ዘፍጥረት 10 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 10:1-32

የኖኅ ልጆች ትውልድ

1የኖኅ ልጆች የሴም፣ የካምና የያፌት ትውልድ ይህ ነው፤ እነርሱም ራሳቸው ከጥፋት ውሃ በኋላ ወንዶች ልጆችን ወለዱ።

የያፌት ዝርያዎች

10፥2-5 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥5-7

2የያፌት ልጆች፦10፥2 ልጆች ማለት ዘርዐ ትውልዶች ወይም ወራሾች ወይም ሕዝቦች ማለት ሊሆን ይችላል፤ በ3፡4፡6፡7፡20-23፡29 እና 31 እንዲሁ፤

ጋሜር፣ ማጎግ፣ ማዴ፣ ያዋን፣ ቶቤል፣ ሞሳሕ፣ ቴራስ ናቸው።

3የጋሜር ልጆች፦

አስከናዝ፣ ራፋት፣ ቴርጋማ ናቸው።

4የያዋን ልጆች፦

ኤሊሳ፣ ተርሴስ፣ ኪቲም፣ ሮዲኢ10፥4 ጥቂት የማሶሬቲክ የጥንት ጽሑፎች፣ ከኦሪተ ሳምራውያን፣ ሰብዓ ሊቃናትና አብዛኞቹ የማሶሬቲክ የጥናት ጽሑፎች የሚሉት ዶዳኒም ነው። ናቸው። 5ከእነዚህም በየነገዳቸው፣ በየጐሣቸውና በየቋንቋቸው ተከፋፍለው በባሕር ዳርና በደሴቶች፣ በየምድራቸው የሚኖሩ ሕዝቦች ወጡ።

የካም ዝርያዎች

10፥6-20 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥8-16

6የካም ልጆች፦

ኵሽ፣ ምጽራይም፣10፥6 13ትንም ጨምሮ ግብፅን ያመለክታል። ፉጥ፣ ከነዓን ናቸው።

7የኵሽ ልጆች፦

ሳባ፣ ኤውላጥ፣ ሰብታ፣ ራዕማ፣ ሰበቅታ ናቸው።

የራዕማ ልጆች፦

ሳባ፣ ድዳን ናቸው።

8ኵሽ የናምሩድ አባት10፥8 13፡15፡24 እና 26ትን ጨምሮ አባት ማለት ቅድመ አያት ወይም ተተኪ ወይም መሥራች ማለት ሊሆን ይችላል። ነበረ፤ ናምሩድም በምድር ላይ ኀያል ሰው እየሆነ ሄደ። 9በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ብርቱ ዐዳኝ ነበረ፤ ስለዚህም፣ “በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት እንደ ናምሩድ ብርቱ ዐዳኝ” ይባል ነበር። 10የግዛቱም የመጀመሪያ ከተሞች፦ ባቢሎን፣ ኦሬክ፣ አርካድና ካልኔ ናቸው፤ እነዚህ በ10፥10 ወይም ኦሬክና አርካድ፣ ሁሉም ሰናዖር10፥10 ባቢሎን ነው ምድር ነበሩ። 11ከዚያም ምድር ወደ አሦር ወጥቶ ነነዌን፣ ረሆቦትን፣10፥11 ወይም ነነዌ ከነከተማዋ አደባባዮች ካለህን 12እንዲሁም በነነዌና በካለህ መካከል ሬስን ቈረቈረ፤ ታላቁንም ከተማ መሠረተ።

13ምጽራይም፦

የሉዳማውያን፣ የዕሚማውያን፣ ላህቢያውያን፣ የነፍታሌማውያን፣ 14የፈትሩሲማውያን፣ ፍልስጥኤማውያን የተገኙባቸው የኮስሉሂማውያን፣ የቀፍቶሪማውያን አባት ነበረ።

15ከነዓንም፦

የበኵር ልጁ10፥15 ወይም ከሲዶናውያን የመጀመሪያው የሲዶን፣ የኬጢያውያን፣ 16የኢያቡሳውያን፣ የአሞራውያን፣ የጌርሳውያን አባት ነበረ፤ 17እንዲሁም የኤዊያውያን፣ የዑር ኬዋናውያን፣ የሲኒያውያን፣ 18የአራዴዎናውያን፣ የሰማሪናውያን፣ የአማቲያውያን አባት ነበረ።

ከጊዜ በኋላ የከነዓን ጐሣዎች በየስፍራው ተሠራጩ፤ 19የከነዓን ወሰን ከሲዶና አንሥቶ በጌራራ በኩል እስከ ጋዛ ይደርሳል፤ ከዚያም በሰዶም በኩል ገሞራን፣ አዳማንና ሰቦይን ይዞ እስከ ላሣ ይዘልቃል።

20እነዚህም በየጐሣቸውና በየቋንቋቸው፣ በየምድራቸውና በየነገዳቸው ይኖሩ የነበሩ የካም ዝርያዎች ናቸው።

የሴም ዝርያዎች

10፥21-31 ተጓ ምብ – ዘፍ 11፥10-271ዜና 1፥17-27

21ለያፌት ታላቅ ወንድም10፥21 ወይም ሴም፣ የ…ታላቅ ወንድም ለሴም ደግሞ ወንዶች ልጆች ተወለዱለት፤ እርሱም የዔቦር ልጆች ሁሉ ቅደመ አያት ነው።

22የሴም ልጆች፦

ኤላም፣ አሦር፣ አርፋክስድ፣ ሉድ፣ አራም ናቸው።

23የአራም ልጆች፦

ዑፅ፣ ሁል፣ ጌቴር፣ ሞሶሕ10፥23 ሰብዓ ሊቃናትንና 1ዜና 1፥17 ይመ፤ በዕብራይስጡ ማሽ ይለዋል። ናቸው።

24አርፋክስድ ሳላን ወለደ፤10፥24 ከዕብራይስጡ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን ሰብዓ ሊቃናት ግን የቃይናን አባት፣ ቃይናንም የ…አባት ነበረ ይላል።

ሳላም ዔቦርን ወለደ።

25ለዔቦርም ሁለት ወንዶች ልጆች ተወለዱለት፤

አንደኛው ልጅ በዘመኑ ምድር ተከፍላ ስለ ነበር ፍሌቅ10፥25 ፍሌቅ ማለት ክፍፍል ማለት ነው። ተባለ፤ ወንድሙም ዮቅጣን ተባለ።

26ዮቅጣንም፦

የኤልሞሳድ፣ የሣሌፍ፣ የሐስረሞት፣ የያራሕ፣ 27የሀደራም፣ የአውዛል፣ የደቅላ አባት ነበረ፤ 28እንዲሁም የዖባል፣ የአቢማኤል፣ የሳባ፣ 29የኦፊር፣ የኤውላጥ፣ የዮባል አባት ነበረ፤ እነዚህ ሁሉ የዮቅጣን ልጆች ናቸው።

30መኖሪያ ስፍራቸውም እስከ ሶፋር ድረስ ይዘልቃል።

31እነዚህም በየጐሣቸውና በየቋንቋቸው፣ በየምድራቸውና በየነገዳቸው ይኖሩ የነበሩ የሴም ዝርያዎች ናቸው።

32የኖኅ ወንዶች ልጆች ጐሣዎች እንደ ትውልዳቸው በየነገዳቸው እነዚህ ነበሩ። ከጥፋት ውሃ በኋላ ሕዝቦች በምድር ላይ የተሠራጩት ከእነዚሁ ነው።

Persian Contemporary Bible

پيدايش 10:1-32

انشعاب قومهای جهان

(اول تواريخ 1‏:5‏-23)

1اينها هستند نسل سام و حام و يافث، پسران نوح، كه بعد از طوفان متولد شدند:

نسل يافث

2پسران10‏:2 «پسران» می‌تواند به معنی «نسل» يا «اعقاب» و يا «قومها» باشد. همچنين در آيات 3‏،4‏،6‏،7‏،22‏،23‏،26‏،30‏.‏ يافث عبارت بودند از: جومر، ماجوج، مادای، ياوان، توبال، ماشَک و تيراس.

3پسران جومر: اَشكناز، ريفات و توجَرمِه.

4پسران ياوان: اليشه، ترشيش، كتيم و رودانيم.

5فرزندان اين افراد به تدریج در سواحل و جزاير دنيا پخش شدند و اقوامی را با زبانهای گوناگون به وجود آوردند.

نسل حام

6پسران حام عبارت بودند از: كوش، مصرايم، فوط و كنعان.

7پسران كوش: سبا، حويله، سبته، رعمه و سبتكا. پسران رعمه: شبا و ددان.

8يكی از فرزندان كوش، شخصی بود به نام نمرود كه در دنيا، دلاوری بزرگ و معروف گشت. 9او با قدرتی كه خداوند به وی داده بود، تيرانداز ماهری شد؛ از اين جهت، وقتی می‌خواهند از مهارتِ تيراندازی كسی تعريف كنند، می‌گويند: «خداوند تو را در تيراندازی مانند نمرود گرداند.» 10قلمرو فرمانروايی او ابتدا شامل بابل، ارک، اكد و كلنه در سرزمين شنعار10‏:10 شنعار همان سرزمين بابل است.‏ بود. 11‏-12ولی بعد كشور آشور را نيز به قلمرو خود درآورد و نينوا، رحوبوت عير، كالح و ريسن را (واقع در بين نينوا و كالح) كه با هم شهر بزرگی را تشكيل می‌دادند، در آن كشور بنا كرد.

13‏-14مصرايم، جد اقوام زير بود: لودی‌ها، عنامی‌ها، لهابی‌ها، نفتوحی‌ها، فتروسی‌ها، كسلوحی‌ها (كه فلسطينی‌ها از اين قوم به وجود آمدند) و كفتوری‌ها.

15‏-19صيدون پسر ارشد كنعان بود و از كنعان اقوام زير به وجود آمدند: حيتّی‌ها، يبوسی‌ها، اموری‌ها، جرجاشی‌ها، حوّی‌ها، عرقی‌ها، سينی‌ها، اروادی‌ها، صماری‌ها و حماتی‌ها. فرزندان كنعان از سرزمين صيدون به سمت جرار تا غزه و به طرف سدوم و عموره و ادمه و صبوئيم تا به لاشع پراكنده شدند.

20اينها نسل حام بودند كه در قبايل و سرزمينهای خود زندگی می‌كردند و هر يک زبان خاص خود را داشتند.

نسل سام

21از نسل سام، كه برادر بزرگ يافث بود، عابر به وجود آمد (عابر جد عبرانيان است). 22اين است اسامی پسران سام: عيلام، آشور، ارفكشاد، لود و ارام.

23اينانند پسران ارام: عوص، حول، جاتر و ماشک.

24ارفكشاد پدر شالح، و شالح پدر عابر بود.

25عابر صاحب دو پسر شد به نامهای: فالح (يعنی «تفرقه» زيرا در زمان او بود كه مردم دنيا متفرق شدند) و يُقطان.

26‏-30الموداد، شالف، حضرموت، يارح، هدورام، اوزال، دقله، عوبال، ابيمائيل، شبا، اوفير، حويله و يوباب پسران يُقطان بودند. ايشان از نواحی ميشا تا كوهستانهای شرقی سفاره پراكنده بودند و در آنجا زندگی می‌كردند.

31اينها بودند فرزندان سام كه در قبايل و سرزمينهای خود زندگی می‌كردند و هر يک زبان خاص خود را داشتند.

32همهٔ افرادی كه در بالا نام برده شدند، از نسل نوح بودند كه بعد از طوفان، در دنيا پخش شدند و قومهای گوناگون را به وجود آوردند.