ዘዳግም 23 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 23:1-25

ከእግዚአብሔር ጉባኤ መለየት

1ብልቱ የተቀጠቀጠ ወይም የተቈረጠ ማናቸውም ሰው ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጉባኤ አይግባ።

2ዲቃላም ይሁን የዲቃላው ዘር የሆነ ሁሉ፣ እስከ ዐሥር ትውልድ ድረስ እንኳን ቢሆን ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጉባኤ አይግባ።

3አሞናዊም ሆነ ሞዓባዊ ወይም ማናቸውም የእርሱ ዘር፣ እስከ ዐሥር ትውልድ እንኳ ቢሆን ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጉባኤ አይግባ። 4ምክንያቱም ከግብፅ ከወጣችሁ በኋላ በጕዞ ላይ በነበራችሁበት ጊዜ እህል ውሃ ይዘው አልተቀበሏችሁም፤ በመስጴጦምያ በምትገኘው በፐቶር23፥4 ይኸውም ሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ነው። ይኖር የነበረውን የቢዖር ልጅ በለዓምን አንተን እንዲረግም በገንዘብ ገዙት። 5ይሁን እንጂ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በለዓምን አልሰማውም፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ስለሚወድህ ርግማኑን በረከት አደረገልህ። 6በሕይወት ዘመንህ ሁሉ ሰላምን ለእነርሱ አትመኝ።

7ወንድምህ ስለሆነ ኤዶማዊውን አትጸየፈው፤ መጻተኛ ሆነህ በአገሩ ኖረሃልና ግብፃዊውን አትጥላው። 8ለእነርሱ የተወለዱላቸው የሦስተኛው ትውልድ ልጆች ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጉባኤ መግባት ይችላሉ።

የጦር ሰፈር ንጽሕና አጠባበቅ

9ጠላትህን ለመውጋት ወጥተህ በሰፈርህ ጊዜ፣ ከማናቸውም ርኩሰት ራስህን ጠብቅ። 10ከመካከላችሁ ሌሊት ዘር በማፍሰስ የረከሰ ሰው ቢኖር፣ ከሰፈር ወጥቶ እዚያው ይቈይ። 11እየመሸ ሲመጣ ግን ገላውን ይታጠብ፤ ፀሓይ ስትጠልቅም ወደ ሰፈሩ ይመለስ።

12ለመጸዳጃ የሚሆንህን ቦታ ከሰፈር ውጭ አዘጋጅ። 13ከትጥቅህም ጋር መቈፈሪያ ያዝ፤ በምትጸዳዳበት ጊዜ ዐፈር ቈፍረህ በዐይነ ምድርህ ላይ መልስበት። 14አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ሊጠብቅህ ጠላቶችህንም በእጅህ አሳልፎ ሊሰጥህ በሰፈር ውስጥ ስለሚዘዋወር፣ በመካከልህ አንዳች ነውር አይቶ ከአንተ እንዳይመለስ፣ ሰፈርህ የተቀደሰ ይሁን።

ልዩ ልዩ ሕጎች

15አንድ ባሪያ ከአሳዳሪው ኰብልሎ ወደ አንተ ቢመጣ፣ ለአሳዳሪው አሳልፈህ አትስጠው። 16ደስ በሚያሰኘው ቦታና ራሱ በመረጠው ከተማ በመካከልህ ይኑር፤ አንተም አታስጨንቀው።

17ወንድ ወይም ሴት እስራኤላዊ የቤተ ጣዖት አመንዝራ አይሁን። 18ለዝሙት ዐዳሪ ሴት ወይም ለወንደቃ23፥18 ዕብራይስጡ፣ ውሻ ይላል። የተከፈለውን ዋጋ ለማናቸውም ስእለት አድርገህ ለመስጠት ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ቤት አታምጣ፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ሁለቱንም ይጸየፋቸዋልና።

19የገንዘብ፣ የእህል ወይም የማንኛውንም ነገር ወለድ ለማግኘት ለወንድምህ በወለድ አታበድር። 20ባዕድ ለሆነ ሰው ወለድ ማበደር ትችላለህ፤ ነገር ግን ልትወርሳት በምትገባባት ምድር እጅህ በሚነካው በማናቸውም ነገር አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንዲባርክህ ለእስራኤላዊ ወንድምህ በወለድ አታበድረው።

21ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ስእለት ከተሳልህ፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አጥብቆ ከአንተ ይሻዋልና፣ ኀጢአት እንዳይሆንብህ ለመክፈል አትዘግይ። 22ሳትሳል ብትቀር ግን በደለኛ አትሆንም። 23በአንደበትህ የተናገርኸውን ሁሉ ለመፈጸም ጠንቃቃ ሁን፤ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በገዛ አንደበትህ ፈቅደህ ስእለት ተስለሃልና።

24ወደ ባልንጀራህ የወይን ተክል ቦታ በምትገባበት ጊዜ፣ ያሰኘህን ያህል መብላት ትችላለህ፤ ነገር ግን አንዳችም በዕቃህ አትያዝ። 25ወደ ባልንጀራህ ዕርሻ በምትገባበት ጊዜ፣ እሸት መቅጠፍ ትችላለህ፤ በሰብሉ ላይ ግን ማጭድ አታሳርፍበት።

New International Reader’s Version

Deuteronomy 23:1-25

Who Can Join in Worship With the Lord’s People?

1No man whose sex organs have been crushed or cut can join in worship with the Lord’s people.

2No one born to an unmarried woman can join in worship with the Lord’s people. That also applies to the person’s children for all time to come.

3The people of Ammon and Moab can’t join in worship with the Lord’s people. That also applies to their children after them for all time to come. 4The Ammonites and Moabites didn’t come to meet you with food and water on your way out of Egypt. They even hired Balaam from Pethor in Aram Naharaim to put a curse on you. Balaam was the son of Beor. 5The Lord your God wouldn’t listen to Balaam. Instead, he turned the curse into a blessing for you. He did it because he loves you. 6So don’t make a peace treaty with the Ammonites and Moabites as long as you live.

7Don’t hate the people of Edom. They are your relatives. Don’t hate the people of Egypt. After all, you lived as outsiders in their country. 8The great-grandchildren of the Edomites and Egyptians can join in worship with the Lord’s people.

Keep the Camp of the Soldiers Pure and “Clean”

9There will be times when you are at war with your enemies. And your soldiers will be in camp. Then keep away from anything that isn’t pure and “clean.” 10Suppose semen flows from the body of one of your soldiers during the night. Then that will make him “unclean.” He must go outside the camp and stay there. 11But as evening approaches, he must wash himself. When the sun goes down, he can return to the camp.

12Choose a place outside the camp where you can go to the toilet. 13Keep a shovel among your tools. When you go to the toilet, dig a hole. Then cover up your waste. 14The Lord your God walks around in your camp. He’s there to keep you safe. He’s also there to hand your enemies over to you. So your camp must be holy. Then he won’t see anything among you that is shameful. He won’t turn away from you.

Several Other Laws

15If a slave comes to you for safety, don’t hand them over to their master. 16Let them live among you anywhere they want to. Let them live in any town they choose. Don’t treat them badly.

17A man or woman in Israel must not become a temple prostitute. 18The Lord your God hates the money that men and women get for being prostitutes. So don’t take that money into the house of the Lord to pay what you promised to give.

19Don’t charge your own people any interest. Don’t charge them when they borrow money, food or anything else. 20You can charge interest to people from another country. But don’t charge your own people. Then the Lord your God will bless you in everything you do. He will bless you in the land you are entering to take as your own.

21Don’t put off giving to the Lord your God everything you promise him. He will certainly require it from you. And you will be guilty of committing a sin. 22But if you don’t make a promise, you won’t be guilty. 23Make sure you do what you promised to do. With your own mouth you made the promise to the Lord your God. No one forced you to do it.

24When you enter your neighbor’s vineyard, you can eat all the grapes you want. But don’t put any of them in your basket. 25When you enter your neighbor’s field, you can pick heads of grain. But don’t cut down their standing grain.