ዘፀአት 31 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 31:1-18

ባስልኤልና ኤልያብ

31፥2-6 ተጓ ምብ – ዘፀ 35፥30-35

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“እነሆ፤ ከይሁዳ ነገድ የሆር የልጅ ልጅ የሆነውን የኡሪን ልጅ ባስልኤልን መርጬዋለሁ። 3በሁሉም ዐይነት የእጅ ጥበብ ሥራ፣ ብልኀት፣ ችሎታና ዕውቀት እንዲኖረው የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም) መንፈስ ሞልቼዋለሁ። 4ይኸውም በወርቅ፣ በብርና በናስ ለሚሠሩት ሥራዎች በጥበብ የተሠሩ ጌጦችን እንዲያበጅ፣ 5ድንጋዮችን እንዲቈፍርና እንዲጠርብ ከዕንጨትም ጥርብ እንዲያወጣ፣ ሁሉንም ዐይነት የእጅ ጥበብ ሥራዎችን እንዲያከናውን ነው። 6በተጨማሪም ከዳን ነገድ የሆነውን የአሂሳሚክን ልጅ ኤልያብን እንዲረዳው መርጬዋለሁ፤ እንዲሁም ያዘዝሁህን ሁሉ ያደርጉ ዘንድ ለእጅ ጥበብ ዐዋቂዎች ሁሉ ብልኀትን ሰጥቻቸዋለሁ፤

7“ይኸውም የመገናኛውን ድንኳን፣

የምስክሩን ታቦት በላዩ ላይ ካለው ከስርየት መክደኛው ጋር፣

ሌሎች የድንኳኑን መገልገያ ዕቃዎች ሁሉ፣

8ጠረጴዛውን ከነዕቃዎቹ፣

ከንጹሕ ወርቅ የተሠራውን የወርቅ መቅረዝ ከነዕቃዎቹ፣

የዕጣኑን መሠዊያ፣

9የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውን ከነዕቃዎቹ፣

ሰኑን፣ ከነማስቀመጫው፣

10ከፈትል የተሠሩ ልብሶችን ይኸውም የካህኑን የአሮንን የተቀደሱ ልብሶችንና ካህናት ሆነው ሲያገለግሉ የሚለብሷቸውን የወንድ ልጆቹ ልብሶች፣

11እንዲሁም የመቅደሱ የሆነውን ቅብዐ ዘይትና ጣፋጭ ሽታ ያለውን ዕጣን እንዲሠሩ ነው።

“ልክ እኔ እንዳዘዝሁህ ያብጇቸው።”

ሰንበት

12ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 13“ለእስራኤላውያን ንገራቸው፤ ‘ሰንበቴን ማክበር አለባችሁ፤ ይህም በእኔና በእናንተ መካከል በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ምልክት ይሆናል፤ ይኸውም የምቀድሳችሁ31፥13 ወይም፣ ቅዱስ አድርጌ የምለያችሁ እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ሆንሁ እንድታውቁ ነው።

14“ ‘ለእናንተ ቅዱስ ነውና ሰንበትን አክብሩ፤ ማንም ቢሽረው በሞት ይቀጣል፤ በዚያ ቀን ማንም የሚሠራ ቢኖር ከወገኑ ተነጥሎ ይለይ። 15ስድስት ቀን ሥራ ይሠራል፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ የዕረፍት ሰንበት ነው፤ በሰንበት ቀን ማንም ቢሠራ በሞት መቀጣት አለበት። 16እስራኤላውያን በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ሰንበትን በመጠበቅ የዘላለም ኪዳን አድርገው ማክበር አለባቸው፤ 17በእኔና በእስራኤላውያን መካከል ለዘላለም ምልክት ይሆናል፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሰማይንና ምድርን በስድስት ቀን ሠርቶ፣ በሰባተኛው ቀን ከሥራ ታቅቦ ዐርፏልና።’ ”

18እግዚአብሔር (ያህዌ) በሲና ተራራ ላይ ለሙሴ መናገሩን ከፈጸመ በኋላ፣ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም) ጣት የተጻፈባቸውን የድንጋይ ጽላቶች፣ ሁለቱን የምስክር ጽላቶች ለእርሱ ሰጠው።

King James Version

Exodus 31:1-18

1And the LORD spake unto Moses, saying, 2See, I have called by name Bezaleel the son of Uri, the son of Hur, of the tribe of Judah: 3And I have filled him with the spirit of God, in wisdom, and in understanding, and in knowledge, and in all manner of workmanship, 4To devise cunning works, to work in gold, and in silver, and in brass, 5And in cutting of stones, to set them, and in carving of timber, to work in all manner of workmanship. 6And I, behold, I have given with him Aholiab, the son of Ahisamach, of the tribe of Dan: and in the hearts of all that are wise hearted I have put wisdom, that they may make all that I have commanded thee; 7The tabernacle of the congregation, and the ark of the testimony, and the mercy seat that is thereupon, and all the furniture of the tabernacle,31.7 furniture: Heb. vessels 8And the table and his furniture, and the pure candlestick with all his furniture, and the altar of incense,31.8 furniture: Heb. vessels 9And the altar of burnt offering with all his furniture, and the laver and his foot,31.9 furniture: Heb. vessels 10And the cloths of service, and the holy garments for Aaron the priest, and the garments of his sons, to minister in the priest’s office, 11And the anointing oil, and sweet incense for the holy place: according to all that I have commanded thee shall they do.

12¶ And the LORD spake unto Moses, saying, 13Speak thou also unto the children of Israel, saying, Verily my sabbaths ye shall keep: for it is a sign between me and you throughout your generations; that ye may know that I am the LORD that doth sanctify you. 14Ye shall keep the sabbath therefore; for it is holy unto you: every one that defileth it shall surely be put to death: for whosoever doeth any work therein, that soul shall be cut off from among his people. 15Six days may work be done; but in the seventh is the sabbath of rest, holy to the LORD: whosoever doeth any work in the sabbath day, he shall surely be put to death.31.15 holy: Heb. holiness 16Wherefore the children of Israel shall keep the sabbath, to observe the sabbath throughout their generations, for a perpetual covenant. 17It is a sign between me and the children of Israel for ever: for in six days the LORD made heaven and earth, and on the seventh day he rested, and was refreshed.

18¶ And he gave unto Moses, when he had made an end of communing with him upon mount Sinai, two tables of testimony, tables of stone, written with the finger of God.