ዘፍጥረት 17 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 17:1-27

የግዝረት ኪዳን

1አብራም ዕድሜው 99 ዓመት በሆነ ጊዜ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ተገልጦለት እንዲህ አለው፤ “እኔ ኤልሻዳይ17፥1 ሁሉን የሚገዛ ማለት ነው። ነኝ፤ በፊቴ ተመላለስ፤ ነቀፋም አይኑርብህ፤ 2በእኔና በአንተ መካከል የተመሠረተውን ኪዳን አጸናለሁ፤ ዘርህንም እጅግ አበዛለሁ።”

3አብራም በግንባሩ መሬት ላይ ተደፋ፤ እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) እንዲህ አለው፤ 4“እነሆ፤ የምገባልህ ኪዳን ይህ ነው፤ የብዙ ሕዝቦች አባት ትሆናለህ። 5ከእንግዲህ ወዲያ ስምህ አብራም17፥5 አብራም ማለት የከበረ አባት ማለት ነው። መባሉ ቀርቶ አብርሃም ይሆናል፤ የብዙ ሕዝቦች አባት አድርጌሃለሁና። 6ዘርህን እጅግ አበዛለሁ፤ ብዙ ሕዝብም አደርግሃለሁ፤ ነገሥታትም ከአንተ ይወጣሉ። 7በእኔና በአንተ፣ ከአንተም በኋላ ከዘርህ ጋር ከትውልድ እስከ ትውልድ የዘላለም ኪዳኔን እመሠርታለሁ፤ በዚህም የአንተና ከአንተም በኋላ የዘርህ አምላክ (ኤሎሂም) እሆናለሁ። 8ይህችን አሁን በእንግድነት የምትኖርባትን የከነዓንን ምድር በሙሉ ለአንተና ከአንተም በኋላ ለዘርህ ለዘላለም ርስት አድርጌ እሰጣለሁ፤ አምላካቸውም (ኤሎሂም) እሆናለሁ።”

9ከዚያም እግዚአብሔር (ኤሎሂም) አብርሃምን እንዲህ አለው፤ “በአንተም በኩል፣ አንተና ከአንተ በኋላ የሚመጣው ዘርህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ኪዳኔን ትጠብቃላችሁ። 10አንተና ከአንተም በኋላ የሚመጣው ዘርህ የምትጠብቁት ኪዳን ይህ ነው፤ በመካከላችሁ ያለ ወንድ ሁሉ ይገረዝ። 11ስለዚህ ሁላችሁም ሸለፈታችሁን ትገረዛላችሁ፤ ይህም በእኔና በእናንተ መካከል ላለው ኪዳን ምልክት ይሆናል። 12የሚመጣውም ትውልድ ሁሉ፣ ማንኛውም ወንድ ልጅ፣ ስምንት ቀን ሲሞላው ይገረዝ፤ እንደዚሁም በቤትህ የተወለደውና ከውጭ በገንዘብ የተገዛ ባዕድ ሁሉ ይገረዝ። 13በቤትህ የተወለደም ሆነ በገንዘብህ የተገዛ ሁሉ መገረዝ አለበት፤ በሥጋችሁ የሚፈጸመው ይህ ኪዳኔ የዘላለም ኪዳን ይሆናል። 14የሥጋ ሸለፈቱን ያልተገረዘ ማንኛውም ወንድ ኪዳኔን በማፍረሱ ከወገኖቹ ይወገድ።”

15እግዚአብሔር (ኤሎሂም) አብርሃምን እንዲህ አለው፤ “ሦራን ከእንግዲህ ሦራ ብለህ አትጠራትም፤ ስሟ ከዛሬ ጀምሮ ሣራ ይሁን። 16እኔ እባርካታለሁ ከእርሷም ወንድ ልጅ እሰጥሃለሁ፤ የብዙም ሕዝቦች እናት ትሆን ዘንድ እባርካታለሁ፤ የሕዝቦችም ነገሥታት ከእርሷ ይወጣሉ።”

17አብርሃምም በግንባሩ መሬት ላይ ተደፋ፤ ሣቀና በልቡ፣ “እንዲያው ምንስ ቢሆን የመቶ ዓመት ሽማግሌ የልጅ አባት መሆን ይችላልን? ሣራስ በዘጠና ዓመቷ ልጅ መውለድ ትችላለችን?” አለ። 18አብርሃም እግዚአብሔርን (ኤሎሂም)፣ “እስማኤልን ብቻ ባርከህ ባኖርህልኝ” አለው።

19እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) እንዲህ አለ፤ “ይሁን እሺ፤ ነገር ግን ሚስትህ ሣራ ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፤ ስሙንም ይስሐቅ17፥19 ይስሐቅ ማለት ይሥቃል ማለት ነው። ብለህ ትጠራዋለህ፤ እኔም ከእርሱ በኋላ ለዘሩ ሁሉ የሚሆን የዘላለም ኪዳን ከእርሱ ጋር እገባለሁ። 20ስለ እስማኤልም ቢሆን ልመናህን ሰምቼሃለሁ፤ እርሱንም እባርከዋለሁ፤ ፍሬያማም አደርገዋለሁ፤ እጅግም አበዛዋለሁ፤ የዐሥራ ሁለት አለቆች አባት ይሆናል፤ ታላቅም ሕዝብ አደርገዋለሁ። 21ኪዳኔን ግን የዛሬ ዓመት በዚሁ ጊዜ ሣራ ከምትወልድልህ ልጅ፣ ከይስሐቅ ጋር አደርጋለሁ።” 22እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ከአብርሃም ጋር መነጋገሩን ከፈጸመ በኋላ ወደ ላይ ወጣ።

23በዚያችም ዕለት አብርሃም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት ልጁን እስማኤልን፣ በቤቱ ውስጥ የተወለዱትንና ከውጭ በገንዘቡ የገዛቸውን ወንዶች በሙሉ ገረዛቸው። 24አብርሃም ሲገረዝ ዕድሜው 99 ዓመት ነበር። 25ልጁም እስማኤል ሲገረዝ 13 ዓመቱ ነበር። 26አብርሃምና ልጁ እስማኤል፣ ሁለቱም በዚያኑ ቀን ተገረዙ። 27በአብርሃም ቤት ያሉ ወንዶች ሁሉ፣ በቤቱ የተወለዱትም ሆኑ ከውጭ በገንዘብ የተገዙ ከእርሱ ጋር ተገረዙ።

Persian Contemporary Bible

پيدايش 17:1-27

وعده تولد اسحاق

1وقتی ابرام نود و نه ساله بود، خداوند بر او ظاهر شد و فرمود: «من خدای قادر مطلق هستم. از من اطاعت كن و آنچه راست است بجا آور. 2با تو عهد می‌بندم كه نسل تو را زياد كنم.»

3‏-4ابرام به خاک افتاد و خدا به وی گفت: «من با تو عهد می‌بندم كه قومهای بسيار از تو به وجود آورم. 5از اين پس نام تو ابرام نخواهد بود، بلكه ابراهيم؛17‏:5 «ابرام» يعنی «پدر سرافراز» و «ابراهيم» يعنی «پدر قومها».‏ زيرا من تو را پدر قومهای بسيار می‌سازم. 6نسل تو را زياد می‌كنم و از آنها قومها و پادشاهان به وجود می‌آورم. 7من عهد خود را تا ابد با تو و بعد از تو با فرزندانت، نسل اندر نسل برقرار می‌كنم. من خدای تو هستم و خدای فرزندانت نيز خواهم بود. 8تمامی سرزمين كنعان را كه اكنون در آن غريب هستی، تا ابد به تو و به نسل تو خواهم بخشيد و خدای ايشان خواهم بود.»

9‏-11خدا به ابراهيم فرمود: «وظيفهٔ تو و فرزندانت و نسلهای بعد، اين است كه عهد مرا نگاه داريد. تمام مردان و پسران شما بايد ختنه شوند تا بدين وسيله نشان دهند كه عهد مرا پذيرفته‌اند.

12«هر پسر هشت روزه بايد ختنه شود. اين قانون شامل تمام مردان خانه‌زاد و زرخريد هم می‌شود. 13همه بايد ختنه شوند و اين نشانی بر بدن شما خواهد بود از عهد جاودانی من. 14هر کس نخواهد ختنه شود، بايد از قومِ خود طرد شود، زيرا عهد مرا شكسته است.»

15خدا همچنين فرمود: «اما در خصوص سارای، زن تو: بعد از اين ديگر او را سارای مخوان. نام او ساره (يعنی ”شاهزاده“) خواهد بود. 16من او را بركت خواهم داد و از وی به تو پسری خواهم بخشيد. بلی، او را بركت خواهم داد و از او قومها به وجود خواهم آورد. از ميان فرزندان تو، پادشاهان خواهند برخاست.»

17آنگاه ابراهيم سجده كرد و خنديد و در دل خود گفت: «آيا برای مرد صد ساله پسری متولد شود و ساره در نود سالگی بزايد؟» 18پس به خدا عرض كرد: «خداوندا، همان اسماعيل را منظور بدار.»

19ولی خدا فرمود: «مطمئن باش خودِ ساره برای تو پسری خواهد زاييد و تو نام او را اسحاق (يعنی ”خنده“) خواهی گذاشت. من عهد خود را با او و نسل وی تا ابد برقرار خواهم ساخت. 20اما در مورد اسماعيل نيز تقاضای تو را اجابت نمودم و او را بركت خواهم داد و نسل او را چنان زياد خواهم كرد كه قوم بزرگی از او به وجود آيد. دوازده امير از ميان فرزندان او برخواهند خاست. 21اما عهد خود را با اسحاق كه ساره او را سال ديگر در همين موقع برای تو خواهد زاييد، استوار می‌سازم.»

22آنگاه خدا از سخن گفتن با ابراهيم باز ايستاد و از نزد او رفت. 23سپس ابراهيم، فرزندش اسماعيل و ساير مردان و پسرانی را كه در خانه‌اش بودند، چنانكه خدا فرموده بود ختنه كرد. 24‏-27در آن زمان ابراهيم نود و نه ساله و اسماعيل سيزده ساله بود. هر دو آنها در همان روز با ساير مردان و پسرانی كه در خانه‌اش بودند، چه خانه‌زاد و چه زرخريد، ختنه شدند.