ዘፀአት 35 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 35:1-35

የሰንበት ሥርዐቶች

1ሙሴ የእስራኤልን ማኅበረ ሰብ ሁሉ ሰብስቦ እንዲህ አላቸው፤ “እግዚአብሔር (ያህዌ) እንድትፈጽሟቸው ያዘዛችሁ ነገሮች እነዚህ ናቸው፤ 2ስድስት ቀን ሥራ ይሠራል፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የሰንበት ዕረፍት፣ የተቀደሰ ቀን ይሆንላችኋል፤ በዕለቱ ማናቸውንም ዐይነት ሥራ የሚሠራ ቢኖር ሞት ይገባዋል። 3በሰንበት ቀን በማናቸውም መኖሪያዎቻችሁ ውስጥ እሳት አታንድዱ።”

ለመገናኛው ድንኳን ዕቃዎች

35፥4-9 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥1-7

35፥10-19 ተጓ ምብ – ዘፀ 39፥32-41

4ሙሴ ለእስራኤላውያን ማኅበረ ሰብ ሁሉ እንዲህ አላቸው፤ “እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘው ይህ ነው፤ 5ካላችሁ ንብረት ሁሉ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት አቅርቡ፤ ፈቃደኛ የሆነ ማንም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የወርቅ፣ የብር፣ የናስ መባ ያምጣ። 6ሰማያዊ፣ ሐምራዊና ቀይ ማግ፤ ቀጭን ሐር፣ የፍየል ጠጕር፣ 7ቀይ የተነከረ የአውራ በግ ቈዳ፣ እንዲሁም አቆስጣ ቈዳ35፥7 በዚህና በቍጥር 23 ላይ አንዳንድ ቅጆች፣ የለፋ የአቆስጣ ቈዳ ይላሉ።፣ የግራር ዕንጨት፤ 8ለመብራት የወይራ ዘይት፣ ለቅብዐ ዘይቱና ለጣፋጭ ሽታ ዕጣን ቅመም፤ 9በኤፉዱና በደረት ኪሱ ላይ የሚሆኑ መረግዶችና ሌሎች ዕንቍዎችን መባ አድርጎ ያምጣ።

10“በመካከላችሁ ጥበበኞች የሆኑ ሁሉ መጥተው እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘውን ሁሉ ይሥሩ፤ 11የመገናኛውን ድንኳን ከነድንኳኑና ከነመደረቢያው፣ ማያያዣዎችን፣ ክፈፎችን፣ አግዳሚዎችን፣ ቋሚዎችንና መሠረቶችን፤ 12ታቦቱን ከነመሎጊያዎቹ፣ የስርየት መክደኛውንና የሚሸፍነውን መጋረጃ፤ 13ጠረጴዛውን ከነመሎጊያዎቹ፣ ዕቃዎቹን ሁሉና የሀልዎቱን ኅብስት፤ 14ለመብራት የሆነውን መቅረዝ ከነዕቃዎቹ፣ ቀንዲሎችንና ለመብራት የሚሆነውን ዘይት፤ 15የዕጣን መሠዊያውን ከነመሎጊያዎቹ፣ ቅብዐ ዘይቱንና ጣፋጭ ሽታ ያለውን ዕጣን፤ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ላይ የሚሆነውን የመግቢያ መጋረጃ፤ 16የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውን ከናስ መጫሪያው፣ መሎጊያዎቹንና ዕቃዎቹን ሁሉ፣ የናስ ሰኑን ከነማስቀመጫው፣ 17የአደባባዩን መጋረጃዎች ከነምሰሶዎቻቸውና ከነመሠረቶቹ፣ ያደባባዩን መግቢያ መጋረጃ፤ 18ለመገናኛው ድንኳንና ለአደባባዩ የሚሆኑ የድንኳን ካስማዎችና ገመዶቻቸው፤ 19በመቅደሱ ውስጥ ለማገልገል የሚለበሱ የፈትል ልብሶችን ይኸውም የካህኑ የአሮንን የተቀደሱ ልብሶችንና ካህናት ሆነው ሲያገለግሉ የሚለብሷቸውን የወንዶች ልጆቹን ልብሶች ይሥሩ።”

20ከዚያም የእስራኤል ማኅበረ ሰብ ሁሉ ከሙሴ ፊት ወጡ፤ 21ፈቃደኛ የነበረና ልቡን ያነሣሣው ሁሉ በመምጣት ለመገናኛው ድንኳን ሥራ፣ ለአገልግሎቱ ሁሉና ለተቀደሱ ልብሶች የሚሆን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መባ አመጡ። 22ፈቃደኛ የነበሩ ሁሉ፣ ወንዶችም ሴቶችም መጥተው ከሁሉም ዐይነት የወርቅ ጌጦች አመጡ፤ የአፍንጫ ጌጦችን፣ ሎቲዎችን፣ ቀለበቶችን፣ ድሪዎችንና ጌጣጌጦችን ሁሉ አመጡ፤ ሁሉም ወርቃቸውን እንደሚወዘወዝ መሥዋዕት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቀረቡ። 23ሰማያዊ፣ ሐምራዊ ወይም ቀይ ማግ ወይም ቀጭን ሐር ወይም የፍየል ጠጕር፣ ቀይ የተነከረ የአውራ በግ ቈዳ ወይም የአቆስጣ ቈዳ አመጡ። 24የብር ወይም የናስ መባ ማቅረብ የቻሉ ሁሉ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መባ አድርገው አመጡ፤ የግራር ዕንጨት ያለው ሁሉ አስፈላጊ በሆነው ሥራ እንዲውል አመጣው። 25ጥበበኞች የሆኑ ሴቶች ሁሉ በእጃቸው ፈተሉ፤ የፈተሉትንም ሰማያዊ ሐምራዊ ወይም ቀይ ማግ ወይም ቀጭን በፍታ አመጡ። 26ፈቃደኛ የነበሩና ጥበቡ ያላቸው ሴቶች ሁሉ የፍየል ጠጕር ፈተሉ። 27መሪዎቹም ኤፉድና በደረት ኪሱ ላይ እንዲሆን የከበሩ ድንጋዮችንና ሌሎች ዕንቍዎች አመጡ። 28እንዲሁም ለመብራቱ፣ ለቅብዐ ዘይቱና ለጣፋጭ ሽታ ዕጣን የሚሆኑ ቅመሞችንና የወይራ ዘይትን አመጡ። 29ፈቃደኛ የሆኑ እስራኤላውያን ወንዶችና ሴቶች ሁሉ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) በሙሴ በኩል እንዲያከናውኑት ላዘዛቸው ሥራ ሁሉ የበጎ ፈቃድ ስጦታዎችን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አመጡ።

ባስልኤልና ኤልያብ

35፥30-35 ተጓ ምብ – ዘፀ 31፥2-6

30ከዚያም ሙሴ እስራኤላውያንን አላቸው፤ “እነሆ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ከይሁዳ ነገድ የሆነውን የሆር ልጅ፣ የኡሪን ልጅ ባስልኤልን መርጧል። 31በጥበብ፣ በችሎታና በዕውቀት፣ በማናቸውም ዐይነት ሙያ የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም) መንፈስ ሞልቶበታል፤ 32ይኸውም በወርቅ፣ በብርና በናስ የጥበብ ሥራ እንዲሠራ ነው፤ 33ድንጋዮችን እንዲጠርብና እንዲያወጣ፣ የዕንጨት ሥራ እንዲሠራና ማንኛውንም ዐይነት የጥበብ ሙያ እንዲያከናውን ነው። 34እንዲሁም ለእርሱና ከዳን ነገድ ለሆነው ለአሂሳሚክ ልጅ ለኤልያብ፣ ለሁለቱም ሌሎችን የማስተማር ችሎታ ሰጣቸው። 35የጥበብ ባለሙያዎች፣ ዕቅድ አውጭዎች፣ በሰማያዊ በሐምራዊና በቀይ ማግ፣ በቀጭን ሐር ጥልፍ ጠላፊዎችና ፈታዮች፤ ሁሉም ዋና የጥበብ ባለሙያዎችና ዕቅድ አውጭዎች በመሆን ማንኛውንም ዐይነት ሥራ ያከናውኑ ዘንድ በጥበብ ሞልቷቸዋል።

Persian Contemporary Bible

خروج 35:1-35

مقررات روز سبت

1موسی تمام قوم اسرائيل را دور خود جمع كرد و به ايشان گفت: «اين است دستوراتی كه خداوند به شما داده است تا از آن اطاعت كنيد: 2فقط شش روز كار كنيد و روز هفتم را كه روز مقدس خداوند است استراحت و عبادت نماييد. هر كس كه در روز هفتم كار كند بايد كشته شود. 3آن روز در خانه‌هايتان حتی آتش هم روشن نكنيد.»

هدايا برای خيمهٔ عبادت

(خروج 25‏:1‏-9)

4سپس موسی به قوم اسرائيل گفت: «خداوند فرموده كه 5از آنچه داريد برای او هديه بياوريد. هدايای كسانی كه از صميم قلب هديه می‌دهند بايد شامل اين چيزها باشد: طلا، نقره، مفرغ؛ 6نخهای آبی، ارغوانی و قرمز؛ كتان لطيف؛ پشم بز؛ 7پوست قوچ كه رنگش سرخ شده باشد و پوست خز؛ چوب اقاقيا؛ 8روغن زيتون برای چراغها؛ مواد خوشبو برای تهيهٔ روغن مسح؛ بخور خوشبو؛ 9سنگ جزع و سنگهای قيمتی ديگر برای ايفود35‏:9 نگاه کنيد به 25‏:7؛ همچنين آيهٔ 27.‏ و سينه‌بند كاهن.

مقررات ساختن عبادتگاه

(خروج 39‏:32‏-43)

10«شما ای صنعتگران ماهر، بياييد و آنچه را كه خداوند امر فرموده است، بسازيد: 11خيمهٔ عبادت و پوششهای آن، تكمه‌ها، چوب‌بست خيمه، پشت‌بندها، ستونها و پايه‌ها؛ 12صندوق عهد و چوبهای حامل آن، تخت رحمت، پردهٔ حايل بين قدس و قدس‌الاقداس؛ 13ميز و چوبهای حامل آن و تمام ظروف آن، نان مقدس؛ 14چراغدان با چراغها و روغن و لوازم ديگر آن؛ 15قربانگاه بخور و چوبهای حامل آن، روغن تدهين و بخور خوشبو؛ پردهٔ در ورودی خيمه؛ 16قربانگاه قربانی سوختنی، منقل مشبک مفرغی قربانگاه و چوبهای حامل با تمام لوازم آن؛ حوض مفرغی با پايهٔ آن؛ 17پرده‌های دور حياط، ستونها و پايه‌های آنها، پردهٔ در ورودی حياط؛ 18ميخهای خيمه و حياط خيمه و طنابهای آن؛ 19لباسهای بافته شده برای خدمت در قدس يعنی لباس مقدس هارون كاهن و لباسهای پسرانش.»

قوم هديه تقديم می‌كنند

20پس تمام قوم اسرائيل از نزد موسی رفتند، 21اما كسانی كه تحت تأثير قرار گرفته بودند با اشتياق بازگشتند و هدايايی برای آماده ساختن لباسهای مقدس، خيمه و وسايل مورد نياز جهت خدمت در آن، با خود آوردند تا به خداوند تقديم كنند. 22مردان و زنان با اشتياق زياد آمدند و جواهراتی از قبيل سنجاق، گوشواره، انگشتر، گردنبند و اشیا ديگری از طلا تقديم كردند. 23برخی نيز نخهای آبی، ارغوانی و قرمز؛ كتان لطيف؛ پشم بز؛ پوست سرخ شدهٔ قوچ و پوست خز آوردند. 24عده‌ای ديگر نقره و مفرغ به خداوند تقديم كردند. بعضی هم چوب اقاقيا برای ساختن خيمه با خود آوردند.

25‏-26زنانی كه در كار ريسندگی مهارت داشتند، نخهای آبی و ارغوانی و قرمز و كتان لطيف و پشم بز ريسيدند و آوردند. 27بزرگان قوم، سنگ جزع و سنگهای قيمتی ديگر برای تزيين ايفود و سينه‌بند كاهن آوردند، 28و نيز عطريات و روغن برای روشنايی و روغن مسح و بخور معطر. 29بدين ترتيب تمام مردان و زنان بنی‌اسرائيل كه مشتاق بودند در كاری كه خداوند به موسی امر فرموده بود كمک كنند، با خرسندی خاطر هدايای خود را به خداوند تقديم كردند.

صنعتگران هنرمند

(خروج 31‏:1‏-11)

30‏-31سپس موسی به قوم گفت: «خداوند، بصل‌ئيل (پسر اوری) را كه نوهٔ حور و از قبيلهٔ يهودا است برگزيده و او را از روح خود پر ساخته است و حكمت و توانايی و مهارت بخشيده، تا خيمهٔ عبادت و تمام وسايل آن را بسازد. 32او در ساختن ظروف طلا و نقره و مفرغ، 33همچنين در كار خراطی و جواهر سازی و هر صنعتی استاد است. 34خدا به او و اهولياب (پسر اخيسامک از قبيلهٔ دان) استعداد تعليم دادن هنر به ديگران را عطا فرموده است. 35خداوند به آنها در كار طراحی، نساجی و طرازی پارچه‌های آبی، ارغوانی، قرمز و كتان لطيف مهارت خاصی بخشيده است. ايشان صنعتگران ماهری هستند.