ሙሴና የሚንበለበለው ቍጥቋጦ
1አንድ ቀን ሙሴ የምድያም ካህን የሆነውን የአማቱን የዮቶር በጎችና ፍየሎች እየጠበቀ ሳለ፣ መንጋውን እየነዳ ወደ ምድረ በዳው ዳርቻ አምርቶ የእግዚአብሔር (ኤሎሂም) ተራራ ተብሎ ወደሚጠራው ወደ ኮሬብ ቀረበ።
2እዚያም የእግዚአብሔር (ያህዌ) መልአክ በቍጥቋጦው ውስጥ በሚንቀለቀል የእሳት ነበልባል መካከል ተገለጠለት። ሙሴም ቍጥቋጦው በእሳት ቢያያዝም እንኳ፣ አለ መቃጠሉን አየ። 3ሙሴም፣ “ቍጥቋጦው ለምን እንደማይቃጠል ቀረብ ብዬ ይህን አስገራሚ ነገር ልመልከት” አለ።
4ሙሴ ሁኔታውን ለመመልከት መቅረቡን እግዚአብሔር (ያህዌ) ባየ ጊዜ፣ ከቍጥቋጦው ውስጥ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) “ሙሴ፣ ሙሴ” ብሎ ጠራው፤ ሙሴም “አቤት እነሆኝ” አለው። 5እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “ወደዚህ እንዳትቀርብ፤ ይህች የቆምህባት ምድር የተቀደሰች ስለሆነች ጫማህን አውልቅ” አለው። 6ቀጥሎም፣ “እኔ የአባቶችህ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ (ኤሎሂም) ነኝ” አለው። በዚህ ጊዜ ሙሴ እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ፊት ለፊት ማየት ስለ ፈራ ፊቱን ሸፈነ።
7ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለ፣ “በግብፅ አገር የሚኖሩትን የሕዝቤን መከራ አይቻለሁ፤ ከአሠሪዎቻቸው ጭካኔ የተነሣ የሚያሰሙትንም ጩኸት ሰምቻለሁ፤ ሥቃያቸውንም ተረድቼአለሁ። 8ስለዚህም ከግብፃውያን እጅ ልታደጋቸውና ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ሰፊና ለም ወደሆነችው ወደ ከነዓናውያን፣ ኬጢያውያን፣ አሞራውያን፣ ፌርዛውያን፣ ኤዊያውያንና ኢያቡሳውያን ምድር ላወጣቸው ወርጃለሁ። 9አሁንም የእስራኤል ልጆች ጩኸት ወደ እኔ ደርሷል፤ ግብፃውያን የሚያደርሱባቸውን ግፍ አይቻለሁ። 10በል እንግዲህ ና፤ ሕዝቤን፣ የእስራኤልን ልጆች ከግብፅ ምድር እንድታወጣቸው ወደ ፈርዖን እልክሃለሁ”።
11ሙሴ እግዚአብሔርን (ኤሎሂም)፣ “ወደ ፈርዖን የምሄድና የእስራኤልን ልጆች ከግብፅ የማወጣ እኔ ማን ነኝ?” አለው።
12እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ እኔ የላክሁህ ለመሆኑ ምልክቱ ይህ ነው፤ ሕዝቡን ከግብፅ ካወጣሃቸው በኋላ በዚህ ተራራ ላይ እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ታመልካላችሁ” አለው።
13ሙሴም እግዚአብሔርን (ኤሎሂም)፣ “ወደ እስራኤል ልጆች ሄጄ፣ ‘የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ልኮኛል’ ስላቸው ‘ስሙ ማን ነው?’ ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላቸዋለሁ?” አለው።
14እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ሙሴን፣ “እኔ፣ ያለሁና የምኖር ነኝ3፥14 ወይም እኔ የምሆነው እኔኑ ነው ማለት ሊሆን ይችላል። (ያህዌ)፤ ስለዚህም፣ ‘ያለና የሚኖር ልኮኛል’ ብለህ ንገራቸው” አለው።
15ደግሞም እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሙሴን፣ “የአባቶቻችሁ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቆብ አምላክ የሆነው እግዚአብሔር3፥15 በዕብራይስጥ እግዚአብሔር የሚለው ቃል ድምፅ በ14 ላይ፣ እኔ ነኝ ከሚለው ሐረግ ጋር ተመሳሳይ ድምፅ አለው። ያህዌ የሚለውም የቃል ውልደት እኔ ነኝ ከሚለው ሐረግ ነው። (ያህዌ) ወደ እናንተ ልኮኛል፤ ስሜም ለዘለዓለም ይኸው ነው፤ ወደ ፊት በተከታታይ በሚነሣው ትውልድ ሁሉ የምታሰበው በዚህ ስም ነው ብለህ ለእስራኤል ልጆች ንገራቸው” አለው።
16“ሂድና የእስራኤልን አለቆች ሰብስበህ፣ የአባቶቻችሁ የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ የሆነው እግዚአብሔር (ያህዌ) ተገለጠልኝና እንዲህ አለኝ፤ ጐብኝቻችኋለሁ፤ በግብፅ የደረሰባችሁንም አይቻለሁ። 17ስለዚህም በግብፅ ከምትቀበሉት መከራ አውጥቼ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ወደ ከነዓናውያን፣ ወደ ኬጢያውያን፣ ወደ አሞራውያን፣ ወደ ፌርዛውያን፣ ወደ ኤዊያውያንና ኢያቡሳውያን ምድር አገባችኋለሁ ብሏል ብለህ ንገራቸው” አለኝ።
18“የእስራኤል አለቆችም ይሰሙሃል። አንተና የእስራኤል አለቆች ወደ ግብፅ ንጉሥ ትሄዱና፣ ‘የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር (ያህዌ) ተገለጠልን፤ ስለዚህም ወደ ምድረ በዳ የሦስት ቀን መንገድ ተጕዘን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት እንድናቀርብ ፍቀድልን’ ብላችሁ ትነግሩታላችሁ። 19የግብፅ ንጉሥ ግን በኀያል ክንድ ካልተገደደ በስተቀር መቼም እንደማይለቅቃችሁ ዐውቃለሁ። 20ስለዚህ እኔ እጅግ ድንቅ የሆኑ ታምራትን እዚያው እመካከላቸው በማድረግ ክንዴን ዘርግቼ ግብፃውያንን እመታቸዋለሁ፤ ከዚያም በኋላ እንድትሄዱ ይለቃችኋል።
21“ይህ ሕዝብ በግብፃውያን ዘንድ የመወደድን ጸጋ እንዲያገኝ ስለማደርግ በምትወጡበት ጊዜ ባዶ እጃችሁን አትሄዱም። 22እያንዳንዷ ዕብራዊት ከጎረቤቷም ይሁን አብራት ከምትኖረው ግብፃዊት የብርና የወርቅ ጌጣጌጦች እንደዚሁም ልብስ እንድትሰጣት ትጠይቅ። እነዚህንም ሁሉ ወስዳችሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁን ታስጌጧቸዋላችሁ፤ ታለብሷቸዋላችሁም። በዚህም መንገድ የግብፃውያኑን ሀብት በእጃችሁ አግብታችሁ ትወጣላችሁ።”
موسی به پيامبری برگزيده میشود
1روزی هنگامی كه موسی مشغول چرانيدن گلهٔ پدر زن خود يَترون، كاهن مديان بود، گله را به آن سوی بيابان، به طرف كوه حوريب، معروف به كوه خدا راند. 2ناگهان فرشتهٔ خداوند چون شعلهٔ آتش از ميان بوتهای بر او ظاهر شد. موسی ديد كه بوته شعلهور است، ولی نمیسوزد. 3با خود گفت: «عجيب است! چرا بوته نمیسوزد؟» پس نزديک رفت تا علتش را بفهمد.
4وقتی خداوند ديد كه موسی به بوته نزديک میشود، از ميان بوته ندا داد: «موسی! موسی!»
موسی جواب داد: «بلی!»
5خدا فرمود: «بيش از اين نزديک نشو! كفشهايت را از پای درآور، زيرا مكانی كه در آن ايستادهای، زمين مقدسی است. 6من خدای اجداد تو ابراهيم، اسحاق و يعقوب هستم.» موسی روی خود را پوشاند، چون ترسيد به خدا نگاه كند.
7خداوند فرمود: «من رنج و مصيبت بندگان خود را در مصر ديدم و نالهشان را برای رهايی از بردگی شنيدم. 8حال، آمدهام تا آنها را از چنگ مصریها آزاد كنم و ايشان را از مصر بيرون آورده، به سرزمين پهناور و حاصلخيزی كه در آن شير و عسل جاری است ببرم، سرزمينی كه اينک قبايل كنعانی، حيتّی، اموری، فرزّی، حوّی و يبوسی در آن زندگی میكنند. 9آری، نالههای بنیاسرائيل به گوش من رسيده است و ظلمی كه مصریها به ايشان میكنند، از نظر من پنهان نيست. 10حال، تو را نزد فرعون میفرستم تا قوم مرا از مصر بيرون آوری.»
11موسی گفت: «خدايا، من كيستم كه نزد فرعون بروم و بنیاسرائيل را از مصر بيرون آورم؟»
12خدا فرمود: «من با تو خواهم بود و وقتی بنیاسرائيل را از مصر بيرون آوردی، در همين كوه مرا عبادت خواهيد كرد. اين نشانهای خواهد بود كه من تو را فرستادهام.»
13موسی عرض كرد: «اگر پيش بنیاسرائيل بروم و به ايشان بگويم كه خدای اجدادشان، مرا برای نجات ايشان فرستاده است، و آنها از من بپرسند: ”نام او چيست؟“ به آنها چه جواب دهم؟»
14خدا فرمود: «هستم آنكه هستم! به ايشان بگو ”هستم“ مرا نزد شما فرستاده است. 15بلی، به ايشان بگو: خداوند3:15 در زبان عبری، کلمهٔ «خداوند» شبيه کلمهٔ «هستم» میباشد و احتمالاً از آن اخذ شده است. يعنی خدای اجداد شما، خدای ابراهيم، اسحاق و يعقوب مرا پيش شما فرستاده است. اين نام جاودانهٔ من است و تمام نسلها مرا به اين نام خواهند شناخت.»
16سپس، خدا به موسی دستور داد: «برو و تمام رهبران اسرائيل را جمع كن و به ايشان بگو: خداوند، خدای اجداد شما ابراهيم، اسحاق و يعقوب بر من ظاهر شد و فرمود كه رفتاری را كه در مصر با شما میشود، ديده است و به ياری شما آمده است. 17او وعده فرموده است كه شما را از سختيهايی كه در مصر میكشيد، آزاد كند و به سرزمينی ببرد كه در آن شير و عسل جاری است، سرزمينی كه اينک كنعانیها، حيتیها، اموریها، فرزیها، حویها و يبوسیها در آن زندگی میكنند.
18«آنگاه بزرگان اسرائيل سخن تو را خواهند پذيرفت. تو همراه آنان به حضور پادشاه مصر برو و به او بگو: ”خداوند، خدای عبرانیها، بر ما ظاهر شده و دستور داده است كه به فاصلهٔ سه روز راه، به صحرا برويم و در آنجا برای خداوند، خدای خود قربانی كنيم.“
19«ولی من میدانم كه پادشاه مصر اجازه نخواهد داد كه برويد، مگر اينكه زير فشار قرار بگيرد. 20پس من با قدرت و معجزات خود، مصر را به زانو درمیآورم، تا فرعون ناچار شود شما را رها كند. 21همچنين كاری میكنم كه مصریها برای شما احترام قايل شوند، به طوری كه وقتی آن سرزمين را ترک میگوييد، تهيدست نخواهيد رفت. 22هر زن اسرائيلی از همسايه و از بانوی خود لباس و جواهرات خواهد خواست و با آن پسران و دختران خود را زينت خواهد داد. به اين ترتيب شما مصريان را غارت خواهيد نمود.»