ያዕቆብ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ያዕቆብ 5:1-20

ለጨካኝ ሀብታሞች የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

1እንግዲህ እናንተ ሀብታሞች ስሙ፤ ስለሚደርስባችሁ መከራ አልቅሱ፤ ዋይ ዋይም በሉ። 2ሀብታችሁ ሻግቷል፤ ልብሳችሁንም ብል በልቶታል። 3ወርቃችሁና ብራችሁ ዝጓል፤ ዝገቱም በእናንተ ላይ ይመሰክራል፤ ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላዋል፤ ለመጨረሻው ዘመን ሀብትን አከማችታችኋል። 4ልብ በሉ፤ ዕርሻችሁን ሲያጭዱ ለዋሉ ሠራተኞች ያልከፈላችሁት ደመወዝ በእናንተ ላይ ይጮኻል፤ የዐጫጆቹም ጩኸት ሁሉን ቻይ ወደ ሆነው ጌታ ጆሮ ደርሷል። 5በምድርም ላይ በምቾትና በመቀማጠል ኖራችኋል፤ ለዕርድ5፥5 ወይም ለድግስ ቀን ልባችሁን አወፍራችኋል። 6እናንተን ያልተቃወሙትን ንጹሓን ሰዎች ኰንናችኋል፤ ገድላችኋልም።

በመከራ ውስጥ መታገሥ

7እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ ጌታ እስከሚመጣ ድረስ ታገሡ። ገበሬ መሬቱ መልካምን ፍሬ እስከሚሰጥ ድረስ እንዴት እንደሚታገሥ፣ የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ እንዴት እንደሚጠባበቅ አስተውሉ። 8እናንተም እንዲሁ ታገሡ፤ ልባችሁንም አጽኑ፤ ምክንያቱም የጌታ መምጫ ተቃርቧል። 9ወንድሞች ሆይ፤ እርስ በርሳችሁ አታጕረምርሙ፤ አለዚያ ይፈረድባችኋል፤ እነሆ፤ ፈራጁ በበር ላይ ቆሟል።

10ወንድሞች ሆይ፤ በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያት የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ አድርጋችሁ ተመልከቱ። 11በትዕግሥት የጸኑትን የተባረኩ አድርገን እንደምንቈጥር ታውቃላችሁ፤ ኢዮብ እንዴት ታግሦ እንደ ጸና ሰምታችኋል፤ ጌታም በመጨረሻ ያደረገለትን አይታችኋል። ጌታ እጅግ ርኅሩኅና መሓሪ ነው።

12ከሁሉም በላይ ወንድሞቼ ሆይ፤ በሰማይ ወይም በምድር ወይም በማናቸውም ነገር ቢሆን አትማሉ፤ “አዎ” ቢሆን አዎ ይሁን፤ “አይደለም” ቢሆን አይደለም ይሁን፤ አለዚያ ይፈረድባችኋል።

ከእምነት የሆነ ጸሎት

13ከእናንተ መካከል በመከራ ውስጥ ያለ አለ? እርሱ ይጸልይ፤ የተደሰተ አለ? የምስጋና መዝሙር ይዘምር። 14ከእናንተ መካከል የታመመ ሰው አለ? የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ይጥራ፤ እነርሱም በጌታ ስም ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። 15በእምነት የቀረበ ጸሎት የታመመውን ሰው ይፈውሰዋል፤ ጌታም ያስነሣዋል፤ ኀጢአትም ሠርቶ ከሆነ፣ ይቅር ይባላል። 16ስለዚህ ኀጢአታችሁን እርስ በርሳችሁ ተናዘዙ፤ ትፈወሱም ዘንድ አንዱ ለሌላው ይጸልይ። የጻድቅ ሰው ጸሎት ኀይል አለው፤ ታላቅ ነገርም ያደርጋል።

17ኤልያስ እንደ እኛ ሰው ነበረ፤ ዝናብ እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፤ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ተኩል ዝናብ አልዘነበም። 18እንደ ገናም ጸለየ፤ ዝናብም ከሰማይ ዘነበ፤ ምድርም ፍሬዋን ሰጠች።

19ወንድሞቼ ሆይ፤ ከእናንተ አንዱ ከእውነት ቢስትና ሌላው ቢመልሰው፣ 20ይህን አስተውሉ፤ ኀጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልስ ሰው ነፍሱን ከሞት ያድነዋል፤ ብዙ ኀጢአትንም ይሸፍናል።

Thai New Contemporary Bible

ยากอบ 5:1-20

ตักเตือนคนมั่งมีผู้รังแกคนจน

1ท่านทั้งหลายที่ร่ำรวยจงฟังเถิด จงร่ำไห้คร่ำครวญเนื่องด้วยทุกข์เข็ญที่จะเกิดกับท่าน 2ทรัพย์สมบัติของท่านก็ผุพังไปแล้วและแมลงได้กัดกินเสื้อผ้าของท่าน 3เงินและทองของท่านขึ้นสนิม สนิมนั้นเป็นพยานปรักปรำและกัดกินเลือด เนื้อท่านดั่งไฟ ท่านกักตุนทรัพย์สมบัติไว้ในวาระสุดท้าย 4ดูเถิด! ค่าจ้างที่ท่านโกงคนงานเกี่ยวข้าวในนาของท่านนั้นกำลังร้องกล่าวโทษท่านอยู่ เสียงร้องทุกข์ของผู้เก็บเกี่ยวได้ขึ้นถึงพระกรรณขององค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงฤทธิ์แล้ว 5ท่านได้ใช้ชีวิตในโลกอย่างหรูหราและปรนเปรอตนเองตามใจชอบ ท่านขุนตนเองไว้รอวันประหาร5:5 หรือราวกับอยู่ในวันเลี้ยงฉลอง 6ท่านตัดสินลงโทษและเข่นฆ่าคนที่ไม่มีความผิดผู้ไม่ได้ต่อต้านท่าน

อดทนในความทุกข์ยาก

7เหตุฉะนั้นพี่น้องทั้งหลาย จงอดทนตราบจนองค์พระผู้เป็นเจ้าเสด็จมา จงดูชาวนารอคอยพืชผลล้ำค่าจากแผ่นดิน ดูเถิดว่าเขาอดทนรอคอยฝนต้นฤดูและฝนปลายฤดูขนาดไหน 8ท่านทั้งหลายก็เช่นกันจงอดทนและยืนหยัดอย่างมั่นคง เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าใกล้จะเสด็จมาแล้ว 9พี่น้องทั้งหลายอย่าบ่นว่ากันเพื่อจะไม่ถูกตัดสินโทษ องค์ผู้พิพากษาทรงยืนอยู่ที่ประตูแล้ว!

10พี่น้องทั้งหลายจงยึดถือเหล่าผู้เผยพระวจนะในพระนามขององค์พระผู้เป็นเจ้าเป็นแบบอย่างในการอดทนเมื่อเผชิญความทุกข์ยาก 11ดังที่ท่านทราบกันอยู่ เราถือว่าผู้ที่อดทนบากบั่นก็เป็นสุข ท่านก็ได้ยินถึงความอดทนบากบั่นของโยบและได้เห็นว่าในที่สุดองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงให้เกิดอะไรขึ้น องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเปี่ยมด้วยพระเมตตากรุณา

12พี่น้องทั้งหลาย เหนือสิ่งอื่นใดอย่าสาบาน ไม่ว่าอ้างสวรรค์ อ้างพิภพโลก หรืออ้างสิ่งอื่นใด ใช่ก็ว่า “ใช่” ไม่ก็ว่า “ไม่” มิฉะนั้นท่านจะถูกตัดสินลงโทษ

คำอธิษฐานด้วยความเชื่อ

13ถ้าผู้ใดในพวกท่านเดือดร้อนผู้นั้นควรจะอธิษฐาน ถ้าผู้ใดมีความสุขให้ผู้นั้นร้องเพลงสรรเสริญพระเจ้า 14ถ้าผู้ใดในพวกท่านเจ็บป่วยผู้นั้นควรเชิญบรรดาผู้ปกครองคริสตจักรมาอธิษฐานเผื่อและเจิมด้วยน้ำมันในพระนามขององค์พระผู้เป็นเจ้า 15คำอธิษฐานด้วยความเชื่อจะทำให้ผู้ป่วยหายดี องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงรักษาเขา ถ้าเขาทำบาปพระองค์ก็จะทรงอภัยให้เขา 16ฉะนั้นจงสารภาพบาปของท่านต่อกันและอธิษฐานเผื่อกันและกัน เพื่อท่านจะได้รับการรักษาให้หาย คำอธิษฐานของผู้ชอบธรรมทรงอานุภาพและเกิดผล

17เอลียาห์ก็เป็นมนุษย์เหมือนเราทั้งหลาย เขาทุ่มเทอธิษฐานขออย่าให้ฝนตก ฝนก็ไม่ตกรดแผ่นดินตลอดสามปีครึ่ง 18เขาอธิษฐานอีก แล้วฟ้าก็ให้ฝนและแผ่นดินให้พืชผล

19พี่น้องทั้งหลายหากใครในพวกท่านหลงไปจากความจริงและมีบางคนนำเขากลับมา 20จงจำไว้ว่าผู้ที่พาคนบาปหันจากทางผิดของเขา จะช่วยเขาพ้นจากความตาย และความผิดบาปมากมายจะได้รับการลบล้างโดยการให้อภัย