ዘፍጥረት 32 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 32:1-32

ያዕቆብ፣ ወንድሙን ዔሳውን ሊገናኝ ተዘጋጀ

1ያዕቆብም ጕዞውን ቀጠለ፤ የእግዚአብሔርም (ኤሎሂም) መላእክት ተገናኙት፤ 2ባያቸውም ጊዜ፣ “ይህ የእግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሰፈር ነው” አለ፤ የዚያንም ቦታ ስም መሃናይም32፥2 መሃናይም ማለት ሁለት ጐራ ማለት ነው። አለው።

3ያዕቆብም በኤዶም አገር ሴይር በተባለው ምድር ወደሚኖረው ወንድሙ ወደ ዔሳው መልእክተኞችን አስቀድሞ ላከ፤ 4እንዲህም ብሎ አዘዛቸው፤ “ጌታዬን ዔሳውን እንዲህ ትሉታላችሁ፤ ‘አገልጋይህ ያዕቆብ እንዲህ ብሏል በሉት፤ “ከላባ ዘንድ ተቀምጬ እስከ አሁን ድረስ እዚያው ኖርሁ፤ 5ከብቶች፣ አህዮች፣ የበግና የፍየል መንጎች እንደዚሁም የወንድና የሴት አገልጋዮች አሉኝ፤ አሁንም ይህን መልእክት ለጌታዬ መላኬ በጎ ፈቃድህን እንዳገኝ በማሰብ ነው።” ’ ”

6የተላኩትም ሰዎች ወደ ያዕቆብ ተመልሰው፣ “ወደ ወንድምህ ወደ ዔሳው ሄደን ነበር፤ እርሱም ሊቀበልህ በመምጣት ላይ ነው፤ አራት መቶ ሰዎችም አብረውት አሉ” አሉት። 7ያዕቆብም በታላቅ ፍርሀትና ጭንቀት ተውጦ፣ አብረውት የነበሩትን ሰዎች ሁለት ቦታ32፥7 ወይም ጐራ፤ በ10 ላይ ያለውም እንዲሁ፤ ከፈላቸው፤ በጎቹን፣ ፍየሎቹን፣ ከብቶቹንና ግመሎቹን ሁለት ቦታ ከፈላቸው። 8“ዔሳው መጥቶ በአንደኛው ላይ አደጋ ቢጥል፣ ሌላው ክፍል32፥8 ወይም ጐራ ሊያመልጥ ይችላል” ብሎ አስቦ ነበር።

9ያዕቆብ እንዲህ ሲል ጸለየ፤ “የአባቴ የአብርሃም አምላክ፣ የአባቴ የይስሐቅ አምላክ (ኤሎሂም) ሆይ፤ ‘ወደ አገርህና ወደ ዘመዶችህ ተመለስ፤ እኔም በጎ ነገር አደርግልሃለሁ’ ያልኸኝ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤ 10እኔ ባሪያህ እስካሁን ላደረግህልኝ ቸርነትና ታማኝነት ብቁ አይደለሁም፤ ዮርዳኖስን ስሻገር በእጄ ላይ ከነበረው በትር በስተቀር ምንም አልነበረኝም፤ አሁን ግን ይኸው ሁለት ሰራዊት ሆኛለሁ። 11ከወንድሜ ከዔሳው እጅ እንድታድነኝ እለምንሃለሁ፤ መጥቶ እኔንም ሆነ እነዚህን እናቶች ከነልጆቻቸው ያጠፋናል ብዬ ፈርቻለሁና፤ 12ነገር ግን፣ አንተ ራስህ፣ ‘አበለጽግሃለሁ፤ ዘርህንም ሊቈጠር እንደማይቻል እንደ ባሕር አሸዋ አበዛዋለሁ’ ብለኸኛል።”

13በዚያችም ሌሊት ያዕቆብ እዚያው ዐደረ፤ ካለው ሀብት ለወንድሙ ለዔሳው እጅ መንሻ እነዚህን መረጠ፦ 14ሁለት መቶ እንስት ፍየሎችና ሃያ አውራ ፍየሎች፣ ሁለት መቶ እንስት በጎችና ሃያ አውራ በጎች፣ 15ሠላሳ የሚያጠቡ ግመሎች ከነግልገሎቻቸው፣ አርባ ላሞችና ዐሥር ኮርማዎች፣ ሃያ እንስት አህዮችና ዐሥር ተባት አህዮች። 16እነዚህንም በየመንጋው ለይቶ፣ የሚነዷቸውን ጠባቂዎች መደበላቸው፤ ጠባቂዎቹንም፣ “እናንተ ቀድማችሁኝ ሂዱ፣ መንጋዎቹንም አራርቃችሁ ንዷቸው” አላቸው።

17ቀድሞ የሚሄደውንም እንዲህ ሲል አዘዘው፤ “ዔሳው አግኝቶህ፣ ‘የማን ነህ? ወዴትስ ትሄዳለህ? የምትነዳውስ ይህ ሁሉ ከብት የማን ነው?’ ብሎ ቢጠይቅህ፣ 18‘የአገልጋይህ የያዕቆብ ናቸው፤ ለጌታዬ ለዔሳው እጅ መንሻ የሰደዳቸው ናቸው፤ እርሱም ከበስተ ኋላችን እየመጣ ነው’ ብለህ ንገረው።”

19እንዲሁም ሁለተኛውን፣ ሦስተኛውንና መንጎችን የሚነዱትን ሌሎቹንም ሁሉ እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ “ዔሳውን ስታገኙት ይህንኑ ትነግሩታላችሁ፤ 20በተለይም ‘አገልጋይህ ያዕቆብ ከኋላችን እየመጣ ነው’ ማለትን አትዘንጉ።” ይህንም ያዘዘው፣ “ዔሳው ከእኔ ጋር ከመገናኘቱ በፊት እጅ መንሻዬ አስቀድሞ ቢደርሰው ምናልባት ልቡ ይራራና በሰላም ይቀበለኛል” ብሎ ስላሰበ ነበር። 21ስለዚህ የያዕቆብ እጅ መንሻ ከእርሱ አስቀድሞ ተላከ፤ እርሱ ራሱ ግን እዚያው በሰፈሩበት ቦታ ዐደረ።

ያዕቆብ ከእግዚአብሔር ጋር የገጠመው ትግል

22በዚያች ሌሊት ያዕቆብ ተነሣ፤ ሁለቱን ሚስቶቹን እንዲሁም ሁለቱን ሴት አገልጋዮቹንና ዐሥራ አንድ ልጆቹን ይዞ በያቦቅ መልካ ተሻገረ። 23ወንዙን አሻግሮ ከሸኛቸው በኋላ፣ ጓዙን ሁሉ ሰደደ። 24ያዕቆብ ግን ብቻውን እዚያው ቀረ፤ አንድ ሰውም እስኪነጋ ድረስ ሲታገለው ዐደረ። 25ያም ሰው ያዕቆብን ታግሎ ማሸነፍ እንዳቃተው በተረዳ ጊዜ፣ የጭኑን ሹልዳ ነካው፤ በግብግቡም የያዕቆብ ጭን ከመጋጠሚያው ላይ ተናጋ። 26በዚያን ጊዜ ሰውየው፣ “እንግዲህ መንጋቱ ስለሆነ ልቀቀኝና ልሂድ” አለው።

ያዕቆብም፣ “ካልባረክኸኝ አልለቅህም” አለው።

27ሰውየውም፣ “ስምህ ማን ነው?” አለው።

እርሱም፣ “ያዕቆብ ነው” አለ።

28ሰውየውም፣ “ከእግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ ከሰዎችም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና ከእንግዲህ ስምህ እስራኤል32፥28 እስራኤል ማለት ከእግዚአብሔር ታገለ ማለት ነው። እንጂ፣ ያዕቆብ አይባልም” አለው።

29ያዕቆብም፣ “እባክህ ስምህን ንገረኝ” ብሎ ጠየቀው።

ሰውየውም፣ “ስሜን ለማወቅ ለምን ፈለግህ?” አለው፤ በዚያም ስፍራ ባረከው።

30ስለዚህ ያዕቆብ፣ “እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ፊት ለፊት አይቼ እንኳ ሕይወቴ ተርፋለች” ሲል፣ የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል32፥30 ጵኒኤል ማለት የእግዚአብሔር ፊት ማለት ነው። አለው።

31ጵኒኤልንም32፥31 በዕብራይስጥ ጵኑኤል ማለት ሲሆን፣ የጵኒኤል አማራጭ ትርጕም ነው። እንዳለፈ ፀሓይ ወጣችበት፤ እርሱም በጭኑ ምክንያት ያነክስ ነበር። 32ከዚህም የተነሣ የእስራኤል ልጆች እስከ ዛሬ ድረስ ሹልዳን ከጭኑ ጋር የሚያገናኘውን ሥጋ አይበሉም፤ ምክንያቱም በጭኑ መጋጠሚያ ላይ ያለው የያዕቆብ ሹልዳ ተነክቶ ነበር።

Swedish Contemporary Bible

1 Moseboken 32:1-32

Jakob ger Esau gåvor

1Jakob startade på nytt sin resa och Guds änglar kom för att möta honom. 2När han såg det sa han: ”Detta är Guds läger”, och han kallade platsen för Machanajim32:2 Machanajim betyder två läger eller två skaror. Två fiendeläger hade just skilts som vänner. Nu skulle Jakob också möta sin bror Esaus läger..

3Jakob skickade nu budbärare till sin bror Esau i Seir, dvs. i landet Edom. 4”Säg så här till min herre, Esau”, sa Jakob. ”Så här hälsar din tjänare Jakob. Jag har bott tillsammans med Laban tills nu, och 5jag äger oxar, åsnor och får och har många tjänare och tjänarinnor. Jag har skickat detta budskap till dig, min herre, för att jag hoppas att du kommer att vara välvilligt inställd mot oss.”

6Budbärarna återvände med nyheten att Esau redan var på väg för att möta Jakob tillsammans med fyrahundra man. 7Jakob blev alldeles utom sig av skräck. Han delade sin familj och hjordarna och kamelerna i två grupper. 8”Om Esau anfaller den ena gruppen, kan den andra gruppen kanske fly”, tänkte han.

9Sedan bad Jakob: ”Min farfar Abrahams och min far Isaks Gud, du Herre, som sa till mig att återvända till mina släktingars land och som sa att du skulle vara god mot mig, 10jag är ovärdig all den nåd och trofasthet som du har visat mig, din tjänare. När jag gick över Jordan ägde jag ju inget annat än min vandringsstav, och nu har jag dessa två läger. 11Rädda mig nu från min bror Esaus hand! Jag är rädd att han kommer för att slå ihjäl mig och mödrarna och barnen. 12Du har ju lovat att göra gott mot mig och föröka mina ättlingar tills de blir som sanden på stranden, så många att man inte kan räkna dem.”

13Jakob stannade där han var under natten och valde av sin egendom ut en gåva åt sin bror Esau: 14200 getter, 20 bockar, 200 tackor, 20 baggar, 1530 kameler med deras föl, 40 kor, 10 tjurar, 20 åsneston och 10 åsnehingstar.

16Han lämnade dem till sina tjänare, var hjord för sig, och sa till dem att gå före honom och hålla avstånd mellan varje hjord. 17Sedan instruerade han tjänaren som gick först: ”När min bror Esau möter dig och frågar: ’Vems tjänare är du? Vart är du på väg? Vems djur är dessa?’ 18så ska du svara: ’De tillhör din tjänare Jakob och är en gåva till hans herre Esau. Han kommer själv strax efter oss!’ ”

19Jakob gav samma instruktion till den andra och tredje tjänaren, och sedan till alla de andra som drev hjordarna. Alla skulle säga samma sak till Esau när de mötte honom. 20De skulle också säga: ”Din tjänare Jakob kommer strax efter oss”. Han ville nämligen blidka Esau med gåvorna, innan han mötte honom ansikte mot ansikte. ”Kanske kommer han då att vara vänlig mot mig”, tänkte Jakob. 21Gåvan sändes alltså i förväg medan Jakob tillbringade natten i lägret.

Jakobs brottningskamp

22Under natten steg Jakob upp, och tog sina båda hustrur, de två slavinnorna och sina elva söner och gick över vid Jabboks vadställe. 23Han förde dem tillsammans med alla sina ägodelar över floden. 24Han blev kvar där ensam, och en man brottades med honom till gryningen. 25När denne såg att han inte kunde vinna kampen, slog han till Jakob på höften så att den gick ur led när de brottades med varandra.

26Sedan sa han: ”Släpp mig, för dagen gryr!” Men Jakob svarade: ”Jag tänker inte släppa dig förrän du välsignar mig.” 27”Vad heter du?” frågade mannen32:27 Översättningen mannen följer v. 24; enligt grundtexten är det bara han i v. 27-29. Fortsättningen visar att det sedan gick upp för Jakob att han brottats med Gud själv.. ”Jakob”, svarade han. 28”Du ska inte längre heta Jakob”, sa mannen. ”Du ska heta Israel32:28 Israel betyder han kämpar med Gud., för du har kämpat med både Gud och människor och segrat.” 29”Säg mig, vad heter du?” frågade Jakob. ”Varför frågar du om mitt namn?” sa mannen till honom. Och han välsignade honom där.

30Jakob kallade platsen Penuel32:30 Penuel betyder Guds ansikte., för han sa: ”Jag har sett Gud ansikte mot ansikte, och ändå är jag fortfarande vid liv.” 31När solen gick upp lämnade han Penuel. Han haltade på grund av sin höftskada. 32Det är därför som Israels folk än i dag inte äter nervsträngen32:32 Grundtexten är svårförståelig. i höftmuskeln, för det var på höftbenet, höftnerven, som mannen slog Jakob.