1 ሳሙኤል 17 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 17:1-58

ዳዊትና ጎልያድ

1ፍልስጥኤማውያን ሰራዊታቸውን ለጦርነት አሰባስበው፣ በይሁዳ ምድር በሰኰት ላይ አከማቹ፤ እነርሱም በሰኰትና በዓዜቃ መካከል ባለው በኤፌሰደሚም ሰፈሩ። 2ሳኦልና እስራኤላውያን ተሰብስበው፣ በዔላ ሸለቆ ሰፈሩ፤ ፍልስጥኤማውያንንም ለመግጠም ቦታ ቦታቸውን ያዙ። 3ሸለቆ በመካከላቸው ሆኖ ፍልስጥኤማውያን አንዱን ኰረብታ እስራኤላውያን ደግሞ፣ ሌላውን ኰረብታ ያዙ።

4ከጌት የመጣ ቁመቱ ከዘጠኝ ጫማ በላይ የሆነ፣ ጎልያድ የተባለ አንድ ጀግና ከፍልስጥኤማውያን ሰፈር ወጣ። 5እርሱም ከናስ የተሠራ የራስ ቍር ደፍቶ፣ ክብደቱ አምስት ሺሕ ሰቅል የሆነ የናስ ጥሩር ለብሶ ነበር። 6በእግሮቹ ላይ የናስ ገምባሌ አድርጎ፣ በጫንቃው ላይ ደግሞ የናስ ጭሬ ይዞ ነበር። 7የጦሩም ዘንግ እንደ ሸማኔ መጠቅለያ የወፈረ፣ የጦሩም ብረት ስድስት መቶ ሰቅል ያህል የሚመዝን ነበር፤ ጋሻ ጃግሬውም ከፊት ከፊቱ ይሄድ ነበር።

8ጎልያድ ቆሞ ለተሰለፈው የእስራኤል ሰራዊት እንዲህ ሲል ጮኾ ተናገረ፤ “ለውጊያ ተሰልፋችሁ መውጣታችሁ ስለ ምንድን ነው? እኔ ፍልስጥኤማዊ፣ እናንተም የሳኦል አገልጋዮች አይደላችሁምን? አንድ ሰው ምረጡና እኔ ወደ አለሁበት ይውረድ፤ 9ከእኔ ጋር ሊዋጋና ሊገድለኝ ከቻለ፣ እኛ ባሪያዎቻችሁ እንሆናለን፤ እኔ ባሸንፈውና ብገድለው ግን እናንተ ባሪያዎቻችን ትሆናላችሁ፤ ትገዙልናላችሁ።” 10ከዚያም ፍልስጥኤማዊው፣ “ዛሬ የእስራኤልን ሰራዊት እገዳደራለሁ፤ እንዋጋ ዘንድ ሰው ስጡኝ” አለ። 11ሳኦልና እስራኤላውያን ሁሉ የፍልስጥኤማዊውን ቃል በሰሙ ጊዜ እጅግ ፈሩ፤ ደነገጡም።

12ዳዊት በይሁዳ የቤተ ልሔሙ ሰው የኤፍራታዊው የእሴይ ልጅ ነበር። እሴይ ስምንት ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ በሳኦልም ዘመን ያረጀና ዕድሜው የገፋ ሰው ነበር። 13ሦስቱ የእሴይ ታላላቅ ልጆች ሳኦልን ተከትለው ወደ ጦርነት ሄደው ነበር፤ እነርሱም ታላቁ ኤልያብ፣ ሁለተኛው አሚናዳብ፣ ሦስተኛውም ሣማ ይባላሉ፤ 14ዳዊት የሁሉም ታናሽ ነበር። ሦስቱ ታላላቅ ወንድሞቹ ሳኦልን ተከትለው ሄዱ፤ 15ዳዊት ግን የአባቱን በጎች ለመጠበቅ ከሳኦል ዘንድ ወደ ቤተ ልሔም ይመላለስ ነበር።

16ፍልስጥኤማዊውም አርባ ቀን ሙሉ ጧትና ማታ ፊት ለፊት ብቅ እያለ ቆሞ ይታያቸው ነበር።

17በዚህ ጊዜ እሴይ ልጁን ዳዊትን እንዲህ አለው፤ “ይህን ዐሥር ኪሎ የተጠበሰ እሸትና ዐሥር እንጀራ ለወንድሞችህ ይዘህ ወዳሉበት የጦር ሰፈር በቶሎ ድረስ። 18ይህንም ዐሥር የአይብ ጥፍጥፍ ለክፍል አዛዣቸው17፥18 ዕብራይስጡ ሻለቃ ይላል። አብረህ ውሰድ፤ ወንድሞችህም እንዴት እንደ ሆኑ አይተህ፣ ደኅንነታቸውን የሚያረጋግጥ ምልክት ከእነርሱ ዘንድ አምጣልኝ። 19እነርሱ ከሳኦልና ከእስራኤል ሰዎች ሁሉ ጋር ሆነው በዔላ ሸለቆ ከፍልስጥኤማውያን ጋር እየተዋጉ ናቸው።”

20ዳዊት በማለዳ በጎቹን ለጠባቂ ትቶ፣ እሴይ እንዳዘዘው ዕቃውን ይዞ ጕዞ ጀመረ። ልክ ሰራዊቱ እየፎከረ ለውጊያ ቦታ ቦታውን ለመያዝ በሚወጣበት ጊዜ ከጦሩ ሰፈር ደረሰ። 21እስራኤልና ፍልስጥኤማውያን ቦታ ቦታቸውን ይዘው ፊት ለፊት ተፋጠው ይጠባበቁ ነበር። 22ዳዊት ዕቃውን ከስንቅ ጠባቂው ዘንድ አስቀምጦ ወደ ጦሩ ግንባር ሮጠ፤ ወንድሞቹንም አግኝቶ ደኅንነታቸውን ጠየቀ። 23ከእነርሱም ጋር በሚነጋገርበት ጊዜ፣ ከጌት የመጣው ፍልስጥኤማዊው ጀግና ጎልያድ ከሰልፉ መካከል ወጥቶ እንደ ለመደው ሲደነፋ፤ ዳዊት ሰማ። 24እስራኤላውያንም ሰውየውን ባዩት ጊዜ ሁሉም በታላቅ ፍርሀት ከፊቱ ሸሹ።

25እስራኤላውያንም እርስ በርሳቸው “ይህ ሰው በየቀኑ እየመጣ እስራኤልን እንደሚገዳደር ታያላችሁ? ይህን ሰው ለሚገድል፣ ንጉሡ ብዙ ሀብት ይሰጠዋል፤ ሴት ልጁን ይድርለታል፣ የአባቱንም ቤት በእስራኤል ዘንድ ከግብር ነጻ ያደርገዋል” ይባባሉ ነበር።

26ዳዊት በአጠገቡ የቆሙትን ሰዎች፣ “ለመሆኑ ይህን ፍልስጥኤማዊ ገድሎ እንዲህ ያለውን ውርደት ከእስራኤል ለሚያስወግድ ሰው ምን ይደረግለታል? ደግሞስ የሕያው እግዚአብሔርን ሰራዊት ይገዳደር ዘንድ ይህ ያልተገረዘ ፍልስጥኤማዊ እርሱ ማነው?” ሲል ጠየቀ።

27እነርሱም፣ “ለሚገድለው ሰው የሚደረግለትማ ይህ ነው” ሲሉ አስቀድመው ያሉትን ደግመው ነገሩት።

28ታላቅ ወንድሙ ኤልያብ፣ ዳዊት ከሰዎች ጋር ሲነጋገር በሰማ ጊዜ እጅግ ተቈጥቶ፣ “ለምን ወደዚህ ወረድህ? እነዚያንስ ጥቂት በጎች በምድረ በዳ ለማን ተውሃቸው? ትዕቢትህንና የልብህን ክፋት ዐውቃለሁ፤ የመጣኸው ጦርነቱን ለማየት ብቻ ነው” አለው።

29ዳዊትም፣ “ታዲያ ምን አደረግሁ? መጠየቅ እንኳ አልችልም?” አለ። 30ከዚያም ወደ ሌላ ሰው ዘወር ብሎ፣ ያንኑ ጥያቄ ጠየቀ፤ ሰዎቹም እንደ ቀድሞው መለሱለት፤ 31ዳዊት የተናገረው ነገር ወደ ሳኦል ጆሮ ደረሰ፤ ሳኦልም ልኮ አስጠራው።

32ዳዊትም ሳኦልን፣ “ከዚህ ፍልስጥኤማዊ የተነሣ የማንም ሰው ልብ አይሸበር፤ ባሪያህ ሄዶ ይዋጋዋል” አለው።

33ሳኦልም መልሶ “አንተ ገና አንድ ፍሬ ልጅ ነህ፣ ሰውየው ግን ከልጅነቱ ጀምሮ ውጊያ የተለማመደ ስለሆነ፣ ወጥተህ ይህን ፍልስጥኤማዊ ልትገጥመው አትችልም” አለው።

34ዳዊት ግን ሳኦልን እንዲህ አለው፣ “አገልጋይህ የአባቱን በጎች በሚጠብቅበት ጊዜ፤ አንበሳ ወይም ድብ መጥቶ ከመንጋው አንድ በግ ነጥቆ ሲሄድ፣ 35ተከትዬ በመሄድ እመታውና ከአፉ አስጥል ነበር፤ ፊቱን ወደ እኔ በሚያዞርበትም ጊዜ ጕረሮውን ይዤ በመምታት እገድለው ነበር። 36ባሪያህ አንበሳውንም ድቡንም ገድሏል፤ ይህም ያልተገረዘ ፍልስጥኤማዊ የሕያው እግዚአብሔርን ሰራዊት ተገዳድሯልና መጨረሻው ከእነርሱ እንደ አንዱ ይሆናል። 37ከአንበሳ መዳፍና ከድብ መንጋጋ ያዳነኝ እግዚአብሔር አሁንም ከዚህ ፍልስጥኤማዊ እጅ ያድነኛል።”

ሳኦልም፣ “ሂድ፤ እግዚአብሔር ካንተ ጋር ይሁን” አለው።

38ከዚያም ሳኦል ለዳዊት የገዛ ራሱን የጦር ልብስ አለበሰው፤ ጥሩር አጠለቀለት፤ ከናስ የተሠራ ቍርም ደፋለት። 39ዳዊትም ይህን ዐይነት ልብስ ለብሶ ስለማያውቅ፣ ሰይፉን በጦር ልብሱ ላይ ታጥቆ ለመራመድ ሞከረ፤

እርሱም ሳኦልን፣ “ያልተለማመድሁት ስለሆነ እንደዚህ ሆኜ መራመድ አልችልም” አለው። ስለዚህ ሁሉንም አወለቀው። 40ከዚያም በትሩን በእጁ ያዘ፤ አምስት ድቡልቡል ድንጋዮች ከወንዝ መርጦ በእረኛ ኮረጆው ከጨመረ በኋላ፣ ወንጭፉን በእጁ ይዞ፣ ወደ ፍልስጥኤማዊው ቀረበ።

41ፍልስጥኤማዊውም፣ ጋሻ ጃግሬውን እፊት እፊቱ በማስቀደም፣ ወደ ዳዊት እየቀረበ መጣ። 42እርሱም ዳዊትን ትኵር ብሎ ሲያየው፣ ደም ግባት ያለው፣ መልከ መልካምና አንድ ፍሬ ልጅ ነበር፤ ስለዚህ ናቀው። 43ፍልስጥኤማዊውም ዳዊትን፣ “በትር ይዘህ የምትመጣብኝ እኔ ውሻ ነኝን?” አለው፤ በአማልክቱም ስም ረገመው። 44እርሱም፣ “እስቲ ወደኔ ና! ሥጋህን ለሰማይ አሞሮችና፣ ለምድር አራዊት እሰጣለሁ” አለው።

45ዳዊትም ፍልስጥኤማዊውን እንዲህ አለው፤ “አንተ ሰይፍ፣ ጦርና ጭሬ ይዘህ ትመጣብኛለህ፤ እኔ ግን አንተ በተገዳደርኸው የእስራኤል ሰራዊት አምላክ በሆነው፣ ሁሉን በሚችል በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ። 46እግዚአብሔር ዛሬ አንተን በእጄ አሳልፎ ይሰጣል፤ እኔ መትቼ እጥልሃለሁ፤ ራስህንም እቈርጠዋለሁ። በዚህች ዕለት የፍልስጥኤማውያንን ሰራዊት ሬሣ ለሰማይ አሞሮችና ለምድር አራዊት እሰጣለሁ፣ ዓለምም ሁሉ በእስራኤል ዘንድ አምላክ መኖሩን ያውቃል። 47እዚህ የተሰበሰቡትም ሁሉ፣ እግዚአብሔር የሚያድነው በሰይፍ ወይም በጦር እንዳልሆነ ያውቃሉ፤ ሰልፉ የእግዚአብሔር ስለ ሆነም ሁላችሁን በእጃችን አሳልፎ ይሰጣል።”

48ፍልስጥኤማዊው ሊመታው በቀረበ ጊዜ፣ ዳዊትም ሊገጥመው ወደ ውጊያው ሜዳ በፍጥነት ሮጠ። 49እጁንም ወደ ኮሮጆው በመስደድ አንድ ድንጋይ አውጥቶ ወነጨፈው፤ ፍልስጥኤማዊውንም ግንባሩ ላይ መታው። ድንጋዩም ግንባሩ ውስጥ ገብቶ ተቀረቀረ፤ ፍልስጥኤማዊውም በግምባሩ ተደፋ።

50በዚህ ሁኔታ ዳዊት በወንጭፍና በድንጋይ ብቻ ፍልስጥኤማዊውን አሸነፈው፤ በእጁም ሰይፍ ሳይዝ ፍልስጥኤማዊውን መታው፤ ገደለውም።

51ዳዊት ሮጦ በላዩ ላይ ቆመ፤ ከዚያም የፍልስጥኤማዊውን ሰይፍ ከሰገባው መዝዞ አወጣው፤ እርሱንም ከገደለው በኋላ ራሱን በሰይፍ ቈረጠው።

ፍልስጥኤማውያንም ጀግናቸው መሞቱን ባዩ ጊዜ ሸሹ። 52ከዚህ በኋላ የእስራኤልና የይሁዳ ሰዎች ተነሥተው እየፎከሩ ፍልስጥኤማውያንን እስከ ጌት መግቢያና እስከ ዔቅሮን በሮች ድረስ አሳደዷቸው። የፍልስጥኤማውያንም ሬሳ ከሸዓይራይም አንሥቶ እስከ ጌት17፥52 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን ሸለቆ ይላል። ከዚያም እስከ ዔቅሮን በሮች ባለው መንገድ ላይ ወድቆ ነበር። 53እስራኤላውያን ፍልስጥኤማውያንን ከማሳደድ ተመለሱ፤ ሰፈራቸውንም በዘበዙ። 54ዳዊትም የፍልስጥኤማዊውን ራስ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም አመጣው፤ ነገር ግን የፍልስጥኤማዊውን የጦር መሣሪያዎች በራሱ ድንኳን ውስጥ አስቀመጠ።

55ዳዊት ፍልስጥኤማዊውን ለመግጠም በሚሄድበት ጊዜ ሳኦል ተመልክቶ የሰራዊቱን አዛዥ አበኔርን፣ “አበኔር ሆይ፤ ይህ ልጅ የማን ነው?” ሲል ጠየቀው።

አበኔርም፣ “ንጉሥ ሆይ፤ በሕያው ነፍስህ እምላለሁ፤ አላውቅም” ብሎ መለሰለት።

56ንጉሡም፣ “እንግዲህ ወጣቱ የማን ልጅ እንደ ሆነ ተከታትለህ ድረስበት” አለው።

57ዳዊት ፍልስጥኤማዊውን ገድሎ እንደ ተመለሰ፣ አበኔር ይዞ ንጉሡ ዘንድ አቀረበው። በዚህ ጊዜ ዳዊት የጎልያድን ራስ በእጁ ይዞ ነበር።

58ሳኦልም፣ “አንተ ወጣት፣ የማን ልጅ ነህ?” ሲል ጠየቀው።

ዳዊትም፣ “እኔ የአገልጋይህ የቤተ ልሔሙ ሰው የእሴይ ልጅ ነኝ” ሲል መለሰ።

Thai New Contemporary Bible

1ซามูเอล 17:1-58

ดาวิดกับโกลิอัท

1ครั้งนั้นชาวฟีลิสเตียรวมพลมาสู้รบและชุมนุมกันที่โสโคห์ในยูดาห์ พวกเขาตั้งค่ายพักที่เอเฟสดัมมิมซึ่งอยู่ระหว่างโสโคห์กับอาเซคาห์ 2ซาอูลและชนอิสราเอลมารวมพลและตั้งค่ายพักอยู่ที่หุบเขาเอลาห์ ตั้งแนวรบประจันหน้ากับชาวฟีลิสเตีย 3ชาวฟีลิสเตียยึดเนินเขาด้านหนึ่ง อิสราเอลยึดเนินเขาอีกด้านหนึ่ง มีหุบเขาคั่นกลาง

4ยอดนักรบชื่อโกลิอัทจากเมืองกัทออกมาจากค่ายฟีลิสเตีย เขาสูง 6 ศอกกับ 1 ฝ่ามือ17:4 คือ สูงประมาณ 3 เมตร 5เขาสวมหมวกเกราะทองสัมฤทธิ์และสวมเสื้อเกราะทองสัมฤทธิ์หนักประมาณ 57 กิโลกรัม17:5 ภาษาฮีบรูว่า 5,000 เชเขล 6ใส่สนับแข้งทองสัมฤทธิ์ มีหอกทองสัมฤทธิ์คล้องอยู่ที่บ่า 7ด้ามหอกเหมือนไม้กระพั่นทอผ้า ปลายหอกทำด้วยเหล็กหนักประมาณ 7 กิโลกรัม17:7 ภาษาฮีบรูว่า 600 เชเขล มีคนแบกโล่เดินนำหน้า

8โกลิอัทยืนร้องท้าทหารอิสราเอลว่า “พวกเจ้าจะมาตั้งแถวสู้รบกันทำไม? ข้าก็เป็นฟีลิสเตีย ส่วนพวกเจ้าก็เป็นบริวารของซาอูลไม่ใช่หรือ? จงเลือกคนหนึ่งลงมาสู้กับข้า 9ถ้าคนของเจ้าฆ่าข้าได้ พวกข้าจะยอมแพ้พวกเจ้า แต่ถ้าข้าชนะและฆ่าเขาได้ พวกเจ้าต้องยอมแพ้เป็นทาสรับใช้พวกข้า” 10ชาวฟีลิสเตียคนนั้นพูดว่า “วันนี้ข้าขอท้ากองทัพอิสราเอล! ส่งคนมาสู้กับข้าสิ” 11เมื่อซาอูลและชนอิสราเอลทั้งหมดได้ยินเช่นนี้ ก็พากันหวาดผวาและท้อแท้ใจ

12ฝ่ายดาวิดเป็นบุตรเจสซีชาวถิ่นเอฟราธาห์จากเบธเลเฮมในเขตยูดาห์ เจสซีมีบุตรชายแปดคน เขาก็ชราและมีอายุมากแล้วในสมัยที่ซาอูลเป็นกษัตริย์ 13บุตรชายสามคนแรกของเจสซีที่ติดตามซาอูลไปรบมีดังนี้คือ เอลีอับบุตรหัวปี อาบีนาดับบุตรคนที่สอง และชัมมาห์บุตรคนที่สาม 14ดาวิดเป็นบุตรคนสุดท้อง พี่ชายสามคนแรกติดตามซาอูลไป 15ส่วนดาวิดไปๆ มาๆ ระหว่างซาอูลกับการเลี้ยงแกะของบิดาที่เบธเลเฮม

16ชาวฟีลิสเตียคนนี้มายืนร้องท้าเป็นประจำทุกเช้าเย็นตลอดสี่สิบวัน

17ฝ่ายเจสซีพูดกับดาวิดบุตรชายว่า “จงรีบเอาข้าวคั่วประมาณ 22 ลิตร17:17 ภาษาฮีบรูว่า 1 เอฟาห์กับขนมปังสิบก้อนนี้ไปให้พี่ชายของเจ้าที่ค่าย 18เอาเนยแข็งสิบชิ้นนี้ไปให้ผู้บังคับกอง17:18 ภาษาฮีบรูว่ากองพันของพี่ๆ ด้วย จงดูว่าพวกพี่เป็นอย่างไรกันบ้าง แล้วนำข่าว17:18 หรือของฝากหรือของที่ริบได้จากพวกเขากลับมาบอกเราด้วย 19พวกเขาอยู่กับซาอูลและกองทัพอิสราเอลที่หุบเขาเอลาห์ระหว่างการสู้รบกับคนฟีลิสเตีย”

20ดาวิดทิ้งฝูงแกะไว้กับคนเลี้ยงอีกคนหนึ่ง แล้วออกเดินทางตามคำสั่งของเจสซีตั้งแต่เช้าตรู่ของวันรุ่งขึ้นพร้อมด้วยของฝาก เขามาถึงค่ายพอดีกับที่กองทัพอิสราเอลกำลังจะยกออกไปสนามรบ มีเสียงตะโกนเสียงโห่ร้องออกศึก 21กองพลอิสราเอลและฟีลิสเตียต่างก็มาตั้งขบวนประจันหน้ากัน 22ดาวิดทิ้งข้าวของไว้กับเจ้าหน้าที่ผู้ดูแลสัมภาระ แล้ววิ่งออกไปที่แนวรบและทักทายพวกพี่ๆ 23ขณะกำลังคุยกับพวกพี่ๆ โกลิอัทยอดนักรบชาวฟีลิสเตียจากเมืองกัทก้าวออกจากแถวมายืนร้องท้าเช่นเคย และดาวิดก็ได้ยิน 24ทันทีที่เห็นโกลิอัทคนอิสราเอลก็พากันวิ่งหนีด้วยความกลัวยิ่งนัก

25คนอิสราเอลพูดกันว่า “เจ้าเห็นคนนี้ไหม? เขาออกมาสบประมาทอิสราเอลอยู่เป็นประจำ กษัตริย์จะประทานทรัพย์สินมากมายให้แก่คนที่ฆ่าเขาได้ และจะยกพระธิดาให้เป็นภรรยา ยิ่งกว่านั้นครอบครัวของบิดาของเขาจะได้รับการยกเว้นภาษีด้วย”

26ดาวิดถามคนที่ยืนอยู่ใกล้ๆ ว่า “ผู้ที่ฆ่าฟีลิสเตียคนนี้และกู้หน้าให้อิสราเอลจะได้รับบำเหน็จอะไรบ้าง? ชาวฟีลิสเตียผู้ไม่ได้เข้าสุหนัตคนนี้เป็นใครกัน ถึงบังอาจมาร้องท้ากองทัพของพระเจ้าผู้ทรงพระชนม์อยู่?”

27พวกเขาก็บอกซ้ำสิ่งที่พูดไปแล้วว่า “คนที่ฆ่าเขาสำเร็จจะได้รับสิ่งต่างๆ ดังกล่าว”

28เมื่อเอลีอับพี่ชายคนโตของดาวิดได้ยินดาวิดพูดกับคนนั้นก็โกรธ และถามว่า “เจ้ามาทำอะไรที่นี่ แล้วเจ้าทิ้งแกะไม่กี่ตัวในถิ่นกันดารไว้ให้ใครดูแล? ข้ารู้ว่าเจ้าชอบคุยโวและรู้จักใจชั่วช้าของเจ้า นึกอยากมาดูเขารบกันล่ะสิ”

29ดาวิดตอบว่า “ข้าทำอะไรผิดหรือ? ถามดูไม่ได้หรือ?” 30แล้วดาวิดเดินไปถามคนอื่นๆ อีกในเรื่องเดิม ก็ได้รับคำตอบอย่างเดียวกัน 31มีผู้ได้ยินคำพูดของดาวิดจึงไปทูลรายงานซาอูล พระองค์จึงให้คนไปตามตัวดาวิดมาเข้าเฝ้า

32ดาวิดทูลซาอูลว่า “อย่าให้ผู้ใดเสียขวัญเพราะชาวฟีลิสเตียคนนี้เลย ผู้รับใช้ของฝ่าพระบาทจะไปรบกับเขา”

33ซาอูลตรัสว่า “เจ้าออกไปสู้กับชาวฟีลิสเตียคนนั้นไม่ได้หรอก เจ้าเป็นเพียงเด็ก ส่วนเขาเป็นนักรบมาตั้งแต่หนุ่ม”

34แต่ดาวิดทูลซาอูลว่า “ข้าพระบาทดูแลแกะของบิดา เมื่อมีสิงโตหรือหมีมาคาบแกะไปจากฝูง 35ข้าพระบาทจะไล่ตามฟาดฟันช่วยแกะนั้นออกมาจากปากของสิงโต หากมันหันมาเล่นงาน ข้าพระบาทก็จะกระชากขนของมัน ฟาดมัน และฆ่าเสีย 36ผู้รับใช้ของฝ่าพระบาทได้ฆ่าทั้งสิงโตและหมีมาแล้ว ชาวฟีลิสเตียผู้ไม่ได้เข้าสุหนัตคนนี้จะเป็นเหมือนสัตว์เหล่านั้น เพราะเขามาสบประมาทกองทัพของพระเจ้าผู้ทรงพระชนม์อยู่ 37องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงช่วยข้าพระบาทจากเขี้ยวเล็บของสิงโตและหมี จะช่วยข้าพระบาทจากมือชาวฟีลิสเตียผู้นี้”

ซาอูลตรัสกับดาวิดว่า “ไปเถิด ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าสถิตกับเจ้า”

38จากนั้นซาอูลก็ให้ดาวิดสวมเครื่องทรงของซาอูลเอง มีเสื้อเกราะและหมวกเกราะทองสัมฤทธิ์ 39ดาวิดสะพายดาบ ทับเสื้อเกราะ ลองเดินวนไปรอบๆ เพราะไม่คุ้นเคยกับชุดแบบนี้มาก่อน

ดาวิดทูลซาอูลว่า “ข้าพระบาทออกไปอย่างนี้ไม่ได้เพราะไม่เคยชิน” แล้วดาวิดก็ถอดชุดนั้นออก 40จากนั้นเขาหยิบไม้เท้าและไปเก็บหินเกลี้ยงห้าก้อนจากลำธารใส่ไว้ในย่ามของเขา ในมือถือสลิง เดินเข้าไปหาชาวฟีลิสเตียคนนั้น

41ขณะนั้นโกลิอัทเดินเข้ามาหาดาวิด มีคนแบกโล่เดินนำหน้า 42เมื่อเห็นดาวิดซึ่งเป็นเพียงเด็กหนุ่มรูปหล่อผิวพรรณดี ก็นึกดูหมิ่น 43และกล่าวว่า “เห็นข้าเป็นหมาหรือไง ถึงได้ถือไม้เท้าออกมาหา?” แล้วก็แช่งด่าดาวิดโดยอ้างนามเทพเจ้าต่างๆ ของตน 44โกลิอัทพูดว่า “มาสิ เดี๋ยวข้าจะแล่เนื้อเจ้าให้นกกาและสัตว์ป่ากิน!”

45ดาวิดพูดว่า “ท่านถือดาบ ถือหอก และหอกซัดมาสู้กับเรา ส่วนเราจะสู้กับท่านในพระนามพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ พระเจ้าของกองทัพอิสราเอลซึ่งท่านลบหลู่ 46วันนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงมอบท่านแก่เรา เราจะฆ่าและตัดหัวท่าน วันนี้เราจะเอาซากศพของกองทัพฟีลิสเตียให้นกกาและสัตว์ป่ากิน แล้วทั้งโลกจะได้รู้ว่ามีพระเจ้าในอิสราเอล 47คนทั้งปวงที่ชุมนุมกันอยู่ที่นี่จะได้รู้ว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ได้ทรงช่วยให้รอดด้วยดาบหรือหอก การศึกครั้งนี้เป็นขององค์พระผู้เป็นเจ้าพระองค์จะทรงมอบเจ้าทุกคนไว้ในมือของพวกเรา”

48ขณะที่โกลิอัทเข้ามาใกล้เพื่อต่อสู้ ดาวิดก็วิ่งเข้าไปประจันหน้า 49เอามือล้วงลงไปในย่ามหยิบก้อนหินออกมาคล้องเข้ากับสลิง แล้วเหวี่ยงก้อนหินอัดเข้าที่หน้าผากของโกลิอัท ก้อนหินฝังจมเข้าไป โกลิอัทล้มคว่ำลงกับพื้น

50เป็นอันว่าดาวิดพิชิตชาวฟีลิสเตียคนนั้นด้วยสลิงและก้อนหิน แม้ไม่มีดาบแต่ก็ล้มเขาได้และฆ่าเขาเสีย

51ดาวิดวิ่งขึ้นไปยืนบนร่างของเขา ดึงดาบของโกลิอัทออกจากฝักและฆ่าเขา แล้วก็ตัดศีรษะออกมา

เมื่อชาวฟีลิสเตียเห็นวีรบุรุษของตนตายเสียแล้ว ก็หันหลังวิ่งหนีไป 52คนอิสราเอลและยูดาห์จึงโห่ร้องมีชัย แล้วรุกไล่ฟีลิสเตียไปไกลถึงทางเข้าเมืองกัท17:52 ภาษาฮีบรูว่าทางเข้าหุบเขาแห่งหนึ่งและประตูเมืองเอโครน ศพชาวฟีลิสเตียเกลื่อนกลาดตลอดเส้นทางชาอาราอิมที่จะไปยังเมืองกัทและเมืองเอโครน 53หลังจากนั้นอิสราเอลก็กลับมาปล้นค่ายของชาวฟีลิสเตีย 54ดาวิดนำศีรษะของโกลิอัทไปยังเยรูซาเล็ม และเก็บอาวุธของเขาไว้ในเต็นท์ของตน

55ขณะซาอูลทอดพระเนตรดาวิดออกไปสู้กับโกลิอัท พระองค์ตรัสถามแม่ทัพอับเนอร์ว่า “อับเนอร์ เด็กหนุ่มคนนั้นเป็นลูกเต้าเหล่าใคร?”

อับเนอร์ทูลตอบว่า “ข้าแต่กษัตริย์ พระองค์ทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด ข้าพระบาทไม่ทราบฉันนั้น”

56ซาอูลตรัสว่า “ไปสืบมาสิว่าชายหนุ่มคนนี้เป็นลูกของใคร”

57ทันทีที่ดาวิดกลับจากสังหารโกลิอัท อับเนอร์นำตัวเขามาเข้าเฝ้าซาอูล ดาวิดยังหิ้วศีรษะของโกลิอัทอยู่

58ซาอูลตรัสถามว่า “พ่อหนุ่ม เจ้าเป็นลูกเต้าเหล่าใคร?”

ดาวิดทูลว่า “ข้าพระบาทเป็นบุตรของเจสซีแห่งเบธเลเฮม ผู้รับใช้ของฝ่าพระบาท”