ዘፀአት 7 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 7:1-25

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “ልብ በል፤ እኔ አንተን ለፈርዖን እንደ አምላክ (ኤሎሂም) አድርጌሃለሁ፤ ወንድምህ አሮንም ያንተ ነቢይ ይሆናል። 2እኔ የማዝህን ሁሉ ትናገራለህ፤ ወንድምህ አሮንም እስራኤላውያንን ከአገሩ እንዲወጡ ይለቅቃቸው ዘንድ ለፈርዖን ይነግረዋል። 3እኔ ግን የፈርዖንን ልብ አደነድናለሁ፤ ታምራዊ ምልክቶችንና ድንቆችን በግብፅ ላይ በብዛት ባደርግም እንኳ፣ አይሰማችሁም። 4ከዚያም እጄን በግብፅ ላይ አደርጋለሁ፤ በኀያል ፍርድም ሰራዊቴን፣ ሕዝቤን እስራኤላውያንን አወጣለሁ። 5እጄን በግብፅ ላይ ስዘረጋና እስራኤላውያንንም ከዚያ ሳወጣ፣ ግብፃውያን እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) መሆኔን ያውቃሉ።”

6ሙሴና አሮን እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ አዘዛቸው አደረጉ። 7ፈርዖንን ባነጋገሩበት ጊዜ ሙሴ ዕድሜው ሰማንያ ዓመት፣ አሮን ደግሞ ሰማንያ ሦስት ነበር።

የአሮን በትር እባብ ሆነች

8እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፣ 9“ፈርዖን፣ ‘ታምር አሳዩኝ’ ባላችሁ ጊዜ፣ አሮንን እንዲህ በለው፤ ‘በትርህን ውሰድና በፈርዖን ፊት ጣላት፤’ ከዚያም እባብ ትሆናለች።”

10ስለዚህ ሙሴና አሮን ወደ ፈርዖን ሄደው እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዛቸው አደረጉ። አሮን በትሩን በፈርዖንና በሹማምቱ ፊት ጣላት፤ እባብም ሆነች። 11ከዚያም ፈርዖን ጠቢባኑንና መተተኞቹን ጠራ፤ የግብፅ አስማተኞችም በድብቅ ጥበባቸው ያንኑ አደረጉ፤ 12እያንዳንዱ የያዛትን በትር ጣለ፤ እባብም ሆነች። ነገር ግን የአሮን በትር የእነርሱን በትሮች ዋጠች። 13ሆኖም የፈርዖን ልብ ደነደነ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ተናግሮ እንደ ነበረውም አላዳመጣቸውም።

የደም መቅሠፍት

14ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “የፈርዖን ልብ ደነደነ፤ ሕዝቡን ለመልቀቅ አልፈቀደም። 15ወደ ውሃው በሚሄድበት ጊዜ ማልደህ ወደ ፈርዖን ሂድ፤ እንድታገኘውም በአባይ ዳር ተጠባበቅ፤ ወደ እባብ ተለውጣ የነበረችውንም በትር በእጅህ ያዝ። 16ከዚያም እንዲህ በለው፤ ‘የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) “ሕዝቤ በምድረ በዳ ያመልኩኝ ዘንድ እንዲሄዱ ልቀቃቸው” ብዬ እንድነግርህ ላከኝ፤ አንተ ግን እስካሁን ድረስ እሺ አላልህም። 17እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚለው ይህ ነው፤ “እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ሆንሁ በዚህ ታውቃለህ፤ እይ በዚህች በእጄ በያዝኋት በትር የአባይን ውሃ እመታለሁ፤ ወደ ደምም ይለወጣል። 18በአባይ ወንዝ ውስጥ ያለው ዓሣ ይሞታል፤ ወንዙ ይከረፋል፤ ግብፃውያንም ውሃውን መጠጣት አይችሉም።” ’ ”

19እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “አሮንን፣ ‘በትርህን ውሰድና በግብፅ ውሆች ላይ፣ ይኸውም በምንጮች፣ በቦዮች፣ በኵሬዎችና በውሃ ማጠራቀሚያዎች ላይ እጅህን ዘርጋ’ ብለህ ንገረው፤ ወደ ደምም ይለወጣሉ። ከዕንጨትና ከድንጋይ በተሠሩ ውሃ መያዣዎች ውስጥም ሳይቀር በግብፅ ምድር ደም በየቦታው ይሆናል።”

20ሙሴና አሮን እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ አዘዛቸው አደረጉ። እርሱም በንጉሡና በሹማምንቱ ፊት በትሩን አንሥቶ የአባይን ወንዝ ውሃ መታ፤ ውሃውም በሙሉ ወደ ደም ተለወጠ። 21በአባይ ያሉት ዓሦች ሞቱ፤ ወንዙም ከመከርፋቱ የተነሣ ግብፃውያኑ ውሃውን ሊጠጡት አልቻሉም። በግብፅ ምድር ሁሉ ደም ነበረ።

22የግብፅ አስማተኞች በድብቅ ጥበባቸው ተመሳሳይ ነገር አደረጉ፤ የፈርዖንም ልብ ደነደነ፤ ልክ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ተናገረው ሙሴንና አሮንን አልሰማቸውም። 23ተመልሶ ወደ ቤተ መንግሥቱ ገባ እንጂ ይህን ከቁም ነገር አልቈጠረውም። 24ግብፃውያን ሁሉ የወንዙን ውሃ መጠጣት ባለመቻላቸው ውሃ ለማግኘት የአባይን ዳር ይዘው ጕድጓድ ቈፈሩ።

25እግዚአብሔር (ያህዌ) አባይን ከመታ ሰባት ቀን ዐለፈ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

出埃及記 7:1-25

亞倫和摩西面見法老

1耶和華對摩西說:「我要使你在法老面前像上帝一樣,你哥哥亞倫是你的發言人。 2你要把我吩咐你的話告訴你哥哥亞倫,由他要求法老讓以色列人離開埃及3可是,我要使法老的心剛硬,雖然我在埃及行許多神蹟奇事, 4他將無動於衷。那時,我必伸手重重地懲罰埃及,然後領我的大隊子民離開埃及5埃及人看見我伸手攻擊他們、把以色列人帶出埃及,就會知道我是耶和華。」 6摩西亞倫便遵命而行。 7去見法老的時候,摩西八十歲,亞倫八十三歲。

8耶和華對摩西亞倫說: 9「倘若法老要你們行神蹟給他看,你就吩咐亞倫把手杖丟在法老面前,使杖變作蛇。」

10摩西亞倫照耶和華的吩咐來到法老面前。亞倫把手杖丟在法老和他的臣僕面前,杖就變作蛇。 11法老召他的謀士和巫師前來,這些人是埃及的術士,他們也用邪術如法炮製。 12各人將自己的手杖扔在地上,杖就變作蛇,但亞倫的杖吞噬了他們的杖。 13法老卻仍然硬著心,不肯聽從摩西亞倫,正如耶和華所言。

水變血之災

14耶和華對摩西說:「法老非常頑固,不肯釋放百姓。 15明天早晨,法老會去尼羅河邊,你就在那裡等他,要拿著曾變成蛇的手杖。 16你要對他說,『希伯來人的上帝耶和華差遣我來告訴你,要讓祂的子民到曠野去事奉祂,但到如今你還是不肯。 17所以祂說要用手杖擊打尼羅河水,使河水變成血,好叫你知道祂是耶和華。 18河裡的魚會死,河水會發臭,埃及人不能再喝尼羅河的水。』」

19耶和華對摩西說:「你告訴亞倫,讓他向埃及境內的各江河、溪流、池塘伸杖,使水變成血。埃及境內,包括木桶和石缸裡將到處是血。」 20摩西亞倫就按著耶和華所吩咐的去做,亞倫在法老和埃及眾臣僕面前舉杖擊打尼羅河水,河水都變成了血。 21河裡的魚都死了,河水臭得不能飲用。埃及遍地都是血。 22可是,法老的巫師也一樣用邪術使水變成血。法老的心仍然剛硬,不肯聽從摩西亞倫的話,正如耶和華所言。 23法老若無其事地轉身回宮去了。 24因為河水不能飲用,埃及人就在尼羅河兩岸掘井取水飲用。

25擊打河水後,七天過去了。