ዘዳግም 27 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 27:1-26

በጌባል ተራራ ላይ የቆመ መሠዊያ

1ሙሴና የእስራኤል አለቆች ሕዝቡን እንዲህ ብለው አዘዙ፤ “ዛሬ የማዝዛችሁን እነዚህን ትእዛዞች ሁሉ ጠብቁ፤ 2አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ወደሚሰጥህ ምድር ለመግባት ዮርዳኖስን በተሻገራችሁ ጊዜ፣ ጥቂት ትልልቅ ድንጋዮችን አቁምና በኖራ ቅባቸው። 3የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሰጠህ ተስፋ መሠረት፣ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ወደሚሰጥህ ምድር ለመግባት ዮርዳኖስን ስትሻገር፣ የዚህን ሕግ ቃላት ሁሉ ጻፍባቸው። 4ዮርዳኖስን እንደ ተሻገርህም፣ ዛሬ ባዘዝሁህ መሠረት እነዚህን ድንጋዮች በጌባል ተራራ ላይ ትከላቸው፤ በኖራም ቅባቸው። 5እዚያም ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የድንጋይ መሠዊያ ሥራ፤ በድንጋዮቹም ላይ ማናቸውንም የብረት መሣሪያ አታሳርፍባቸው። 6የአምላክህን የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) መሠዊያ ካልተጠረበ ድንጋይ ሥራ፤ በላዩም ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሚቃጠል መሥዋዕት አቅርብበት። 7በዚያም የኅብረት መሥዋዕት27፥7 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት በመባል ይታወቃል ሠዋ፤ ብላም፤ በአምላክህ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ደስ ይበልህ። 8በድንጋዮቹ ላይ የዚህን ሕግ ቃላት ሁሉ ግልጽ አድርገህ ጻፍባቸው።”

በጌባል ተራራ ላይ የተነገረ መርገም

9ሙሴና ሌዋውያን ካህናትም ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ አሉ፤ “እስራኤል ሆይ፤ ጸጥ ብለህ አድምጥ! አንተ ዛሬ የአምላክህ የእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ሕዝብ ሆነሃል፤ 10አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ታዘዝ፤ ዛሬ የምሰጥህን ትእዛዙንና ሥርዐቱን ጠብቅ።”

11ሙሴ በዚያኑ ዕለት ሕዝቡን እንዲህ ብሎ አዘዘ፦

12ዮርዳኖስን በተሻገራችሁ ጊዜ፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዮሴፍና ብንያም ሕዝቡን ለመባረክ በገሪዛን ተራራ ላይ ይቁሙ። 13ሮቤል፣ ጋድ፣ አሴር፣ ዛብሎን፣ ዳንና ንፍታሌምም በጌባል ተራራ ላይ ለመርገም ይቁሙ።

14ሌዋውያን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ እንዲህ ብለው ይናገሩ፦

15“የእጅ ጥበብ ባለሙያ የሠራውን፣ በእግዘአብሔር (ያህዌ) ዘንድ አስጸያፊ የሆነውን ምስል የሚቀርጽ ወይም ጣዖትን የሚያበጅ፣ በስውርም የሚያቆም ሰው የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

16“አባቱን ወይም እናቱን የሚያቃልል የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን! ይበል።

17“የባልንጀራውን የድንበር ድንጋይ ከቦታው የሚያንቀሳቅስ የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

18“ዐይነ ስውሩን በተሳሳተ መንገድ የሚመራ፣ የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

19“በመጻተኛው፣ አባት በሌለውና በመበለቲቱ ላይ ፍትሕ የሚያዛባ የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

20“ከአባቱ ሚስት ጋር የሚተኛ የተረገመ ይሁን፤ የአባቱን መኝታ ያረክሳልና።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

21“ከማናቸውም እንስሳ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚያደርግ የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

22“የአባቱ ወይም የእናቱ ልጅ ከሆነችው እኅቱ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚፈጽም የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

23“ከዐማቱ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚፈጽም የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

24“በድብቅ ባልንጀራውን የሚገድል የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

25“ንጹሕን ሰው ለመግደል ጕቦ የሚቀበል የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

26“የዚህን ሕግ ቃሎች በመፈጸም የማይጸና የተረገመ ይሁን።”

ሕዝቡም ሁሉ፣ “አሜን!” ይበል።

Japanese Contemporary Bible

申命記 27:1-26

27

エバル山に建てる記念碑

1さらに、モーセとイスラエルの長老たちは、民に次のような指示を与え、そのとおり行うよう命じました。 2-4「ヨルダン川を渡り、約束の地、乳とみつの流れる地に入ったら、川底から丸い石を取り、川向こうのエバル山に記念碑を建てなさい。石の表面には石灰を塗り、神様の律法のすべてのことばを書き記しなさい。 5-6またそこに、主のために祭壇を築きなさい。自然のままの丸い石を積み重ね、その上で、焼き尽くすいけにえをささげるのです。 7さらに和解のいけにえをささげ、あなたの神、主の前で喜び祝いなさい。 8重ねて言いますが、記念碑にこの律法のことばをすべてはっきりと書き記しなさい。」

のろいの宣言

9それから、モーセとレビ人の祭司たちとは、イスラエルのすべての民に呼びかけました。「みんな、よく聞きなさい。今日、あなたがたは主の民となりました。 10だから今日から、主の御声に聞き従い、今日、私が与える律法を行いなさい。」

11その日、モーセは民に命じました。 12「約束の地に入ったら、シメオン、レビ、ユダ、イッサカル、ヨセフ、ベニヤミンの各部族は、ゲリジム山に立って祝福を告げ、 13ルベン、ガド、アシェル、ゼブルン、ダン、ナフタリの各部族は、エバル山に立ってのろいを告げなさい。 14それから、レビ人が両者の間に立って全国民に向かって宣言しなさい。

15『隠れて、彫像や鋳像を造って拝む者はのろわれる。主は人間が造った神々を憎まれるからだ。』民はみな、『アーメン』(「そのとおりです」「そうしてください」の意)と答えなさい。

16『親を侮辱する者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

17『隣人の土地との境界線を移す者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

18『盲人の弱みにつけ込む者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

19『在留外国人、身寄りのない子、未亡人などに不正を働く者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

20『父の妻(義理の母)と寝る者はのろわれる。彼女は父親のものだからだ。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

21『獣姦をする者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

22『異父姉妹であれ異母姉妹であれ、自分の姉妹と寝る者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

23『妻の母と寝る者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

24『ひそかに殺人を犯す者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

25『報酬をもらって、罪のない人を殺す者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。

26『この律法を守らない者はのろわれる。』民はみな、『アーメン』と答えなさい。