ዘፀአት 40 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 40:1-38

የማደሪያውን ድንኳን መትከል

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ 2“ማደሪያውን ይኸውም የመገናኛውን ድንኳን በወሩ የመጀመሪያ ቀን ትከለው፤ 3የምስክሩን ታቦት በውስጡ አኑር፤ ታቦቱንም በመጋረጃው ጋርደው። 4ጠረጴዛውንም ወደ ውስጥ አምጥተህ ዕቃዎቹን በላዩ ላይ አሰናዳ፤ ከዚያም መቅረዙን አስገብተህ መብራቶቹን በቦታቸው አስቀምጥ። 5የዕጣኑን የወርቅ መሠዊያ በምስክሩ ታቦት ፊት ለፊት አስቀምጠው፤ ከማደሪያውም መግቢያ ላይ መጋረጃውን አድርግ።

6“የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውን በማደሪያው መግቢያ ፊት ለፊት፣ በመገናኛው ድንኳን አስቀምጠው። 7የመታጠቢያውን ሰን በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አኑርበት፤ ውሃም አኑርበት። 8በዙሪያውም የአደባባዩን ቅጥር ትከል፤ መጋረጃውንም በአደባባዩ መግቢያ ላይ አድርገው።

9“ቅብዐ ዘይቱን ወስደህ ማደሪያውንና በውስጡ ያለውን ሁሉ ቅባ፤ እርሱንና ዕቃውን ሁሉ ቀድስ፤ የተቀደሰም ይሆናል። 10ከዚያም የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውንና ዕቃዎቹን ሁሉ ቅባ፤ መሠዊያውን ቀድስ፣ እጅግም የተቀደሰ ይሆናል። 11የመታጠቢያው ሰንና ማስቀመጫውን ቅባ፤ ቀድሳቸውም።

12“አሮንና ወንዶች ልጆቹን ወደ መገናኛው ድንኳን መግቢያ አምጥተህ በውሃ ዕጠባቸው። 13ከዚያም አሮንን የተቀደሰውን ልብስ አልብሰው፤ ካህን ሆኖ ያገለግለኝ ዘንድ ቅባው፤ ቀድሰውም። 14ወንዶች ልጆቹን አምጥተህ ሸሚዝ አልብሳቸው። 15ካህናት ሆነው ያገለግሉኝ ዘንድ ልክ አባታቸውን እንደ ቀባህ ቅባቸው፤ መቀባታቸውም በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ለሚቀጥል ክህነት ነው።” 16ሙሴ ሁሉንም ነገር ልክ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው አደረገ።

17እንዲሁም በሁለተኛው ዓመት፣ የመጀመሪያው ወር በገባ በመጀመሪያው ቀን የማደሪያው ድንኳን ተተከለ። 18ሙሴ የማደሪያውን ድንኳን በተከለ ጊዜ፣ መቆሚያዎቹን በቦታቸው አኖረ፤ ወጋግራዎቹን አቆመ፤ አግዳሚዎቹን አስገባ፤ ምሰሶዎቹንም ተከለ። 19ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው ድንኳኑን በማደሪያው ላይ፣ መደረቢያውንም በድንኳኑ ላይ ዘረጋው።

20ምስክሩን ወስዶ በታቦቱ ውስጥ አስቀመጠው፤ መሎጊያዎቹንም ከታቦቱ ጋር አያያዛቸው፤ የስርየት መክደኛውንም በላዩ ላይ አደረገው። 21ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው ታቦቱን ወደ ማደሪያው ድንኳን አስገብቶ መከለያ መጋረጃውን ሰቀለ፤ የምስክሩንም ታቦት ጋረደው።

22ሙሴ ጠረጴዛውን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ፣ ከማደሪያው በስተ ሰሜን ከመጋረጃው ውጭ አኖረው፤ 23እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም ኅብስቱን በላዩ ላይ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አኖረ።

24መቅረዙን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ከጠረጴዛው ትይዩ ከማደሪያው ድንኳን በስተ ደቡብ በኩል አኖረው፤ 25እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም መብራቶቹን በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አበራ።

26ሙሴ የወርቅ መሠዊያውን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ከመጋረጃው ፊት ለፊት አኖረው፤ 27እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም መልካም መዐዛ ያለውን ዕጣን አጠነበት። 28ከዚያም መጋረጃውን በማደሪያው ድንኳን መግቢያ ላይ ሰቀለው።

29የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውንም በማደሪያው፣ በመገናኛው ድንኳን መግቢያ ላይ አኖረው፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህሉን መሥዋዕት በላዩ ላይ አቀረበ።

30የመታጠቢያውን ሰን በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አስቀመጠ፤ ለመታጠቢያም ውሃ አደረገበት፤ 31ሙሴና አሮን፣ ወንዶች ልጆቹም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ይታጠቡበት ነበር። 32እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዳዘዘው ወደ መገናኛው ድንኳን በገቡና ወደ መሠዊያው በቀረቡ ቍጥር ይታጠቡ ነበር።

33ከዚያም ሙሴ በማደሪያውና በመሠዊያው ዙሪያ አደባባዩን ተከለ፤ በአደባባዩም መግቢያ ላይ መጋረጃውን ሰቀለ፤ እንደዚህ አድርጎ ሙሴ ሥራውን ፈጸመ።

የእግዚአብሔር ክብር

34ከዚያም ደመናው የመገናኛውን ድንኳን ሸፈነ፤ የእግዚአብሔርም (ያህዌ) ክብር ማደሪያውን ሞላ። 35ደመናው በላዩ ላይ ስለ ነበረና የእግዚአብሔርም (ያህዌ) ክብር ማደሪያውን ስለ ሞላው፣ ሙሴ ወደ መገናኛው ድንኳን መግባት አልቻለም።

36በእስራኤላውያን ጕዞ ሁሉ ደመናው ከማደሪያው ላይ በተነሣ ጊዜ፣ ይጓዙ ነበር፤ 37ደመናው ካልተነሣ ግን፣ እስከሚነሣበት ቀን ድረስ አይጓዙም ነበር። 38ስለዚህ በጕዟቸው ሁሉ ወቅት፣ በእስራኤል ቤት ፊት ሁሉ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ደመና በቀን ከማደሪያው በላይ፣ በሌሊትም እሳቱ በደመናው ውስጥ ነበር።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

出埃及記 40:1-38

支起會幕

1耶和華對摩西說: 2「你要在一月一日支起聖幕,即會幕, 3把約櫃安置在裡面,用幔子遮掩。 4把桌子搬進去,擺好桌上的器具,再把燈臺搬進去,點上燈, 5把燒香的金壇放在約櫃前面,掛上聖幕入口的簾子。 6要把燔祭壇放在聖幕前面, 7洗濯盆放在會幕和祭壇中間,盆裡要有水。 8用帷幔在聖幕四周圍成院子,在院子的入口掛上簾子。 9你要用膏油抹聖幕和裡面所有的器具,使它們分別出來,成為聖潔之物。 10要抹燔祭壇和壇上所有器具,使燔祭壇分別出來,成為至聖之物。 11要抹洗濯盆和盆座,使它們分別出來,成為聖潔之物。 12要把亞倫父子們叫到會幕入口,用水為他們沐浴, 13亞倫穿上聖衣後膏立他,使他分別出來,做聖潔的祭司事奉我。 14也要把他的兒子們叫來,給他們穿上內袍, 15用同樣的儀式膏立他們,使他們做祭司事奉我。他們的受膏將使他們永遠做祭司,世代相傳。」

16摩西照耶和華的吩咐把事情都辦好了。 17第二年一月一日,聖幕支起來了。 18摩西支起聖幕,裝上帶凹槽的底座,豎起木板,插上橫閂,立起柱子, 19在聖幕上面搭起罩棚,鋪上頂蓋,都遵照耶和華的吩咐。 20他把約版放在約櫃裡,橫杠穿在約櫃的兩旁,施恩座放在約櫃上, 21把約櫃抬進聖幕,掛起幔子遮掩約櫃,都遵照耶和華的吩咐。 22他把桌子放在會幕內、遮掩約櫃的幔子外面、聖幕的北側, 23將獻給耶和華的供餅放在桌上,都遵照耶和華的吩咐。 24他把燈臺放在會幕內的桌子對面,在聖幕的南側, 25然後在耶和華面前點燈,都遵照耶和華的吩咐。 26他把金香壇放在會幕裡、遮掩約櫃的幔子前面, 27在壇上點燃芬芳的香,都遵照耶和華的吩咐。 28他掛上聖幕入口的簾子, 29在會幕,即聖幕入口的前面設立燔祭壇,在壇上獻燔祭和素祭,都遵照耶和華的吩咐。 30他把洗濯盆放在會幕和祭壇之間,盆裡盛水,供洗濯用。 31摩西亞倫及其眾子都在那裡清洗手腳, 32他們進會幕或走近祭壇的時候,都要先清洗,都遵照耶和華的吩咐。 33摩西又在聖幕和祭壇的四周用帷幔圍成院子,然後在院子入口掛上簾子。這樣,摩西完成了工作。

耶和華的榮光

34那時,有雲彩遮蓋會幕,耶和華的榮光充滿了聖幕。 35摩西不能進會幕,因為雲彩停在上面,耶和華的榮光充滿了聖幕。 36一路上,雲彩從聖幕升起,他們就出發。 37雲彩不升起,他們就不出發,一直等到雲彩升起。 38一路上,白天有耶和華的雲彩停留在聖幕上面,夜間雲中有火光為以色列百姓照明。