህ ሽማግሌ እንዳይገኝ ያንተን ኀይልና የአባትህን ቤተ ሰብ ኀይል የምሰብርበት ጊዜ ይመጣል፤ 32በማደሪያዬም መከራ ታያለህ፤ ምንም እንኳ ለእስራኤል በጎ ነገር ቢደረግም፣ በቤተ ሰብህ ውስጥ ሽማግሌ ፈጽሞ አይገኝም። 33ከመሠዊያዬ የማላስወግዳቸው ዘሮችህ በሕይወት የሚተርፉትም ዐይኖችህን በእንባ ለማፍዘዝ፣ ልብህን በሐዘን ለማደንዘዝ ብቻ ነው፣ ሌሎቹ ዘሮችህ ግን በሙሉ በለጋነታቸው በዐጭር ይቀጫሉ።

34“ ‘በሁለቱ ልጆችህ በአፍኒንና በፊንሐስ ላይ የሚደርሰው ላንተ ምልክት ይሆንሃል፣ ሁለቱም በአንድ ቀን ይሞታሉ። 35እንደ ልቤና እንደ አሳቤ የሚያገለግል የታመነ ካህን ለራሴ አስነሣለሁ፤ ቤቱን አጽንቼ አቆማለሁ፣ እርሱም በቀባሁት ፊት ለዘላለም ያገለግላል። 36ከዘሮችህም መካከል የተረፈው ማንኛውም ሰው፣ ለአንዲት ጥሬ ብርና ለቍራሽ እንጀራ ሲል በፊቱ ወድቆ ይሰግዳል፤ “የዕለት ጕርሴን እንዳገኝ እባክህ በማንኛውም የክህነት ሥራ ላይ መድበኝ” በማለት ይለምናል።’ ”

Thai New Contemporary Bible

1ซามูเอล 2:1-36

คำอธิษฐานของฮันนาห์

1แล้วนางฮันนาห์อธิษฐานว่า

“จิตใจของข้าพเจ้าปีติยินดีในองค์พระผู้เป็นเจ้า

ข้าพเจ้าได้รับการชูกำลังขึ้นในองค์พระผู้เป็นเจ้า2:1 หรือเขาของข้าพเจ้าได้รับการยกชูขึ้นในองค์พระผู้เป็นเจ้า

ริมฝีปากข้าพเจ้าข่มทับศัตรู

เพราะข้าพเจ้าชื่นชมในการช่วยกู้ของพระองค์

2“ไม่มีผู้ใดบริสุทธิ์สูงส่งเสมอเหมือนองค์พระผู้เป็นเจ้า

ไม่มีผู้ใดนอกจากพระองค์

ไม่มีศิลาใดเสมอเหมือนพระเจ้าของเรา

3“อย่าพูดโอหังอีกต่อไป

อย่าปริปากแสดงความจองหองเช่นนั้น

เพราะพระยาห์เวห์เป็นพระเจ้าผู้ทรงรอบรู้

และทรงเป็นผู้ชั่งดูการกระทำทั้งหลาย

4“คันธนูของนักรบก็ถูกหัก

แต่ผู้ที่ซวนเซได้รับการเสริมกำลัง

5บรรดาผู้ที่อิ่มหนำต้องออกรับจ้างเลี้ยงชีพ

แต่บรรดาผู้ที่หิวโหยไม่ต้องหิวโหยอีกต่อไป

หญิงหมันมีบุตรเจ็ดคน

แต่หญิงผู้มีบุตรหลายคนก็ร่วงโรยไป

6องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกำหนดให้ตายหรือให้มีชีวิต

พระองค์ทรงนำไปสู่แดนผู้ตายและให้เป็นขึ้นมา

7ความยากจนและความร่ำรวยมาจากองค์พระผู้เป็นเจ้า

พระองค์ทรงทำให้ต่ำลงและทรงยกชูขึ้น

8พระองค์ทรงยกชูผู้ยากไร้ขึ้นจากธุลี

ทรงยกคนขัดสนจากกองขี้เถ้า

พระองค์ทรงให้เขานั่งร่วมกับเจ้านาย

และให้เขาครองบัลลังก์อันทรงเกียรติ

“เพราะรากฐานของแผ่นดินโลกเป็นขององค์พระผู้เป็นเจ้า

พระองค์ทรงสถาปนาโลกไว้บนนั้น

9พระองค์จะทรงพิทักษ์ปกป้องย่างเท้าของประชากรของพระองค์

ส่วนคนชั่วร้ายจะนิ่งอึ้งอยู่ในความมืด

“คนเราชนะได้ไม่ใช่ด้วยพลัง

10บรรดาผู้ที่ต่อสู้กับองค์พระผู้เป็นเจ้าจะต้องกระจัดกระจายไป

พระองค์ทรงฟาดฟันพวกเขาด้วยฟ้าผ่าจากสวรรค์

องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงพิพากษาทั่วพิภพ

“พระองค์จะประทานกำลังแก่กษัตริย์ของพระองค์

และเชิดชูผู้ที่ทรงเจิมตั้งไว้”

11แล้วเอลคานาห์ก็กลับบ้านที่รามาห์ ส่วนเด็กน้อยซามูเอลปรนนิบัติรับใช้ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าภายใต้การดูแลของปุโรหิตเอลี

บุตรผู้ชั่วร้ายของเอลี

12บุตรชายทั้งสองของเอลีเป็นคนชั่ว ไม่เคารพยำเกรงองค์พระผู้เป็นเจ้า 13ทุกครั้งที่มีผู้ถวายเครื่องบูชา ขณะที่กำลังต้มเนื้อสัตว์ถวายบูชานั้น พวกเขามักจะสั่งคนรับใช้ให้เอาสามง่าม 14จิ้มลงในกระทะหรือในกาต้ม ในหม้อหรือในหม้อต้มใหญ่ อะไรติดขึ้นมาก็จะเอาไป เขาปฏิบัติเช่นนี้ต่ออิสราเอลทั้งปวงที่มายังชิโลห์ 15บางครั้งคนรับใช้ของปุโรหิตมาก่อนการเผาไขมันบนแท่นบูชา และบอกว่า “จงแบ่งเนื้อดิบให้ปุโรหิต เพราะท่านไม่รับเนื้อต้มจากเจ้า รับแต่เนื้อดิบเท่านั้น”

16หากผู้ถวายกล่าวว่า “ขอเผาไขมันให้เสร็จก่อน แล้วต้องการอะไรก็เอาไปเถิด” คนรับใช้ผู้นั้นจะกล่าวว่า “ไม่ได้ ต้องเอาเดี๋ยวนี้ ถ้าไม่ให้ เราจะใช้กำลัง”

17องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเห็นว่าบุตรทั้งสองของเอลีทำบาปใหญ่หลวง เพราะเขาปฏิบัติต่อเครื่องบูชาขององค์พระผู้เป็นเจ้าด้วยความดูหมิ่น

18ฝ่ายซามูเอลรับใช้อยู่ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าเป็นเด็กชายสวมเอโฟดลินิน 19มารดาทำเสื้อชุดเล็กๆ มาให้ทุกปีเมื่อนางมาพร้อมกับสามีเพื่อถวายเครื่องบูชาประจำปี 20เอลีจะอวยพรเอลคานาห์และภรรยาของเขาว่า “ขอให้องค์พระผู้เป็นเจ้าประทานบุตรอีกหลายคนจากหญิงคนนี้แก่ท่านแทนที่บุตรซึ่งนางได้ทูลขอและถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า” แล้วพวกเขาก็กลับบ้าน 21องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเมตตาฮันนาห์ นางตั้งครรภ์และมีบุตรชายสามคน บุตรสาวสองคน ซามูเอลก็เติบโตขึ้นต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า

22ฝ่ายเอลีซึ่งชรามากแล้ว ได้ยินทุกอย่างที่บุตรชายทำต่อปวงชนอิสราเอล และการที่พวกเขาหลับนอนกับผู้หญิงซึ่งมาปรนนิบัติที่ทางเข้าเต็นท์นัดพบ 23เอลีจึงกล่าวกับบุตรของตนว่า “ทำไมถึงทำอย่างนี้ พ่อได้ยินจากปากทุกคนว่าลูกทำตัวเลวทรามมาก 24อย่าทำเช่นนี้เลยลูกเอ๋ย เรื่องที่พ่อได้ยินคนขององค์พระผู้เป็นเจ้าพูดกันไปทั่วไม่มีเรื่องดีเลย 25ถ้าทำบาปกับเพื่อนมนุษย์ด้วยกัน พระเจ้า2:25 หรือตุลาการอาจจะไกล่เกลี่ยให้ แต่ถ้าทำบาปต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าใครจะช่วยอ้อนวอนแทนได้?” แต่พวกเขาไม่ฟังคำห้ามปรามของบิดา เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงดำริจะประหารพวกเขาอยู่แล้ว

26ส่วนเด็กชายซามูเอลเติบโตขึ้น เป็นที่โปรดปรานของทั้งองค์พระผู้เป็นเจ้าและคนทั้งหลาย

คำตัดสินพงศ์พันธุ์ของเอลี

27ครั้งนั้นคนของพระเจ้ามาพบเอลีและกล่าวว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘เราไม่ได้เปิดเผยตัวเองอย่างชัดเจนแก่วงศ์วานของบิดาของเจ้า เมื่อครั้งพวกเขาเป็นทาสของฟาโรห์อยู่ในอียิปต์หรอกหรือ? 28เราแยกบรรพบุรุษของเจ้าออกจากเผ่าอื่นๆ ของอิสราเอลมาเป็นปุโรหิตของเรา ให้มาที่แท่นบูชาของเรา เผาเครื่องหอมและสวมเอโฟดอยู่ต่อหน้าเรา และเราก็ได้ยกเครื่องบูชาด้วยไฟซึ่งอิสราเอลนำมาเผาถวายนั้นให้แก่วงศ์วานของบิดาของเจ้า 29เหตุใดพวกเจ้าจึงดูหมิ่นเครื่องบูชาและเครื่องถวายซึ่งเรากำหนดไว้เพื่อเราจะสถิตอยู่ด้วย? เหตุใดเจ้าจึงให้เกียรติลูกชายของเจ้ายิ่งกว่าเรา โดยขุนตัวเองจนอ้วนพีด้วยส่วนดีๆ ของเครื่องถวายบูชาทั้งปวงจากอิสราเอลประชากรของเรา?’

30“ฉะนั้นเรา พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลประกาศว่า ‘เราสัญญาไว้ว่าพงศ์พันธุ์ของเจ้าและของบิดาของเจ้าจะรับใช้อยู่ต่อหน้าเราตลอดไป’ แต่บัดนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า ‘ให้การนั้นห่างไกลจากเรา! เราจะให้เกียรติคนที่ให้เกียรติเรา และเราจะเหยียดหยามคนที่ดูหมิ่นเรา 31ใกล้จะถึงเวลาที่เราจะตัดเจ้าและวงศ์วานของบิดาของเจ้าออก จะไม่มีใครในครอบครัวของเจ้าที่แก่ตาย 32เจ้าจะริษยาความเจริญรุ่งเรืองซึ่งเราจะให้แก่อิสราเอล แต่เจ้ากับครอบครัวจะทุกข์ยากและขัดสน ไม่มีสักคนเดียวได้อยู่จนแก่เฒ่า 33ทุกคนในพวกเจ้าที่เราไม่ได้ตัดออกจากแท่นบูชาของเรา เราจะไว้ชีวิตเพียงเพื่อให้น้ำตานองหน้าและจิตใจทุกข์ระทม วงศ์วานทั้งปวงของเจ้าจะตายตั้งแต่วัยฉกรรจ์

34“ ‘และเพื่อเป็นหมายสำคัญแก่เจ้า โฮฟนีกับฟีเนหัสบุตรชายทั้งสองของเจ้าจะสิ้นชีวิตในวันเดียวกัน 35เราจะแต่งตั้งปุโรหิตที่ซื่อสัตย์ขึ้นเพื่อเราเอง ผู้ซึ่งจะทำตามความคิดและจิตใจของเรา เราจะสถาปนาวงศ์วานของเขาไว้ให้มั่นคง และเขาจะปรนนิบัติรับใช้อยู่ต่อหน้าผู้ที่เราเจิมตั้งไว้นั้นตลอดไป 36วงศ์วานทุกคนของเจ้าที่รอดชีวิตอยู่จะมาค้อมคำนับผู้นั้น แล้วร้องขอเศษเงินและอาหารว่า “โปรดมอบหมายงานปุโรหิตให้ข้าพเจ้าทำสักอย่างเถิด เพื่อข้าพเจ้าจะได้มีอาหารรับประทาน” ’ ”