ዘፍጥረት 10 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 10:1-32

የኖኅ ልጆች ትውልድ

1የኖኅ ልጆች የሴም፣ የካምና የያፌት ትውልድ ይህ ነው፤ እነርሱም ራሳቸው ከጥፋት ውሃ በኋላ ወንዶች ልጆችን ወለዱ።

የያፌት ዝርያዎች

10፥2-5 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥5-7

2የያፌት ልጆች፦10፥2 ልጆች ማለት ዘርዐ ትውልዶች ወይም ወራሾች ወይም ሕዝቦች ማለት ሊሆን ይችላል፤ በ3፡4፡6፡7፡20-23፡29 እና 31 እንዲሁ፤

ጋሜር፣ ማጎግ፣ ማዴ፣ ያዋን፣ ቶቤል፣ ሞሳሕ፣ ቴራስ ናቸው።

3የጋሜር ልጆች፦

አስከናዝ፣ ራፋት፣ ቴርጋማ ናቸው።

4የያዋን ልጆች፦

ኤሊሳ፣ ተርሴስ፣ ኪቲም፣ ሮዲኢ10፥4 ጥቂት የማሶሬቲክ የጥንት ጽሑፎች፣ ከኦሪተ ሳምራውያን፣ ሰብዓ ሊቃናትና አብዛኞቹ የማሶሬቲክ የጥናት ጽሑፎች የሚሉት ዶዳኒም ነው። ናቸው። 5ከእነዚህም በየነገዳቸው፣ በየጐሣቸውና በየቋንቋቸው ተከፋፍለው በባሕር ዳርና በደሴቶች፣ በየምድራቸው የሚኖሩ ሕዝቦች ወጡ።

የካም ዝርያዎች

10፥6-20 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥8-16

6የካም ልጆች፦

ኵሽ፣ ምጽራይም፣10፥6 13ትንም ጨምሮ ግብፅን ያመለክታል። ፉጥ፣ ከነዓን ናቸው።

7የኵሽ ልጆች፦

ሳባ፣ ኤውላጥ፣ ሰብታ፣ ራዕማ፣ ሰበቅታ ናቸው።

የራዕማ ልጆች፦

ሳባ፣ ድዳን ናቸው።

8ኵሽ የናምሩድ አባት10፥8 13፡15፡24 እና 26ትን ጨምሮ አባት ማለት ቅድመ አያት ወይም ተተኪ ወይም መሥራች ማለት ሊሆን ይችላል። ነበረ፤ ናምሩድም በምድር ላይ ኀያል ሰው እየሆነ ሄደ። 9በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ብርቱ ዐዳኝ ነበረ፤ ስለዚህም፣ “በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት እንደ ናምሩድ ብርቱ ዐዳኝ” ይባል ነበር። 10የግዛቱም የመጀመሪያ ከተሞች፦ ባቢሎን፣ ኦሬክ፣ አርካድና ካልኔ ናቸው፤ እነዚህ በ10፥10 ወይም ኦሬክና አርካድ፣ ሁሉም ሰናዖር10፥10 ባቢሎን ነው ምድር ነበሩ። 11ከዚያም ምድር ወደ አሦር ወጥቶ ነነዌን፣ ረሆቦትን፣10፥11 ወይም ነነዌ ከነከተማዋ አደባባዮች ካለህን 12እንዲሁም በነነዌና በካለህ መካከል ሬስን ቈረቈረ፤ ታላቁንም ከተማ መሠረተ።

13ምጽራይም፦

የሉዳማውያን፣ የዕሚማውያን፣ ላህቢያውያን፣ የነፍታሌማውያን፣ 14የፈትሩሲማውያን፣ ፍልስጥኤማውያን የተገኙባቸው የኮስሉሂማውያን፣ የቀፍቶሪማውያን አባት ነበረ።

15ከነዓንም፦

የበኵር ልጁ10፥15 ወይም ከሲዶናውያን የመጀመሪያው የሲዶን፣ የኬጢያውያን፣ 16የኢያቡሳውያን፣ የአሞራውያን፣ የጌርሳውያን አባት ነበረ፤ 17እንዲሁም የኤዊያውያን፣ የዑር ኬዋናውያን፣ የሲኒያውያን፣ 18የአራዴዎናውያን፣ የሰማሪናውያን፣ የአማቲያውያን አባት ነበረ።

ከጊዜ በኋላ የከነዓን ጐሣዎች በየስፍራው ተሠራጩ፤ 19የከነዓን ወሰን ከሲዶና አንሥቶ በጌራራ በኩል እስከ ጋዛ ይደርሳል፤ ከዚያም በሰዶም በኩል ገሞራን፣ አዳማንና ሰቦይን ይዞ እስከ ላሣ ይዘልቃል።

20እነዚህም በየጐሣቸውና በየቋንቋቸው፣ በየምድራቸውና በየነገዳቸው ይኖሩ የነበሩ የካም ዝርያዎች ናቸው።

የሴም ዝርያዎች

10፥21-31 ተጓ ምብ – ዘፍ 11፥10-271ዜና 1፥17-27

21ለያፌት ታላቅ ወንድም10፥21 ወይም ሴም፣ የ…ታላቅ ወንድም ለሴም ደግሞ ወንዶች ልጆች ተወለዱለት፤ እርሱም የዔቦር ልጆች ሁሉ ቅደመ አያት ነው።

22የሴም ልጆች፦

ኤላም፣ አሦር፣ አርፋክስድ፣ ሉድ፣ አራም ናቸው።

23የአራም ልጆች፦

ዑፅ፣ ሁል፣ ጌቴር፣ ሞሶሕ10፥23 ሰብዓ ሊቃናትንና 1ዜና 1፥17 ይመ፤ በዕብራይስጡ ማሽ ይለዋል። ናቸው።

24አርፋክስድ ሳላን ወለደ፤10፥24 ከዕብራይስጡ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን ሰብዓ ሊቃናት ግን የቃይናን አባት፣ ቃይናንም የ…አባት ነበረ ይላል።

ሳላም ዔቦርን ወለደ።

25ለዔቦርም ሁለት ወንዶች ልጆች ተወለዱለት፤

አንደኛው ልጅ በዘመኑ ምድር ተከፍላ ስለ ነበር ፍሌቅ10፥25 ፍሌቅ ማለት ክፍፍል ማለት ነው። ተባለ፤ ወንድሙም ዮቅጣን ተባለ።

26ዮቅጣንም፦

የኤልሞሳድ፣ የሣሌፍ፣ የሐስረሞት፣ የያራሕ፣ 27የሀደራም፣ የአውዛል፣ የደቅላ አባት ነበረ፤ 28እንዲሁም የዖባል፣ የአቢማኤል፣ የሳባ፣ 29የኦፊር፣ የኤውላጥ፣ የዮባል አባት ነበረ፤ እነዚህ ሁሉ የዮቅጣን ልጆች ናቸው።

30መኖሪያ ስፍራቸውም እስከ ሶፋር ድረስ ይዘልቃል።

31እነዚህም በየጐሣቸውና በየቋንቋቸው፣ በየምድራቸውና በየነገዳቸው ይኖሩ የነበሩ የሴም ዝርያዎች ናቸው።

32የኖኅ ወንዶች ልጆች ጐሣዎች እንደ ትውልዳቸው በየነገዳቸው እነዚህ ነበሩ። ከጥፋት ውሃ በኋላ ሕዝቦች በምድር ላይ የተሠራጩት ከእነዚሁ ነው።

Het Boek

Genesis 10:1-32

De nakomelingen van Noach

1Dit zijn de nakomelingen van Sem, Cham en Jafet, de drie zonen van Noach, want na de watervloed werden hun zonen geboren. 2De zonen van Jafet waren Gomer, Magog, Madai, Jawan, Tubal, Mesech en Tiras.

3De zonen van Gomer waren Askenaz, Rifat en Togarma. 4De zonen van Jawan waren Elisa, Tarsis, de Kittieten en de Dodanieten. 5Hun nakomelingen werden de zeevaarders die langs de kust wonen en ieder een eigen taal hebben.

6De zonen van Cham waren Kus, Misraïm, Put en Kanaän. 7De zonen van Kus waren Saba, Chawila, Sabta, Rama en Sabtecha. 8De zonen van Rama waren Seba en Dedan. Een van de nakomelingen van Kus heette Nimrod. Hij werd de eerste machthebber op aarde. 9Hij was een geweldig jager, door niemand overtroffen. De naam Nimrod werd een begrip voor de mensen. Zij zeiden: ‘Hij is een Nimrod,’ waarmee dan werd bedoeld dat iemand een geweldenaar was. 10De basis van zijn koninkrijk waren de steden Babel, Uruk, Akkad en Kalne in het land Sinear. 11-12 Van daaruit trok hij naar Assyrië en bouwde daar Ninevé, Rechobot-Ir, Kalach en Resen. Die laatste stad lag tussen Ninevé en Kalach en was de belangrijkste stad van het rijk.

13-14 Misraïm was de voorvader van de Ludieten, de Anamieten, de Lehabieten, de Naftuchieten, de Patrusieten, de Kasluchieten, waaruit de Filistijnen zijn voortgekomen en de Kretenzers.

15-19Kanaäns oudste zoon heette Sidon en diens broer heette Chet. De volgende volken zijn afstammelingen van Kanaän: de Jebusieten, de Amorieten, de Girgasieten, de Chiwwieten, de Arkieten, de Sinieten, de Arwadieten, de Semarieten en de Hamatieten. De nakomelingen van Kanaän verspreidden zich van Sodom, Gomorra, Adma en Seboïm tot Lesa. 20Al deze volken, die zich overal verspreidden en veel verschillende talen spraken, waren nakomelingen van Cham.

21Eber was een afstammeling van Sem, de oudste broer van Jafet. 22Hier volgen de zonen van Sem: Elam, Assur, Arpachsad, Lud en Aram. 23De zonen van Aram waren Us, Chul, Geter en Mas. 24De zoon van Arpachsad heette Selach en diens zoon heette Eber. 25Eber kreeg twee zonen: Peleg (dat betekent Verdeeldheid, tijdens zijn leven verdeelde God de talen van de mensen) en Joktan. 26-30Joktan was de vader van Almodad, Selef, Chasarmawet, Jerach, Hadoram, Uzal, Dikla, Obal, Abimaël, Seba, Ofir, Chawila en Jobab. De afstammelingen van Joktan leefden in het gebied tussen Mescha en het in het oosten gelegen gebergte van Sefar. 31Al deze mensen waren afstammelingen van Sem, verdeeld per geslacht, taal, land en volk.

32Dit was het geslachtsregister van Noach en zijn zonen. Door de geslachten heen verspreidden hun afstammelingen zich over de aarde en vormden zo de volken.