ዘፀአት 23 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 23:1-33

የፍትሕና የምሕረት ሕጎች

1“የሐሰት ወሬ አትንዛ፤ ተንኰል ያለበትን ምስክርነት በመስጠት ክፉውን ሰው አታግዝ።

2“ክፉ በማድረግ ብዙዎችን አትከተል፤ በሕግ ፊት ምስክርነት ስትሰጥ፣ ከብዙዎቹ ጋር ተባብረህ ፍትሕ አታጣምም። 3በዳኝነት ጊዜ ለድኻው አታድላ።

4“የጠላትህ በሬ ወይም አህያ ሲባዝን ብታገኘው ወደ እርሱ መልሰው። 5የሚጠላህ ሰው አህያ፣ ጭነት ከብዶት ወድቆ ብታየው ርዳው እንጂ ትተኸው አትሂድ።

6“በዳኝነት ጊዜ በድኻው ላይ ፍርድ አታጓድልበት። 7ከሐሰት ክስ ራቅ፤ በደል የሌለበትን ወይም ትክክለኛውን ሰው ለሞት አሳልፈህ አትስጥ፣ በደለኛውን ንጹሕ አላደርግምና።

8“ጕቦ አትቀበል፤ ጕቦ አጥርተው የሚያዩትን ሰዎች ዐይን ያሳውራል፤ የጻድቃንንም ቃል ያጣምማልና።

9“መጻተኛውን አትጨቍን፤ በግብፅ መጻተኛ ስለ ነበራችሁ፣ መጻተኛ ምን እንደሚሰማው እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁና።

የሰንበት ሕጎች

10“ስድስት ዓመት በዕርሻህ ላይ ዝራ፤ አዝመራንም ሰብስብ፤ 11ነገር ግን በሰባተኛው ዓመት ምድሪቱን ሳትጠቀምባትና ሳታርሳት እንዲሁ ተዋት፤ ከዚያም በወገንህ መካከል ያሉት ድኾች ከእርሷ ምግብ ያገኛሉ፤ የዱር አራዊትም ከእነርሱ የተረፈውን ይበላሉ። በወይን ቦታህና በወይራ ዛፎችህም ላይ እንዲሁ አድርግ።

12“ስድስት ቀን ሥራህን ሥራ፤ በሬህና አህያህ በቤትህ የተወለደው ባሪያና መጻተኛው ያርፉ ዘንድ በሰባተኛው ቀን ምንም አትሥራ።

13“ያልኋችሁን ሁሉ ታደርጉ ዘንድ ተጠንቀቁ፤ የሌሎችን አማልክት ስም አትጥሩ፤ ከአፋችሁም አይስሙ።

ሦስቱ ዐውደ ዓመታዊ በዓላት

14“በዓመት ሦስት ጊዜ ለእኔ በዓልን ታከብራላችሁ።

15“ያልቦካ የቂጣ በዓልን አክብር፤ እንዳዘዝሁህ ሰባት ቀን እርሾ የሌለውን ቂጣ ብላ፤ ይህንም በአቢብ ወር በተወሰነ ቀን አድርግ፤ በዚያ ወር ከግብፅ ወጥተሃልና።

“ማንም በፊቴ ባዶ እጁን አይቅረብ።

16“በማሳህ ላይ በዘራኸው እህል በኵራት የመከርን በዓል አክብር።

“በዓመቱ መጨረሻ በማሳህ ላይ ያለውን እህልህን ስትሰበስብ የመክተቻውን በዓል አክብር።

17“በዓመት ሦስት ጊዜ ወንድ ሁሉ በጌታ በእግዚአብሔር (አዶናይ ያህዌ) ፊት ይቅረብ።

18“የመሥዋዕትን ደም እርሾ ካለበት ነገር ጋር አድርገህ ለእኔ አታቅርብ።

“የበዓል መሥዋዕቴ ስብ እስከ ንጋት ድረስ አይቈይ።

19“የምድርን ምርጥ ፍሬ በኵራት ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አምጣ።

“ጠቦት ፍየልን በእናቱ ወተት አትቀቅል።

የእግዚአብሔር መልአክ መንገድ ስለ መምራቱ

20“እነሆ፤ በጕዞ ላይ ሳለህ የሚጠብቅህንና ወዳዘጋጀሁልህ ስፍራ የሚያስገባህን መልአክ በፊትህ ልኬልሃለሁ። 21በጥንቃቄ ተከተለው፤ የሚናገረውንም ልብ ብለህ አድምጠው፤ አታምፅበት። ስሜ በእርሱ ላይ ነውና ዐመፅህን ይቅር አይልም። 22የሚናገረውን በጥንቃቄ ብታደምጥና ያልኩህን ሁሉ ብታደርግ ለጠላቶችህ ጠላት እሆናለሁ፤ የሚቃወሙህን እቃወማለሁ። 23መልአኬ በፊትህ ይሄዳል፤ አንተንም ወደ አሞራውያን፣ ወደ ኬጢያውያን፣ ወደ ፌርዛውያን፣ ወደ ከነዓናውያን፣ ወደ ኤዊያውያንና ኢያቡሳውያን ምድር ያስገባሃል፤ እኔም እነርሱን አጠፋቸዋለሁ። 24ለአማልክቶቻቸው አትስገድ፤ ወይም አታምልካቸው፤ ወይም ልምዳቸውን አትከተል፤ እነርሱን ማፈራረስ አለብህ፤ የአምልኮ ድንጋዮቻቸውንም ሰባብር። 25አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) አምልክ፤ በረከቱም በምትበላውና በምትጠጣው ላይ ይሆናል፤ በሽታንም ከአንተ ዘንድ አርቃለሁ። 26በምድርህም የሚያስወርዳት ወይም መካን ሴት አትኖርም፤ ረዥም ዕድሜም እሰጥሃለሁ።

27“በሚያጋጥሙህ አሕዛብ ሁሉ ላይ ማስፈራቴን በፊትህ እልካለሁ፤ ግራም አጋባቸዋለሁ፤ ጠላቶችህ ሁሉ ወደ ኋላ ተመልሰው እንዲሸሹ አደርጋለሁ። 28ኤዊያውያንን፣ ከነዓናውያንን፣ ኬጢያውያንን ከመንገድህ ለማስወጣት ተርብን በፊትህ እሰድዳለሁ። 29ነገር ግን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አላወጣቸውም፤ ምክንያቱም ምድሪቱ ባድማ ሆና የዱር አራዊት ይበዙባችኋል። 30ቍጥርህ ጨምሮ ምድሪቱን ለመውረስ እስክትበቃ ድረስ ጥቂት በጥቂት ከፊታችሁ አባርራቸዋለሁ።

31“ድንበርህን ከቀይ ባሕር23፥31 በዕብራይስጥ፣ ያም ሱፍ ይባላል፤ ይኸውም፣ የደንገል ባሕር ማለት ነው። እስከ ፍልስጥኤም ባሕር፣23፥31 የሜዲትራንያን ከምድረ በዳው እስከ ወንዙ23፥31 የኤፍራጥስ ድረስ አደርገዋለሁ፤ በምድሪቱም ላይ የሚኖሩትን ሰዎች አሳልፌ እሰጥሃለሁ፤ አንተም አሳድደህ ከፊትህ ታስወጣቸዋለህ። 32ከእነርሱም ሆነ ከአማልክቶቻቸው ጋር ኪዳን አታድርግ። 33በምድርህ ላይ እንዲኖሩ አትፍቀድላቸው፤ አለዚያ እኔን እንድትበድል ያደርጉሃል፤ አማልክታቸውን ማምለክ በርግጥ ወጥመድ ይሆንብሃልና።”

Korean Living Bible

출애굽기 23:1-33

모든 사람에게 공정하라

1“너희는 헛된 소문을 퍼뜨리지 말며 허위 증언을 하여 악한 사람을 돕지 말아라.

2“너희는 다수를 따라 악을 행하지 말고 법정에서 증언할 때 대중의 편이 되어 허위 진술을 하지 말며

3소송 문제를 다룰 때 가난한 사람이라고 해서 두둔하지 말아라.

4“너희가 원수의 소나 나귀가 길을 잃고 헤매는 것을 보거든 그에게 끌어다 주어라.

5또 너희를 미워하는 사람이 짐을 실은 채 쓰러져 있는 나귀를 일으키려고 애쓰는 것을 보거든 그냥 지나가지 말고 그를 도와주어라.

6“너희는 가난한 사람의 소송 문제라고 해서 공정하지 못한 재판을 해서는 안 된다.

7또 허위 문책을 해서는 안 되며 죄 없는 자나 정직한 자를 죽이는 일이 있어서도 안 된다. 나는 그런 악한 짓을 하는 악인을 절대로 용서하지 않을 것이다.

8너희는 뇌물을 받지 말아라. 뇌물은 사람의 눈을 멀게 하고 의로운 사람의 진술을 묵살시킨다.

9“너희는 외국인을 학대하지 말아라. 너희도 이집트에서 외국인이었으므로 너희는 외국인의 심정이 어떠한지 알고 있다.”

안식년과 안식일에 관한 법

10“너희는 6년 동안만 너희 땅에 파종하여 수확을 거두고

117년째 되는 해에는 땅을 갈지 말고 묵혀 두어라. 거기서 저절로 자라는 것은 가난한 사람들이 먹게 하고 남은 것은 들짐승이 먹게 하라. 그리고 너희 포도원과 감람원에도 그렇게 하라.

12“너희는 6일 동안만 일하고 7일째 되는 날에는 휴식하여 너희 소와 나귀가 쉴 수 있게 하고 너희 집의 종들과 외국인이 휴식을 취할 수 있게 하라.

13“너희는 내가 말한 모든 것을 조심스럽게 지켜라. 그리고 다른 신들의 이름은 부르지도 말고 그 신들을 너희 입으로 들먹이지도 말아라.”

3대 명절

14“너희는 매년 세 명절을 지켜라.

15내가 너희에게 명령한 대로 너희가 이집트에서 나온 23:15 히 ‘아빕월’1월의 정한 때에 무교절을 지켜라. 너희는 7일 동안의 이 명절 기간에 누룩 넣지 않은 빵을 먹어야 하며 나에게 경배하러 올 때에는 빈손으로 오는 자가 없어야 한다.

16“너희는 밭에 씨를 뿌려 수확한 곡식의 첫열매로 맥추절을 지켜라. “너희는 농산물을 거둬들여 저장하는 연말에 수장절을 지켜라.

17매년 이 세 명절에 너희 모든 남자들은 너희 하나님 나 여호와에게 경배하러 와야 한다.

18“너희는 나에게 희생제물의 피를 누룩이 든 빵과 함께 드리지 말며 이 명절 동안 나에게 바친 희생제물의 기름을 다음날 아침까지 남겨 두지 말아라.

19“너희는 추수한 첫열매 중에서 제일 좋은 것을 너희 하나님 나 여호와의 집으로 가져오너라. “너희는 염소 새끼를 그 어미의 젖으로 삶지 말아라.”

천사를 통해 길을 인도하고 보호하겠다는 약속

20“내가 한 천사를 너희 앞에 보내 너희가 길을 가는 동안 줄곧 너희를 보호하여 내가 예비한 곳에 너희를 인도하도록 하겠다.

21너희는 그의 말을 잘 듣고 순종하며 그에게 거역하지 말아라. 그는 내 이름으로 보냄을 받은 자이므로 너희가 거역하는 것을 용서하지 않을 것이다.

22그러나 너희가 그에게 순종하고 내가 말하는 모든 것을 행하면 내가 너희 원수에게 원수가 되고 너희 대적에게 대적이 될 것이다.

23나의 천사가 너희 선두에 서서 너희를 아모리족, 헷족, 브리스족, 가나안족, 히위족, 여부스족의 땅으로 인도할 것이다. 내가 그들을 완전히 없애 버리겠다.

24너희는 그들의 신을 숭배하거나 섬기지 말아라. 그들의 행위를 본받지 말고 그들의 신을 없애 버리며 신상이 새겨진 돌기둥을 부숴 버리고

25너희 하나님 나 여호와를 섬겨라. 그러면 내가 너희 양식과 물에 복을 내리고 너희 가운데 병을 없애겠다.

26너희 땅에 낙태하거나 아이를 낳지 못하는 여자가 없을 것이며 23:26 또는 ‘내가 너희 날수를 채우리라’너희가 장수하게 될 것이다.

27“너희가 만나는 백성들을 내가 두려움과 혼란 가운데 빠뜨려 너희를 등지고 달아나게 할 것이며

28또 너희가 전진할 때 내가 히위족과 가나안족과 헷족에게 23:28 원문에는 ‘왕벌을 네 앞에 보내리니’공포심을 일으켜 그들을 너희 앞에서 쫓아내겠다.

29그러나 내가 그들을 년 안에 다 쫓아내지는 않을 것이다. 만일 내가 그렇게 한다면 그 땅이 황폐해지고 들짐승이 득실거려 너희에게 피해가 클 것이다.

30그래서 너희가 그 땅을 소유할 만큼 인구가 증가할 때까지 내가 그들을 조금씩 서서히 쫓아내겠다.

31내가 너희 땅의 경계선을 홍해에서 23:31 또는 ‘블레셋 바다’지중해 연안까지, 그리고 23:31 또는 ‘광야에서부터 하수까지’아라비아 사막에서 유프라테스강까지 정하고 그 땅의 백성들을 너희에게 넘겨 주겠다. 너희가 그들을 너희 앞에서 쫓아내게 될 것이다.

32너희는 그들이나 그들의 신들과 계약을 맺지 말아라.

33너희는 그들을 너희 땅에 살지 못하게 하라. 그렇지 않으면 그들 때문에 너희가 나에게 범죄할 것이다. 너희가 그들의 신을 섬기면 그것이 너희에게 덫이 될 것이다.”