ዮሐንስ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 5:1-47

በቤተ ሳይዳ የተደረገው ፈውስ

1ከዚህ በኋላ የአይሁድ በዓል ነበረ፤ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ። 2በኢየሩሳሌም፣ በበጎች በር አጠገብ፣ አምስት ባለ መጠለያ መመላለሻዎች የነበሯት፣ በአራማይክ ቋንቋ ቤተ ሳይዳ5፥2 አንዳንድ ቅጆች ቤተ ዛታ ሌሎች ቅጆች ቤተ ሳይዳ ይላሉ። የተባለች አንዲት መጠመቂያ አለች። 3በእነዚህም መመላለሻዎች ውስጥ ብዙ አካለ ስንኩላን፣ ዐይነ ስውሮች፣ ዐንካሶችና ሽባዎች ይተኙ ነበር። [የውሃውንም መንቀሳቀስ እየተጠባበቁ፣ 4ዐልፎ ዐልፎ የጌታ መልአክ ወርዶ ውሃውን በሚያናውጥበት ጊዜ፣ ቀድሞ ወደ መጠመቂያዪቱ የገባ ካደረበት ማንኛውም በሽታ ይፈወስ ነበር።]5፥4 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ከ3 የመጨረሻ ክፍል አንሥቶ እስከ 4 ድረስ ያለውን ክፍል አይጨምሩም። 5በዚያም ለሠላሳ ስምንት ዓመት ሕመምተኛ ሆኖ የኖረ አንድ ሰው ነበር። 6ኢየሱስም ይህን ሰው ተኝቶ ባገኘው ጊዜ፣ ለብዙ ጊዜ በዚህ ሁኔታ እንደ ነበር ዐውቆ “ልትድን ትፈልጋለህን?” አለው።

7ሕመምተኛውም መልሶ፣ “ጌታዬ፣ ውሃው በሚናወጥበት ጊዜ ወደ መጠመቂያዪቱ የሚያወርደኝ ሰው የለኝም፤ ለመግባትም ስሞክር ሌላው ይቀድመኛል” አለው።

8ኢየሱስም፣ “ተነሥ! መተኛህን ተሸክመህ ሂድ” አለው። 9ሰውየውም ወዲያው ተፈወሰ፤ መተኛውንም ተሸክሞ ሄደ።

ይህም የሆነው በሰንበት ቀን ነበር። 10አይሁድም የተፈወሰውን ሰው፣ “ሰንበት ስለሆነ መተኛህን እንድትሸከም ሕጉ አይፈቅድልህም” አሉት።

11እርሱ ግን፣ “ያ የፈወሰኝ ሰው፣ ‘መተኛህን ተሸክመህ ሂድ’ ብሎኛል” ሲል መለሰላቸው።

12እነርሱም፣ “ ‘መተኛህን ተሸክመህ ሂድ’ ያለህ እርሱ ማነው?” ብለው ጠየቁት።

13ኢየሱስ ፈቀቅ ብሎ ወደ ሕዝብ መካከል ገብቶ ስለ ነበር፣ ሰውየው ማን እንደ ፈወሰው አላወቀም።

14ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ያን ሰው በቤተ መቅደስ አግኝቶ፣ “እነሆ፣ ተፈውሰሃል፤ ከእንግዲህ ግን ኀጢአት አትሥራ፤ ያለዚያ ከዚህ የባሰ ይደርስብሃል” አለው። 15ሰውየውም የፈወሰው ኢየሱስ መሆኑን ሄዶ ለአይሁድ ነገራቸው።

ወልድ ሕይወትን ይሰጣል

16አይሁድም፣ በሰንበት ቀን እነዚህን ድርጊቶች በመፈጸሙ፣ ኢየሱስን ያሳድዱት ነበር። 17ኢየሱስም፣ “አባቴ እስካሁን እየሠራ ነው፤ እኔም ደግሞ እሠራለሁ” አላቸው። 18እንግዲህ አይሁድ፣ ኢየሱስ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ ሳይሆን፣ እግዚአብሔርን አባቱ በማድረግ፣ ራሱን ከእግዚአብሔር እኩል በማድረጉ፣ ሊገድሉት አጥብቀው ይፈልጉት ነበር።

19ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ፤ አብ ሲሠራ ያየውን ብቻ እንጂ ወልድ ከራሱ ምንም ሊያደርግ አይችልም፤ አብ የሚያደርገውን ሁሉ ወልድ ደግሞ ያደርጋልና፤ 20አብ ወልድን ስለሚወድድ የሚያደርገውን ሁሉ ያሳየዋል፤ ትደነቁም ዘንድ ከእነዚህም የሚበልጥ ነገር ያሳየዋል። 21ምክንያቱም አብ ሙታንን እንደሚያስነሣ፣ ሕይወትንም እንደሚሰጥ፣ ወልድም ደግሞ ለሚፈቅደው ሁሉ ሕይወትን ይሰጣል። 22አብ በማንም ላይ አይፈርድም፤ ነገር ግን ፍርድን ሁሉ ለወልድ አሳልፎ ሰጥቶታል፤ 23ይኸውም፣ ሁሉ አብን እንደሚያከብሩ ወልድን ያከብሩት ዘንድ ነው፤ ወልድን የማያከብር፣ የላከውን አብንም አያከብርም።

24“እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም። 25እውነት እላችኋለሁ፤ ሙታን የእግዚአብሔርን ልጅ ድምፅ የሚሰሙበት ጊዜ ይመጣል፤ አሁንም መጥቷል፤ የሚሰሙትም በሕይወት ይኖራሉ። 26አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው ሁሉ፣ ወልድም በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና፤ 27ወልድ የሰው ልጅ ስለ ሆነም እንዲፈርድ ሥልጣን ሰጥቶታል።

28“በዚህ አትደነቁ፤ መቃብር ውስጥ ያሉ ሁሉ ድምፁን የሚሰሙበት ጊዜ ይመጣል፤ 29መልካም የሠሩ ለሕይወት ትንሣኤ፣ ክፉ የሠሩ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉ። 30እኔ ብቻዬን ከራሴ ምንም ማድረግ አልችልም፤ የምፈርደው የምሰማውን ብቻ ነው፤ የላከኝን እንጂ የራሴን ፈቃድ ስለማልሻም ፍርዴ ትክክል ነው።

ስለ ኢየሱስ የሚናገሩ ምስክርነቶች

31“እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር፣ ምስክርነቴ ተቀባይነት አይኖረውም። 32ስለ እኔ የሚመሰክር ሌላ አለ፤ እርሱ ስለ እኔ የሚሰጠውም ምስክርነት እውነት እንደ ሆነ ዐውቃለሁ።

33“ወደ ዮሐንስ ልካችሁ ነበር፤ እርሱም ስለ እውነት መስክሯል፤ 34እኔ የሰው ምስክርነት የምቀበል አይደለሁም፤ ይህን የምናገረው ግን እናንተ እንድትድኑ ነው። 35ዮሐንስ እየነደደ ብርሃን የሚሰጥ መብራት ነበረ፤ እናንተም ለጥቂት ጊዜ በብርሃኑ ደስ ልትሰኙ ወደዳችሁ።

36“እኔ ግን ከዮሐንስ ምስክርነት የላቀ ምስክር አለኝ፤ እንድፈጽመው አብ የሰጠኝ፣ እኔም የምሠራው ሥራ አብ እንደ ላከኝ ይመሰክራል። 37የላከኝ አብ ራሱ ስለ እኔ መስክሯል፤ እናንተም ከቶ ድምፁን አልሰማችሁም፤ መልኩንም አላያችሁም፤ 38የላከውንም ስላላመናችሁ ቃሉ በእናንተ አይኖርም። 39በእነርሱ የዘላለም ሕይወትን የምታገኙ እየመሰላችሁ፣ መጻሕፍትን ትመረምራላችሁ፤5፥39 ወይም መጻሕፍትን መርምሩ እነዚሁ መጻሕፍት ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ 40እናንተ ግን፣ ሕይወት እንዲኖራችሁ ወደ እኔ መምጣት አትፈልጉም።

41“እኔ ከሰው ክብር አልቀበልም፤ 42ነገር ግን እናንተን ዐውቃችኋለሁ፤ የእግዚአብሔርም ፍቅር በልባችሁ እንደሌለ ዐውቃለሁ። 43እኔ በአባቴ ስም መጥቼ አልተቀበላችሁኝም፤ ሌላው በራሱ ስም ቢመጣ ግን ትቀበሉታላችሁ። 44እናንተ እርስ በርሳችሁ ክብር የምትሰጣጡ፣ ነገር ግን ከአንዱ አምላክ5፥44 አንዳንድ የጥንት ቅጆች አንድዬ ይላሉ። የሚመጣውን ክብር የማትፈልጉ ከሆነ፣ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ?

45“ከሳሻችሁ ተስፋ የጣላችሁበት ሙሴ እንጂ፣ እኔ በአብ ፊት የምከስሳችሁ አይምሰላችሁ፤ 46ሙሴን ብታምኑ ኖሮ፣ እኔን ባመናችሁ ነበር፤ ምክንያቱም እርሱ የጻፈው ስለ እኔ ነው። 47እርሱ የጻፈውን ካላመናችሁ፣ እኔ የምናገረውን እንዴት ታምናላችሁ?”

Thai New Contemporary Bible

ยอห์น 5:1-47

การรักษาโรคที่สระน้ำ

1ต่อมาพระเยซูเสด็จไปยังกรุงเยรูซาเล็มเพื่อร่วมเทศกาลของชาวยิว 2ในกรุงเยรูซาเล็ม ใกล้ประตูแกะมีสระน้ำแห่งหนึ่ง เรียกตามภาษาอารเมคว่า เบเธสดา5:2 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าเบธซาธาสำเนาต้นฉบับอื่นๆว่าเบธไซดา สระนี้รายล้อมด้วยศาลาห้าหลัง 3ที่นี่มีคนพิการมากมายนอนอยู่ ไม่ว่าคนตาบอด คนง่อย คนเป็นอัมพาต5:3 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาที่สำคัญน้อยกว่าว่าเป็นอัมพาต พวกเขาคอยให้น้ำกระเพื่อม 4ทูตองค์หนึ่งขององค์พระผู้เป็นเจ้าจะลงมากวนน้ำเป็นครั้งคราว ในแต่ละครั้งที่น้ำกระเพื่อมคนแรกซึ่งลงไปในสระจะหายโรคใดๆที่เขาเป็นอยู่ 5ที่นั่นมีชายคนหนึ่งป่วยมา 38 ปีแล้ว 6เมื่อพระเยซูทรงเห็นเขานอนอยู่ และทรงทราบว่าเขาตกอยู่ในสภาพนี้มานาน ก็ตรัสกับเขาว่า “ท่านต้องการจะหายโรคหรือไม่?”

7คนป่วยนั้นทูลว่า “ท่านเจ้าข้า เวลาน้ำกระเพื่อมไม่มีใครช่วยข้าพเจ้าลงสระ ขณะที่ข้าพเจ้าพยายามจะลงไป คนอื่นก็ลงไปก่อนแล้ว”

8พระเยซูจึงตรัสกับเขาว่า “จงลุกขึ้น! ยกที่นอนเดินไปเถิด” 9ชายผู้นี้ก็หายโรคทันที เขายกที่นอนเดินไป

วันที่เกิดเหตุการณ์นี้เป็นวันสะบาโต 10พวกยิวจึงพูดกับคนที่หายโรคนั้นว่า “นี่เป็นวันสะบาโต บทบัญญัติห้ามเจ้าแบกที่นอน”

11แต่เขาตอบว่า “ชายผู้ที่รักษาข้าพเจ้าให้หายบอกข้าพเจ้าว่า ‘จงยกที่นอนเดินไปเถิด’ ”

12พวกเขาจึงถามว่า “คนที่บอกให้เจ้ายกที่นอนเดินไปนั้นคือใคร?”

13คนที่หายโรคไม่ทราบว่าพระองค์คือใคร เพราะพระเยซูได้เสด็จปะปนหายไปในฝูงชนที่นั่น

14ต่อมาพระเยซูทรงพบเขาที่พระวิหารและตรัสว่า “ดูเถิด ท่านสบายดีแล้ว จงเลิกทำบาป มิฉะนั้นสิ่งเลวร้ายกว่าเดิมอาจจะเกิดกับท่าน” 15เขาก็ไปและบอกพวกยิวว่า พระเยซูคือผู้ที่รักษาเขาให้หายโรค

ชีวิตที่ผ่านมาทางพระบุตร

16ฉะนั้นพวกยิวจึงข่มเหงพระเยซูเพราะพระองค์ทรงกระทำสิ่งเหล่านั้นในวันสะบาโต 17พระเยซูตรัสกับพวกเขาว่า “พระบิดาของเราทรงกระทำพระราชกิจของพระองค์เสมอตราบจนทุกวันนี้ และเราก็กำลังทำงานเช่นกัน” 18ด้วยเหตุนี้พวกยิวจึงยิ่งพยายามทุกวิถีทางที่จะฆ่าพระเยซู เพราะพระองค์ไม่เพียงแต่ทรงละเมิดบทบัญญัติวันสะบาโต แต่ยังทรงเรียกพระเจ้าว่าพระบิดาของตนอันเป็นการยกตนเองเสมอพระเจ้า

19พระเยซูตรัสตอบพวกเขาว่า “เราบอกความจริงแก่ท่านว่า พระบุตรไม่อาจทำสิ่งใดโดยลำพังพระองค์เอง พระองค์สามารถทำได้แต่เพียงสิ่งที่เห็นพระบิดาของพระองค์ทรงกระทำ เพราะพระบิดาทรงกระทำสิ่งใด พระบุตรก็กระทำสิ่งนั้นด้วย 20เพราะพระบิดาทรงรักพระบุตร และสำแดงทุกสิ่งที่ทรงกระทำให้พระบุตรเห็น ท่านจะประหลาดใจที่พระองค์จะสำแดงให้พระบุตรเห็นสิ่งที่ยิ่งใหญ่ กว่านี้อีก 21เพราะพระบิดาทรงให้คนที่ตายแล้วกลับมีชีวิตขึ้นมาใหม่อย่างไร พระบุตรก็จะให้ชีวิตแก่ผู้ที่พระบุตรพอพระทัยอย่างนั้น 22ยิ่งกว่านั้นพระบิดาไม่ได้ทรงพิพากษาใครแต่ทรงมอบการพิพากษาทั้งหมดแก่พระบุตร 23เพื่อคนทั้งปวงจะได้ถวายเกียรติแด่พระบุตรเหมือนที่ได้ถวายเกียรติแด่พระบิดา ผู้ที่ไม่ถวายเกียรติแด่พระบุตรก็ไม่ได้ถวายเกียรติแด่พระบิดาผู้ทรงส่งพระบุตรมา

24“เราบอกความจริงแก่ท่านว่า ผู้ใดฟังคำของเราและเชื่อพระองค์ผู้ทรงส่งเรามา ผู้นั้นก็มีชีวิตนิรันดร์และจะไม่ถูกลงโทษ เขาได้ผ่านพ้นความตายเข้าสู่ชีวิตแล้ว 25เราบอกความจริงแก่ท่านว่า ใกล้ถึงเวลาแล้ว และบัดนี้ถึงเวลาแล้วที่คนตายจะได้ยินเสียงพระบุตรของพระเจ้าและบรรดาผู้ที่ได้ยินจะมีชีวิต 26เพราะพระบิดาทรงมีชีวิตในพระองค์เองฉันใด พระองค์ก็ทรงให้พระบุตรมีชีวิตในพระองค์เองฉันนั้น 27และพระองค์ทรงให้พระบุตรมีสิทธิอำนาจที่จะพิพากษาเพราะว่าพระองค์คือบุตรมนุษย์

28“อย่าประหลาดใจในข้อนี้ เพราะจะถึงเวลาที่คนทั้งปวงซึ่งอยู่ในหลุมฝังศพของตนจะได้ยินเสียงของพระบุตร 29และจะออกมา ผู้ที่ทำดีจะฟื้นขึ้นสู่ชีวิต ผู้ที่ทำชั่วจะฟื้นขึ้นรับการลงโทษ 30เราทำสิ่งใดโดยลำพังตัวเราเองไม่ได้เลย เราพิพากษาตามที่เราได้ยินเท่านั้น และคำพิพากษาของเรายุติธรรม เพราะเราไม่ได้มุ่งทำให้ตนเองพอใจแต่มุ่งให้พระองค์ผู้ทรงส่งเรามาพอพระทัย

พยานรับรองพระเยซู

31“ถ้าเราเป็นพยานให้ตนเอง คำพยานของเราก็ไม่น่าเชื่อถือ 32มีอีกผู้หนึ่งที่เป็นพยานให้เรา และเรารู้ว่าคำพยานของผู้นั้นเกี่ยวกับเราก็เชื่อถือได้

33“ท่านส่งคนไปหายอห์น และยอห์นได้เป็นพยานถึงความจริง 34ไม่ใช่ว่าเรายอมรับคำพยานของมนุษย์ แต่เราเอ่ยถึงเรื่องนี้เพื่อท่านจะรอด 35ยอห์นเป็นตะเกียงที่ลุกอยู่และให้แสงสว่าง และพวกท่านเลือกที่จะชื่นชมความสว่างของยอห์นชั่วขณะหนึ่ง

36“เรามีคำพยานที่หนักแน่นยิ่งกว่าคำพยานของยอห์น เพราะงานที่พระบิดาทรงมอบหมายให้เราทำให้สำเร็จและเรากำลังทำอยู่นั้นเองเป็นพยานว่าพระบิดาทรงส่งเรามา 37ทั้งพระบิดาผู้ทรงส่งเรามาพระองค์เองได้ทรงเป็นพยานให้เรา ท่านไม่เคยได้ยินพระสุรเสียงหรือเห็นรูปพรรณสัณฐานของพระองค์ 38ทั้งพระดำรัสของพระองค์ก็ไม่ได้อยู่ในท่านเพราะท่านไม่เชื่อผู้ที่พระองค์ทรงส่งมา 39ท่านขยันศึกษา5:39 หรือจงขยันศึกษาพระคัมภีร์เพราะท่านคิดว่าโดยพระคัมภีร์ท่านจะได้ชีวิตนิรันดร์ พระธรรมเหล่านั้นคือพระคัมภีร์ที่เป็นพยานเกี่ยวกับเรา 40กระนั้นพวกท่านก็ไม่ยอมมาหาเราเพื่อจะได้ชีวิต

41“เราไม่ยอมรับการสรรเสริญจากมนุษย์ 42แต่เรารู้จักพวกท่าน เรารู้ว่าท่านไม่ได้มีความรักของพระเจ้าอยู่ในใจ 43เราได้มาในพระนามของพระบิดาของเราและท่านไม่ยอมรับเรา แต่ถ้าผู้อื่นมาในนามของเขาเอง ท่านจะยอมรับผู้นั้น 44ท่านจะเชื่อได้อย่างไร ถ้าหากท่านยอมรับคำสรรเสริญกันเอง แต่ไม่ขวนขวายหาคำสรรเสริญจากพระเจ้าผู้ทรงเป็นพระเจ้าแต่องค์เดียว5:44 สำเนาต้นฉบับเก่าแก่บางสำเนาว่าพระองค์ผู้เป็นหนึ่งเดียว?

45“แต่อย่าคิดว่าเราจะฟ้องท่านต่อพระบิดา ผู้ที่ฟ้องท่านคือโมเสสซึ่งท่านได้ตั้งความหวังไว้กับเขา 46หากท่านเชื่อโมเสส ท่านควรจะเชื่อเราเพราะโมเสสได้เขียนเกี่ยวกับเรา 47แต่เพราะท่านไม่เชื่อสิ่งที่โมเสสเขียนไว้ ท่านจะเชื่อสิ่งที่เราพูดได้อย่างไร?”