ፊልጵስዩስ 1 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ፊልጵስዩስ 1:1-30

1የክርስቶስ ኢየሱስ አገልጋዮች የሆኑ ጳውሎስና ጢሞቴዎስ፤

ከቤተ ክርስቲያን ኤጲስ ቆጶሳትና1፥1 ወይም ተመልካች ጠባቂዎች ከዲያቆናት ጋር በፊልጵስዩስ ላሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ቅዱሳን ለሆኑ ሁሉ፤

2ከእግዚአብሔር ከአባታችን፣ ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

ምስጋናና ጸሎት

3እናንተን ባስታወስሁ ቍጥር አምላኬን አመሰግናለሁ። 4ዘወትር ስለ ሁላችሁ ስጸልይ፣ በደስታ እጸልያለሁ፤ 5ከመጀመሪያው ቀን አንሥቶ እስካሁን ድረስ በወንጌል አገልግሎት ተካፋይ ሆናችኋልና። 6በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እርሱ እስከ ክርስቶስ ኢየሱስ ቀን ድረስ ከፍጻሜው እንደሚያደርሰው ርግጠኛ ነኝ።

7በልቤ ስላላችሁ፣ ስለ ሁላችሁ እንዲህ ማሰቤ ተገቢ ነው፤ በእስራቴም ሆነ ለወንጌል ስመክትና ሳጸናው ሁላችሁም ከእኔ ጋር የእግዚአብሔር ጸጋ ተካፋዮች ናችሁና። 8በክርስቶስ ኢየሱስ ፍቅር ሁላችሁንም ምን ያህል እንደምናፍቃችሁ እግዚአብሔር ምስክሬ ነው።

9ፍቅራችሁ በጥልቅ ዕውቀትና በማስተዋል ሁሉ በዝቶ እንዲትረፈረፍ እጸልያለሁ። 10ይኸውም ከሁሉ የሚሻለውን ለይታችሁ እንድታውቁ፣ እስከ ክርስቶስም ቀን ድረስ ንጹሓንና ነቀፋ የሌለባችሁ እንድትሆኑ፣ 11ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሚገኘው የጽድቅ ፍሬ እንድትሞሉ ነው።

በጳውሎስ እስራት ወንጌል መስፋፋቱ

12አሁንም ወንድሞች ሆይ፤ በእኔ ላይ የደረሰው ነገር ወንጌል በይበልጥ እንዲስፋፋ መርዳቱን ታውቁ ዘንድ እወድዳለሁ። 13ከዚህ የተነሣ እስራቴ ስለ ክርስቶስ እንደ ሆነ፣ በቤተ መንግሥት ዘበኞችና1፥13 ወይም በቤተ መንግሥት ሁሉ በሌሎችም ሁሉ ዘንድ ታውቋል። 14በእኔ መታሰር ምክንያት በጌታ ካሉት ወንድሞች ብዙዎቹ የእግዚአብሔርን ቃል ያለ ፍርሀት፣ በድፍረት ለመናገር ብርታት አግኝተዋል።

15አንዳንዶች ከቅናትና ከፉክክር የተነሣ፣ ሌሎች ግን ከበጎ ፈቃድ የተነሣ ክርስቶስን ይሰብካሉ። 16እነዚህ፣ እኔ ለወንጌል ለመሟገት እዚህ እንዳለሁ ስለሚያውቁ፣ በፍቅር ይህን ያደርጋሉ፤ 17እነዚያ ግን በእስራቴ ላይ ሳለሁ መከራ ሊያጸኑብኝ ዐስበው፣ በቅንነት ሳይሆን ለግል ምኞታቸው ሲሉ ክርስቶስን ይሰብካሉ1፥16-17 አንዳንድ ጥንታዊ ያልሆኑ ቅጆች የ16 እና 17 ቅደም ተከተል ለዋውጠውታል።18ታዲያ ችግሩ ከምኑ ላይ ነው? ቁም ነገሩ በቅንነትም ይሁን በማስመሰል በማንኛውም መንገድ ክርስቶስ መሰበኩ ነው። በዚህም ደስ ይለኛል።

አዎን፤ ደስ ይለኛል፤ 19በእኔ ላይ የደረሰው ነገር፣ በጸሎታችሁ አማካይነትና ከኢየሱስ ክርስቶስ መንፈስ በተሰጠ ረድኤት ለመዳኔ1፥19 ወይም ለትድግናዬ እንደሚሆን ዐውቃለሁና። 20በምንም ዐይነት መንገድ ዐፍሬ እንዳልገኝ ጽኑ ናፍቆትና ተስፋ አለ፤ ነገር ግን እንደ ወትሮው ሁሉ ዛሬም በሕይወትም ሆነ በሞት ክርስቶስ በሥጋዬ እንዲከበር ሙሉ ድፍረት ይኖረኛል። 21ለእኔ፣ መኖር ክርስቶስ ነው፤ ሞትም ማትረፍ ነው። 22በሥጋ ከቈየሁ፣ ፍሬያማ ተግባር ይኖረኛል፤ ነገር ግን የትኛውን እንደምመርጥ አላውቅም። 23በእነዚህ በሁለቱ እጨነቃለሁ፤ ልሄድ፣ ከክርስቶስም ጋር ልሆን እናፍቃለሁ፤ ይህ እጅግ የተሻለ ነውና። 24ነገር ግን በሥጋ መኖሬ ለእናንተ ይበልጥ አስፈላጊ ነው። 25ይህን በማስተዋል፣ በእምነት እንድታድጉና ደስ እንዲላችሁ፣ በሁላችሁ ዘንድ እንደምቈይና እንደምኖር ተረድቻለሁ። 26እንደ ገና መጥቼ በእናንተ ዘንድ በምሆንበት ጊዜ፣ በእኔ ምክንያት በክርስቶስ ኢየሱስ ያላችሁ ደስታ ይበዛላችኋል።

27ብቻ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ፤ ይህ ከሆነ መጥቼ ባያችሁ ወይም በርቀት ሆኜ ስለ እናንተ ብሰማ፣ ለወንጌል እምነት እንደ አንድ ሰው ሆናችሁ በመጋደል በአንድ መንፈስ ጸንታችሁ እንደምትቆሙ ዐውቃለሁ። 28በማንኛውም መንገድ በተቃዋሚዎቻችሁ አትሸበሩ፤ ይህ እነርሱ እንደሚጠፉ፣ እናንተ ግን እንደምትድኑ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ምልክት ነው። 29በክርስቶስ እንድታምኑ ብቻ ሳይሆን ስለ እርሱ መከራ እንድትቀበሉም ይህ ጸጋ ተሰጥቷችኋልና፤ 30ቀድሞ እንዳያችሁት አሁንም በእኔ እንዳለ በምትሰሙት በዚያው ዐይነት ተጋድሎ እናንተም እያለፋችሁ ነውና።

Knijga O Kristu

Filipljanima 1:1-30

Pavlovi pozdravi

1Ovo je pismo od Pavla i Timoteja, slugu Krista Isusa, svima svetima u Kristu Isusu koji su u Filipima te starješinama i đakonima.

2Neka vam je milost i mir od našega Boga Oca i Gospodina Isusa Krista.

Pavlova zahvalnost i molitva

3Kad god vas se sjetim, zahvaljujem Bogu. 4U svakoj svojoj molitvi radosno se molim za vas 5jer ste bili sudionicima navješćivanja Radosne vijesti o Kristu od prvoga dana pa sve do sada. 6Siguran sam da će Bog, koji je započeo dobro djelo među vama, to djelo i dovršiti do dana kad se Isus Krist vrati.

7I pravo je da tako osjećam prema vama. Nosim vas u srcu jer ste sa mnom dijelili Božju milost i kad sam bio u okovima, i u obrani i u utvrđivanju Radosne vijesti. 8Bog mi je svjedok da čeznem za svima vama ljubavlju Isusa Krista. 9Moja je molitva za vas da vaša ljubav još više uzraste, da rastete u znanju i razumijevanju, 10da znate odabrati najbolje. Tako ćete biti čisti od svake nečistoće i krivnje na Dan Kristova povratka, 11puni ploda pravednosti koja dolazi po Isusu Kristu.

Pavlova radost zbog propovijedanja Krista

12Želim, draga braćo, da znate da je sve što mi se ovdje dogodilo pomoglo širenju Radosne vijesti 13jer ovdje svi, pa čak i carska tjelesna straža, znaju da sam u okovima zbog Krista. 14A i većina braće osmjelila se zbog mojih okova još neustrašivije propovijedati Božju riječ.

15Neki, doduše, propovijedaju iz zavisti i nadmetanja, ali drugi zato iz dobre volje. 16Propovijedaju jer me vole i jer znaju da me je Gospodin doveo ovamo da branim Radosnu vijest. 17Oni drugi pak Krista navješćuju neiskreno, zaradi vlastite koristi. Misle da će mi time još više otežati okove. 18Ali što onda? Bile njihove pobude iskrene ili ne, Krist se navješćuje. Tomu se radujem. A i dalje ću se radovati 19jer znam da se molite za mene, da mi pomaže Duh Isusa Krista i da ću na koncu biti spašen.

Pavlov život za Krista

20Živim u žarkoj nadi da me ništa neće smesti, nego da ću uvijek, kao i sada, biti hrabar za Krista i da će se on u meni proslaviti, živio ja ili umro za njega. 21Jer za mene je život Krist, a smrt dobitak. 22Ipak, ako živim u tijelu, plodonosno ću djelovati. Što onda odabrati? Ne znam. 23Razdiru me dvije želje. Želim otići i biti s Kristom. To je mnogo bolje za mene. 24Ali zbog vas je potrebnije da ostanem živjeti u tijelu.

25Uvjeren sam u to. Ostat ću s vama da rastete i radujete se u vjeri. 26Tako ćete se, kad opet dođem k vama, imati još više razloga hvaliti onime što je Krist Isus učinio za mene.

Živjeti dostojno evanđelja

27Samo se ponašajte dostojno evanđelja tako da, došao li vas ja vidjeti ili samo slušao o vama, znam da ste postojani u jednome Duhu i da se jednodušno borite za evanđeosku vjeru 28te da se ni u čemu ne strašite protivnika. To će im biti Božji znak njihove propasti, a vašega spasenja. 29Jer dana vam je milost ne samo da vjerujete u Krista, nego i da trpite za njega 30u istoj borbi u kojoj ste me vidjeli i za koju sada čujete da ju vodim.