1 ሳሙኤል 13 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 13:1-23

ሳሙኤል ሳኦልን መገሠጹ

1ሳኦል በነገሠ ጊዜ ዕድሜው ሠላሳ13፥1 ጥንታዊ ያልሆኑ ጥቂት የሰብዓ ሊቃናት ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን ሠላሳ የሚለውን አይጨምርም ዓመት ነበረ፤ እስራኤልንም አርባ13፥1 የዐሥር ብዜት የሆኑት ቍጥሮች በተመለከተ ሐሥ 13፥21 ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን አርባ የሚለውን አይጨምርም። ሁለት ዓመት ገዛ።

2ሳኦል13፥2 ወይም እርሱ በእስራኤል ላይ ለሁለት ዓመት ከነገሠ በኋላ ከእስራኤል ሦስት ሺሕ ሰዎች መረጠ። ሁለቱ ሺሕ በማክማስና በኰረብታማው አገር በቤቴል ከሳኦል ጋር፣ አንዱ ሺሕ ደግሞ በብንያም ግዛት በጊብዓ ከዮናታን ጋር ነበሩ። የቀሩትን ሰዎች ግን ወደየቤታቸው እንዲሄዱ አሰናበተ።

3ዮናታን ጊብዓ የነበረውን የፍልስጥኤማውያን ጦር ሰፈር መታ፤ ፍልስጥኤማውያንም ይህን ሰሙ። ሳኦልም፣ “ዕብራውያን ይስሙ!” በማለት በምድሪቱ ሁሉ መለከት አስነፋ። 4ስለዚህ እስራኤላውያን ሁሉ፣ “ሳኦል የፍልስጥኤማውያንን ጦር ሰፈር መታ፤ እስራኤልም በፍልስጥኤማውያን ዘንድ እንደ ርኩስ ተቈጥራ ተጠላች” የሚለውን ወሬ ሰሙ፤ ሕዝቡም ሳኦልን ለመከተል ወደ ጌልገላ ተሰበሰቡ።

5ፍልስጥኤማውያን ሦስት13፥5 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞችና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን ሠላሳ ሺሕ ይላል። ሺሕ ሠረገሎች፣ ስድስት ሺሕ ፈረሰኞች ቍጥሩ እንደ ባሕር አሸዋ የበዛ ሰራዊት ይዘው እስራኤልን ለመውጋት ተሰበሰቡ፤ ወጥተውም ከቤት አዌን በስተ ምሥራቅ ባለችው በማክማስ ሰፈሩ። 6እስራኤላውያን፣ ያሉበት ሁኔታ እጅግ የሚያሠጋ መሆኑንና ሰራዊታቸውም በከባድ ጭንቀት ውስጥ መግባቱን ባዩ ጊዜ፣ በየዋሻውና በየቍጥቋጦው፣ በየዐለቱ መካከልና በየገደሉ እንዲሁም በየጕድጓዱ ሁሉ ተደበቁ። 7ከዕብራውያንም አንዳንዶቹ ዮርዳኖስን ተሻግረው ወደ ጋድና ወደ ገለዓድ ምድር ሄዱ።

ሳኦል ግን በጌልገላ ቈየ፣ አብሮት የነበረውም ሰራዊት ሁሉ በፍርሀት ይንቀጠቀጥ ነበር። 8እርሱም ሳሙኤል በሰጠው ቀጠሮ መሠረት ሰባት ቀን ጠበቀው። ነገር ግን ሳሙኤል ወደ ጌልገላ አልመጣም፤ የሳኦልም ሰራዊት መበታተን ጀመረ። 9በዚህ ጊዜ ሳኦል፣ “የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕቱን13፥9 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። አምጡልኝ” አለ። ከዚያም የሚቃጠለውን መሥዋዕት አቀረበ። 10ልክ መሥዋዕቱን አቅርቦ እንዳበቃ፣ ወዲያውኑ ሳሙኤል መጣ፤ ሳኦልም ሊቀበለው ወጣ።

11ሳሙኤልም፣ “ያደረግኸው ምንድን ነው?” ሲል ጠየቀው።

ሳኦልም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ሰራዊቱ መበታተኑን፣ አንተም በቀጠርኸው ጊዜ አለመምጣትህን፣ ፍልስጥኤማውያንም በማክማስ መሰብሰባቸውን አየሁ፤ 12‘ስለዚህ ፍልስጥኤማውያን ወርደው ወደ ጌልገላ ይመጡብኛል፤ እኔም የእግዚአብሔርን ሞገስ አልለመንሁም’ ብዬ አሰብሁ። ስለዚህ የሚቃጠል መሥዋዕት ማቅረብ ግድ ሆነብኝ።”

13ሳሙኤልም እንዲህ አለ፤ “የማይገባህን አደረግህ፤ አምላክህ እግዚአብሔር የሰጠህን ትእዛዝ አልጠበቅህም፤ ጠብቀኸው ቢሆን ኖሮ፣ መንግሥትህን በእስራኤል ላይ ለዘላለም ባጸናልህ ነበር፤ 14አሁን ግን መንግሥትህ አይጸናም፤ እነሆ፣ እግዚአብሔር እንደ ልቡ የሚሆንለትን ሰው አግኝቷል፤ አንተ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ባለመጠበቅህም፣ እርሱን የሕዝቡ መሪ አድርጎ መርጦታል።”

15ከዚያ በኋላ ሳሙኤል ከጌልገላ ተነሥቶ13፥15 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ ከጌልገላ ተነሥተው ወደ መንገድ ሄዱ፤ ከጦሩ ጋር ለመገናኘት የተቀረው ሕዝብ ሳኦልን ተከተለ፤ ከጌልገላም ወጥቶ ሄደ ይላል። በብንያም ግዛት ወዳለው ወደ ጊብዓ ወጣ። ሳኦልም አብረውት የነበሩትን ሰዎች ቈጠራቸው፤ ብዛታቸውም ስድስት መቶ ያህል ነበረ።

እስራኤል ያለ ጦር መሣሪያ

16ፍልስጥኤማውያን በማክማስ ሰፍረው በነበረበት ጊዜ ሳኦል፣ ልጁ ዮናታንና አብረዋቸው የነበሩት ሰዎች በብንያም ግዛት በምትገኘው በጊብዓ ነበሩ። 17በሦስት ምድብ የተከፈሉ ወራሪዎች ከፍልስጥኤማውያን ሰፈር ወጡ፤ አንዱ ምድብ በሦጋል ግዛት ወደሚገኘው ወደ ዖፍራ አቀና፤ 18ሌላው ወደ ቤትሖሮን፣ ሦስተኛው ደግሞ በምድረ በዳው ትይዩ ካለው ከስቦይም ሸለቆ ቍልቍል ወደሚያሳየው ድንበር ዞረ።

19ፍልስጥኤማውያን፣ “ዕብራውያን ሰይፍ ወይም ጦር ለራሳቸው አይሥሩ” ብለው ስለ ነበር፣ በመላው የእስራኤል ምድር ብረት ቀጥቃጭ አልተገኘም። 20ስለዚህ እስራኤላውያን ሁሉ፣ ማረሻቸውንና ዶማቸውን ለማሾል፣ ጠገራቸውንና ማጭዳቸውን ለማሳል ወደ ፍልስጥኤማውያን ይወርዱ ነበር። 21ማረሻና ዶማ ለማሾል የሚከፈለው ዋጋ ሁለት ሦስተኛ ሰቅል13፥21 በዕብራይስጡ፣ ፒም ይባላል፤ 8 ግራም ያህል ነው ሲሆን፣ መንሽና ጠገራ እንዲሁም የበሬ መንጃ ለማሾል ደግሞ አንድ ሦስተኛ ሰቅል13፥21 4 ግራም ያህል ነው። ነበር።

22ስለዚህ ጦርነቱ በተደረገበት ዕለት ከሳኦልና ከልጁ ከዮናታን በስተቀር፣ አብረዋቸው ከነበሩት ወታደሮች መካከል ሰይፍ ወይም ጦር የያዘ አንድም ሰው አልነበረም።

ዮናታን በፍልስጥኤማውያን ላይ አደጋ መጣሉ

23በዚያ ጊዜ አንድ የፍልስጥኤማውያን ጭፍራ ወደ ማክማስ መተላለፊያ ወጥቶ ነበር።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

撒母耳记上 13:1-23

扫罗犯罪

1扫罗四十岁13:1 希伯来文无“四十岁”,一些七十士希腊文译本有此数字。登基。他在统治以色列的第二年, 2以色列人中选出三千人,亲自带领其中的两千人到密抹伯特利山,另外一千人和约拿单留在便雅悯境内的基比亚。他把其余的人遣散回家。 3约拿单攻打迦巴非利士驻军,非利士人听到了这消息。于是,扫罗在各地吹响号角,通告希伯来人。 4以色列众人听说扫罗攻打非利士人的驻军,并听说非利士人对以色列人恨之入骨,便响应扫罗的号召,聚集在吉甲5非利士人调兵遣将,要攻打以色列。他们有三万辆战车和六千骑兵,步兵多如海边的沙。大军来到伯·亚文以东的密抹,驻扎在那里。 6以色列人看见敌军压境,情势危急,纷纷躲进山洞、丛林、石穴、地洞和坑里。 7有些希伯来人过了约旦河,逃到迦得基列。但扫罗仍然留在吉甲,跟随他的人都害怕得发抖。

8扫罗按着撒母耳所定的日期在吉甲等了七天,可是撒母耳还没有来。扫罗的军兵开始溜走。 9于是,扫罗说:“你们把燔祭和平安祭带到我这里来”。他就献上了燔祭。 10扫罗刚把燔祭献完,撒母耳就来了,扫罗出去迎接他,向他问安。 11撒母耳扫罗说:“你做的是什么事?”扫罗答道:“我看见手下的人不断离我而去,你到了约定的时候还没有来,而且非利士人就聚集在密抹12我想非利士人就要到吉甲来攻打我们了,但我们还没有向耶和华求助,我迫不得已,就献上燔祭了。” 13撒母耳说:“你真糊涂!你违背了你的上帝耶和华的命令。祂本来要使你的王位在以色列永远坚立, 14但现在你的王位不能长久了,耶和华已经找到一个合祂心意的人,要立他做百姓的君王。因为你没有遵守耶和华的命令。” 15撒母耳离开吉甲便雅悯境内的基比亚扫罗数了一下跟随他的人,约有六百人。

16扫罗及其儿子约拿单和随从留在便雅悯境内的迦巴非利士人则在密抹扎营。 17非利士人分成三队施行突袭,一队前往书亚境内的俄弗拉18一队前往伯·和仑,一队前往边境地区,那里可以俯瞰旷野附近的洗波音谷。

19那时,以色列全境找不到一个铁匠,这是因为非利士人的禁令,以免希伯来人制造刀枪。 20以色列人都要到非利士的铁匠那里去磨锄、犁、斧和铲。 21磨锄或犁要花八克银子,磨三齿叉、斧头或赶畜棒要花四克银子。 22所以在交战的日子,除了扫罗约拿单外,其他以色列人手上都没有刀枪。 23当时非利士的一队防兵前往密抹的隘口驻守。