ዘፍጥረት 20 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 20:1-18

አብርሃምና አቤሜሌክ

20፥1-18 ተጓ ምብ – ዘፍ 12፥10-2026፥1-11

1አብርሃም ከዚያ ተነሥቶ ወደ ኔጌብ አካባቢ ሄዶ በቃዴስና በሱር መካከል ሰፈረ፤ ለጥቂት ጊዜም በጌራራ ተቀመጠ። 2በዚያም አብርሃም ሚስቱን ሣራን፣ “እኅቴ ናት” ይል ነበር። ስለዚህ የጌራራ ንጉሥ አቢሜሌክ መልእክተኛ ልኮ ሣራን ወሰዳት።

3እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) በአንድ ሌሊት በሕልም ወደ አቢሜሌክ መጥቶ፣ “እነሆ፤ በወሰድሃት ሴት ምክንያት ምዉት ነህ፤ እርሷ ባለ ባል ናት” አለው።

4አቢሜሌክም ገና አልደረሰባትም ነበርና እንዲህ አለ፤ “ጌታ ሆይ፤ በደል ያልፈጸመውን ሕዝብ ታጠፋለህን? 5‘እኅቴ ናት’ ያለኝ ራሱ አይደለምን? ደግሞስ ራሷም ብትሆን፣ ‘ወንድሜ ነው’ አላለችምን? እኔ ይህን ያደረግሁት በቅን ልቦናና በንጹሕ እጅ ነው።”

6እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) በሕልሙ እንዲህ አለው፤ “አንተ ይህን ያደረግኸው በቅን ልቦና መሆኑን ዐውቄአለሁ፤ በእኔም ላይ ኀጢአት እንዳትሠራ የጠበቅሁህና እንዳትነካትም ያደረግሁት ለዚሁ ነው። 7አሁንም ሚስቱን ለሰውየው መልስለት፤ ነቢይ ነውና ይጸልይልሃል፤ አንተም ትድናለህ፤ ባትመልስለት ግን አንተም ሆንህ የአንተ የሆነ ሁሉ እንደምትሞቱ ዕወቅ።”

8በማግስቱም ማለዳ፣ አቢሜሌክ ሹማምቱን ሁሉ ጠርቶ፣ የሆነውን ሁሉ ነገራቸው፤ እነርሱም ታላቅ ፍርሀት ዐደረባቸው። 9ከዚያም አቢሜሌክ አብርሃምን አስጠርቶ እንዲህ አለው፤ “ይህ ያደረግህብን ነገር ምንድን ነው? ምን በደልሁህና ነው በእኔና በግዛቴ ላይ እንዲህ ያለውን ታላቅ የጥፋት መዘዝ ያመጣህብን? በእውነቱ መደረግ የማይገባውን ነው ያደረግህብን።” 10ከዚያም አቢሜሌክ፣ “ለመሆኑ ይህን ያደረግህበት ምክንያት ምንድን ነው?” ሲል አብርሃምን ጠየቀው።

11አብርሃምም አቢሜሌክን እንዲህ አለው፤ “እዚህ ቦታ ፈሪሀ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) አለመኖሩን ተገነዘብሁ፤ ሰዎቹም ለሚስቴ ሲሉ ይገድሉኛል ብዬ ሠጋሁ፤ 12ደግሞም እኮ በርግጥ እኅቴ ናት፤ ከአንድ እናት ባንወለድም በአባት አንድ ነን፤ ኋላም አገባኋት። 13እግዚአብሔር (ኤሎሂም) አዝዞኝ ከአባቴ ቤት ወጥቼ በየአገሩ ስዞር፣ ‘ለእኔ ያለሽን ፍቅር በዚህ ግለጭልኝ፤ በየደረስንበት ስፍራ ሁሉ “እርሱ ወንድሜ ነው” በዪ’ ብያት ነበር።”

14ከዚያም አቢሜሌክ፣ በጎችና የቀንድ ከብቶች፣ ወንድና ሴት አገልጋዮችን ለአብርሃም ሰጠው፤ ሚስቱን ሣራንም መለሰለት። 15አቢሜሌክም አብርሃምን፣ “እነሆ፤ አገሬ አገርህ ናት፤ በፈቀድህበት ስፍራ መኖር ትችላለህ” አለው።

16ሣራንም፣ “እነሆ፤ ለወንድምሽ ለአብርሃም አንድ ሺሕ ጥሬ ብር20፥16 11.5 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል። እሰጠዋለሁ፤ ይህም በአንቺ ላይ ለተፈጸመው በደል ካሣ እንዲሆንና አብረውሽ ያሉ ሁሉ እንዲያውቁት ነው፤ በዚህም ንጽሕናሽ ይረጋገጣል” አላት።

17ከዚያም አብርሃም ወደ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ጸለየ፤ እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) አቢሜሌክን፣ ሚስቱንና ሴት አገልጋዮቹን ፈወሳቸው፤ እንደ ገናም ልጅ ለመውለድ በቁ። 18እግዚአብሔር (ያህዌ) በአብርሃም ሚስት በሣራ ምክንያት፣ በአቢሜሌክ ቤት የሚገኙትን ሴቶች ማሕፀናቸውን ሁሉ ዘግቶ ነበርና።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

創世記 20:1-18

亞伯拉罕與亞比米勒

1亞伯拉罕幔利遷往南地,住在加低斯書珥之間。在基拉耳寄居期間, 2他稱妻子撒拉是自己的妹妹。基拉耳亞比米勒派人帶走了撒拉

3晚上,上帝在夢中對亞比米勒說:「你的死期到了,因為你帶來的那個女人是別人的妻子。」 4亞比米勒還沒有親近撒拉,因此他說:「主啊,難道你要毀滅一個無辜的國家嗎? 5那人親口對我說這女人是他妹妹,她也說那人是她哥哥。我問心無愧,沒有做錯。」 6上帝在夢中對他說:「我知道你問心無愧,所以我才阻止你,不讓你親近她,免得你得罪我。 7現在你要把那人的妻子還給他,他是個先知,他會為你禱告,使你活命。要知道,如果你不這樣做,你和你的人民都必死。」

8亞比米勒清早起來召來他的臣僕,把這件事情告訴他們,他們聽了都十分害怕。 9亞比米勒召見亞伯拉罕,對他說:「你為什麼要害我們?我什麼地方得罪了你?你竟使我和我的人民陷入大罪!你不該這樣做。」 10又說:「你為什麼這樣做?」 11亞伯拉罕回答說:「因為我想這裡的人不敬畏上帝,他們必為了奪我妻子而殺我。 12況且,她真是我的妹妹,與我同父異母,後來做了我的妻子。 13上帝吩咐我離開家鄉到外面漂泊的時候,我對她說,『無論我們到哪裡,你都要說我是你哥哥,這就是你對我的恩情。』」

14於是,亞比米勒帶來牛、羊和男女僕婢送給亞伯拉罕,並把他妻子撒拉還給他, 15又對他說:「我的國土就在你面前,你想住在哪裡都可以。」 16亞比米勒撒拉說:「我給你哥哥十一公斤銀子,在你家人面前證明你是清白的,你沒有做錯什麼。」

17亞伯拉罕祈求上帝,上帝就治好了亞比米勒,也使他妻子和眾婢女恢復了生育能力。 18原來耶和華因為亞伯拉罕的妻子撒拉這件事,使亞比米勒宮中所有的婦女都不能生育。