ዘፀአት 19 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 19:1-25

በሲና ተራራ ላይ

1በሦስተኛው ወር እስራኤላውያን ከግብፅ ለቀው በወጡበት በዚያችው ዕለት ወደ ሲና ምድረ በዳ መጡ። 2ከራፊዲም ከተነሡ በኋላ ወደ ሲና ምድረ በዳ ገቡ፤ እስራኤልም በዚያ በምድረ በዳው በተራራው ፊት ለፊት ሰፈሩ።

3ከዚያም ሙሴ ወደ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ወጣ፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) ከተራራው ጠራውና እንዲህ አለው፤ “ለያዕቆብ ቤት የምትለው ለእስራኤልም ሕዝብ የምትናገረው ይህ ነው፤ 4‘በግብፅ ላይ ያደረግሁትን፣ በንስርም ክንፍ ተሸክሜ ወደ ራሴ እንዴት እንዳመጣኋችሁ እናንተ ራሳችሁ አይታችኋል። 5አሁንም በፍጹም ብትታዘዙኝና ቃል ኪዳኔን ብትጠብቁ እነሆ ከአሕዛብ ሁሉ እናንተ የተወደደ ርስቴ ትሆናላችሁ፤ ምንም እንኳ ምድር ሁሉ የእኔ ብትሆንም፣ 6እናንተ19፥6 ወይም ምድር ሁሉ የእኔ ርስት ናት፤ እናንተ ለእኔ የመንግሥት ካህናት የተቀደሰ ሕዝብ ትሆናላችሁ፤’ ለእስራኤላውያን የምትነግራቸው ቃሎች እነዚህ ናቸው።”

7ስለዚህ ሙሴ ተመልሶ የሕዝቡን አለቆች አስጠራ፤ እንዲናገር እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘውን ቃሎች ሁሉ ነገራቸው። 8ሕዝቡም ሁሉ በአንድ ላይ “እግዚአብሔር (ያህዌ) ያለውን ሁሉ እናደርጋለን” ብለው መለሱ፤ ስለዚህ ሙሴ እነርሱ ያሉትን መልሶ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ወሰደ።

9እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “ከአንተ ጋር ስናገር ሕዝቡ እንዲሰሙኝና እምነታቸውን ምንጊዜም በአንተ ላይ እንዲጥሉ በከባድ ደመና ወደ አንተ እመጣለሁ” ከዚያም ሙሴ ሕዝቡ ያሉትን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ነገረው።

10እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “ወደ ሕዝቡ ሂድና ዛሬና ነገ ቀድሳቸው፤ ልብሳቸውን እንዲያጥቡ አድርግ፤ 11በሦስተኛውም ቀን ይዘጋጁ፤ ምክንያቱም በዚያ ቀን በሕዝቡ ፊት እግዚአብሔር (ያህዌ) በሲና ተራራ ላይ ይወርዳል። 12በተራራው ዙሪያ ለሕዝቡ ወሰን አበጅተህ እንዲህ በላቸው፤ ‘ወደ ተራራው እንዳትወጡ ወይም ግርጌውን እንዳትነኩ ተጠንቀቁ፤ ማንም ተራራውን ቢነካ በርግጥ ይሞታል። 13በድንጋይ ይወገራል ወይም በቀስት ይወጋል፤ ምንም እጅ በእርሱ ላይ አያርፍም፤ ሰውም ሆነ እንስሳ በሕይወት እንዲኖር አይተውም።’ ወደ ተራራው መውጣት የሚችሉት ከፍ ባለ ድምፅ መለከት በተነፋ ጊዜ ብቻ ነው።”

14ሙሴ ከተራራው ወርዶ ወደ ሕዝቡ ከሄደ በኋላ ቀደሳቸው፤ ልብሳቸውንም ዐጠቡ። 15ከዚያም ለሕዝቡ፣ “ለሦስተኛው ቀን ራሳችሁን አዘጋጁ፤ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ከማድረግ ተቈጠቡ” አላቸው።

16በሦስተኛውም ቀን ጧት ከባድ ደመና በተራራው ላይ ሆኖ ነጐድጓድና መብረቅ እንዲሁም ታላቅ የቀንደ መለከት ድምፅ ነበር፤ በሰፈሩ ያሉት ሁሉ ተንቀጠቀጡ። 17ከዚያም ሙሴ ከእግዚአብሔር (ያህዌ) ጋር ለማገናኘት ሕዝቡን ከሰፈር ይዞ ወጣ፤ ከተራራውም ግርጌ ቆሙ። 18የሲና ተራራ እግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት ስለወረደበት በጢስ ተሸፍኖ ነበር። ጢሱ ከምድጃ እንደሚወጣ ጢስ ወደ ላይ ተትጐለጐለ፤ ተራራውም በሙሉ19፥18 ብዙ የዕብራይስጥ ቅጆችና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ ሕዝቡ ሁሉ ይላሉ። በኀይል ተናወጠ። 19የመለከቱም ድምፅ እያየለ መጣ። ከዚያም ሙሴ ተናገረ፤ እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) በድምፅ መለሰለት።19፥19 ወይም፣ እግዚአብሔርም በነጐድጓድ መለሰለት

20እግዚአብሔር (ያህዌ) በሲና ተራራ ጫፍ ላይ ወረደ፤ ሙሴን ወደ ተራራው ጫፍ ጠራው፤ ሙሴም ወጣ። 21እግዚአብሔርም (ያህዌ) እንዲህ አለው፤ “ሕዝቡ እግዚአብሔርን (ያህዌ) ለማየት በመጣደፍ ብዙዎቹ እንዳይጠፉ ውረድና አስጠንቅቃቸው 22ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚቀርቡት ካህናት እንኳ ራሳቸውን መቀደስ አለባቸው፤ አለዚያ እግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣውን ያወርድባቸዋል።”

23ሙሴ እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲህ አለው፤ “ሕዝቡ ወደ ሲና ተራራ ሊወጡ አይችሉም፤ ምክንያቱም አንተ ራስህ ‘በተራራው ዙሪያ ወሰን አድርግ፤ የተቀደሰም በማድረግ ለየው’ በማለት አስጠንቅቀኸናልና።”

24እግዚአብሔርም (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “ውረድና አሮንን ከአንተ ጋር ይዘኸው ውጣ፤ ካህናቱና ሕዝቡ ግን ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ለመምጣት መጣደፍ የለባቸውም፤ አለዚያ እርሱ ቍጣውን ያወርድባቸዋል።”

25ስለዚህ ሙሴ ወደ ሕዝቡ ወርዶ ነገራቸው።

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 19:1-25

ที่ภูเขาซีนาย

1ในเดือนที่สามหลังจากชนชาติอิสราเอลออกจากอียิปต์ ในวันนั้นพวกเขาก็มาถึงถิ่นกันดารซีนาย 2เมื่อเขาเดินทางออกจากเรฟีดิมแล้ว พวกเขาก็เข้าเขตถิ่นกันดารซีนายและชาวอิสราเอลตั้งค่ายหน้าภูเขาซีนาย

3แล้วโมเสสขึ้นไปเข้าเฝ้าพระเจ้า องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเรียกเขาจากภูเขานั้นและตรัสว่า “เจ้าจงบอกพงศ์พันธุ์ของยาโคบและจงกล่าวแก่ประชากรอิสราเอลว่า 4‘พวกเจ้าเองได้เห็นสิ่งที่เรากระทำแก่ชาวอียิปต์แล้ว และเห็นวิธีที่เราพาเจ้ามาเหมือนลูกนกอินทรีบนปีกแม่ของมัน และนำเจ้ามาถึงเรา 5บัดนี้หากเจ้าทั้งหลายเชื่อฟังเราอย่างหมดใจและรักษาพันธสัญญาของเรา เจ้าก็จะเป็นกรรมสิทธิ์ล้ำค่าของเราจากประชาชาติทั้งปวงทั่วโลก ถึงแม้ทั้งโลกนี้เป็นของเรา 6แต่เจ้า19:5,6 หรือประชาชาติทั้งปวงทั่วโลก เพราะทั้งโลกนี้เป็นของเรา 6เจ้าจะเป็นอาณาจักรแห่งปุโรหิตและเป็นชนชาติที่บริสุทธิ์สำหรับเรา’ เจ้าจงบอกชนชาติอิสราเอลตามนี้”

7โมเสสจึงกลับลงมาจากภูเขา แล้วเรียกประชุมผู้อาวุโสของอิสราเอลมาแจ้งให้พวกเขาทราบทุกถ้อยคำที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาให้เขากล่าว 8ประชากรทั้งปวงตอบเป็นเสียงเดียวกันว่า “เราจะทำทุกสิ่งตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่ง” โมเสสจึงนำคำตอบของพวกเขามากราบทูลองค์พระผู้เป็นเจ้า

9องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “เราจะมาหาเจ้าในเมฆหนาทึบ เพื่อเหล่าประชากรจะได้ยินเสียงเราพูดกับเจ้า และเขาจะได้ไว้วางใจในตัวเจ้าเสมอไป” โมเสสจึงกราบทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าตามคำของประชากร

10องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงไปหาเหล่าประชากร ชำระพวกเขาให้บริสุทธิ์ทั้งวันนี้และวันพรุ่งนี้ ให้เขาซักเสื้อผ้า 11และเตรียมตัวให้พร้อมสำหรับวันที่สาม เพราะในวันนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจะลงมาที่ภูเขาซีนายต่อหน้าประชากรทั้งปวง 12จงกำหนดเขตห้ามประชากรล่วงล้ำเข้ามาบริเวณภูเขา บอกเขาว่า ‘จงระวังให้ดี อย่าให้ใครขึ้นมาบนภูเขาหรือแตะต้องเชิงเขานั้น ใครแตะต้องภูเขานั้นจะมีโทษถึงตาย 13อย่าให้มือของใครแตะต้องผู้ที่ฝ่าฝืนนั้น แต่ให้เอาหินขว้างเขาหรือยิงด้วยลูกธนูจนตาย ไม่ว่าเป็นคนหรือสัตว์ เมื่อฝ่าฝืนจะต้องตาย’ และประชาชนจะขึ้นไปบนภูเขาได้ก็ต่อเมื่อได้ยินเสียงเป่าเขาสัตว์เป็นสัญญาณยาวหนึ่งครั้งแล้วเท่านั้น”

14จากนั้นโมเสสจึงลงจากภูเขามาหาเหล่าประชากร เขาชำระประชากรให้บริสุทธิ์และให้พวกเขาซักเสื้อผ้าของตนให้สะอาด 15แล้วเขาบอกกับประชากรว่า “จงเตรียมตัวให้พร้อมสำหรับวันที่สาม จงงดเพศสัมพันธ์ในช่วงนี้”

16เช้าวันที่สามมีฟ้าแลบฟ้าร้องน่าสะพรึงกลัวและมีเมฆทะมึนปกคลุมภูเขานั้น แล้วมีเสียงเป่าแตรดังก้อง ทุกคนในค่ายตกใจกลัวจนตัวสั่น 17โมเสสจึงนำพวกเขาออกจากค่ายพักมาเข้าเฝ้าพระเจ้า พวกเขายืนอยู่ที่เชิงเขา 18มีควันหนาทึบปกคลุมภูเขาซีนาย เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าเสด็จลงมาโดยไฟ ควันพวยพุ่งขึ้นสู่ท้องฟ้าเหมือนควันจากเตาหลอม ทั้งภูเขา19:18 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูบางฉบับ และ LXX. ว่าประชากรทั้งหมดสั่นสะเทือนอย่างรุนแรง 19เสียงแตรดังก้องขึ้นเรื่อยๆ โมเสสจึงทูลพระเจ้า และมีพระสุรเสียงของพระองค์ตรัสตอบเขา19:19 หรือและพระเจ้าตรัสตอบเขาเป็นเสียงฟ้าร้อง

20องค์พระผู้เป็นเจ้าเสด็จลงมาที่ยอดเขาซีนายและตรัสเรียกโมเสสขึ้นบนยอดเขา โมเสสก็ขึ้นไป 21องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงกลับลงไปเตือนประชากรไม่ให้รุกล้ำเขตขึ้นมาเพราะอยากเห็นองค์พระผู้เป็นเจ้ามิฉะนั้นพวกเขาจะต้องตาย 22แม้แต่บรรดาปุโรหิตซึ่งเข้าใกล้องค์พระผู้เป็นเจ้าก็ต้องชำระตนให้บริสุทธิ์ มิฉะนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงทำลายพวกเขา”

23โมเสสกราบทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “ประชาชนทั้งหลายจะขึ้นมาบนภูเขาซีนายไม่ได้ เพราะพระองค์เองทรงเตือนข้าพระองค์ทั้งหลายไว้ว่า ‘ให้กำหนดเขตรอบภูเขาแยกไว้เป็นเขตบริสุทธิ์ศักดิ์สิทธิ์’ ”

24องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงตอบว่า “จงลงไปพาอาโรนขึ้นมาด้วย แต่อย่าให้บรรดาปุโรหิตหรือประชากรรุกล้ำเขตเพื่อหาทางขึ้นมาหาองค์พระผู้เป็นเจ้ามิฉะนั้นเราจะลงโทษพวกเขา”

25ดังนั้นโมเสสจึงลงไปแจ้งแก่ประชากร